Get Mystery Box with random crypto!

የህይወት ቃል / Word of life

የቴሌግራም ቻናል አርማ dailywordoflife — የህይወት ቃል / Word of life
የቴሌግራም ቻናል አርማ dailywordoflife — የህይወት ቃል / Word of life
የሰርጥ አድራሻ: @dailywordoflife
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.80K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የቴሌግራም ቻናል በየእለቱ ህይወት ከሆነው ከእግዚአብሔር ቃል አጠር ያለ መልእክት የሚቀርብበት ነው። ይህንን ቻናል በመቀላቀልና አብረን ይህንን የህይወት ቃል እንድንመረምር እናድማችኋለን። ጥያቄ ወይም አስተያየት ቢኖራችሁ በዚህ አድራሻ ጻፉልን። @melakalex ወይም 254724416340

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2022-07-10 06:51:25 ያንጸው
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሞት የሚገባን ህይወት ሊሰጠን የሰማይ ዙፋኑን ለቆ የእኛን የተዋረደ ተፈጥሮ በመልበስ ወደ ምድር መጣ፤ እስከ መስቀል ሞት ድረስ ታዛዥ በመሆን ድንቅ መስዋእትነትን ከፍሎ አዳነን። የእርሱ ተል እኮ “ለታሰሩት መፈታትን፣ለታወሩትም ማየትን ማወጅ፣ የተጨቈኑትንም ነጻ ማውጣት” ነበር። የእርሱ ተከታዮች የሆኑትንም በጨለማ ያሉትን፣ በተለያየ ፈተና የደቀቁትን “መንገድ፣ እውነትና ህይወት ወደ ሆነው ወደ ክርስቶስ” በማደም እነርሱም የማነጽ ስራ እንዲሰሩ ይፈልጋል።
እርስ በርሳችን እየተናነጽን፣ የክፋት ጨለማ በዋጣት አለም ውስጥ እየዳከሩ ያሉትን በክርስቶስ ጸጋ ወደ ወንጌል ብርሃን ልናመለክታቸው ይገባል።
ይህንን ለማድረግ ደግሞ ከአፋችን ስለሚወጣው ቃል ቃሉ የሚመክረንን በትኩረት ማሰብና ያንንም መለማመድ እንድንችል መጸለይ ያስፈልገናል ፦
ለእያንዳንዱ ሰው እንዴት መልስ መስጠት እንደሚገባችሁ ታውቁ ዘንድ ንግግራችሁ በጨው እንደ ተቀመመ ሁል ጊዜ በጸጋ የተሞላ ይሁን። ቆላ 4:6
እንደ አስፈላጊነቱ ሌሎችን የሚያንጽና ሰሚዎችን የሚጠቅም ቃል እንጂ የማይረባ ቃል ከአፋችሁ አይውጣ። ኤፌ 4:29
አባት ሆይ፣ በንግግርም ሆነ በጽሁፍ፣ በማንኛውም መንገድ ከእኛ የሚወጣው ነገር በጸጋ የተቀመመ፣ ሌሎችን የሚያንጽ፣ ሰሚዎችን የሚጠቅም ቃል እንዲሆንልን በጸጋህ እርዳን። አሜን።
263 views03:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-10 06:51:20
225 views03:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-09 07:41:15 ይቅር በሉ
ጥላቻ፣ መራርነት፣ ቂምና በቀል አየሩን በሞላበት በዚህ ጊዜ የክርስቶስ ደቀ መዛሙርት የሆንን ሁሉ፣ እርሱ ስለ ይቅርታ ያስተማረንን ልናስታውስ ያስፈልጋል። በወንጌላት ውስጥ ጌታችን ስለ ይቅርታ ያስተማራቸው ሰባት ጥቅሶች ከዚህ በታች ቀርበዋል፦ በጸሎት መንፈስ ራሳችንን እየመረመርን እናንብባቸው።
አንደኛ ፣
“ስለዚህ መባህን በመሠዊያው ላይ ለእግዚአብሔር በምታቀርብበት ጊዜ ወንድምህ የተቀየመብህ ነገር መኖሩ ትዝ ቢልህ፣ መባህን በዚያው በመሠዊያው ፊት ተወው፤ በመጀመሪያ ሄደህ ከወንድምህ ጋር ተስማማ፤ ከዚያም ተመልሰህ መባህን ለእግዚአብሔር አቅርብ። ማቴ 5:23፣ 24
ሁለተኛ፣
“እናንተ ግን እንዲህ ብላችሁ ጸልዩ፤ … እኛም ደግሞ የበደሉንን ይቅር እንደምንል፣
በደላችንን ይቅር በለን።” ማቴ 6:12
ሶስተኛ፣
“እናንተ የበደሏችሁን ይቅር ብትሉ የሰማዩ አባታችሁ ደግሞ እናንተን ይቅር ይላችኋል። ነገር ግን የሰዎችን ኀጢአት ይቅር የማትሉ ከሆነ፣ አባታችሁም ኀጢአታችሁን ይቅር አይልላችሁም።” ማቴ 6:14፣ 15
አራተኛ፣
“ስለዚህ መንግሥተ ሰማይ፣ በአገልጋዮቹ እጅ የነበረውን ሂሳብ ለመተሳሰብ የፈለገን ንጉሥ ትመስላለች። ሂሳቡን ማጣራት እንደ ጀመረም ዐሥር ሺህ ታላንት ዕዳ ያለበትን አንድ አገልጋይ አቀረቡለት። አገልጋዩም ያለበትን ዕዳ መክፈል ስላቃተው እርሱ ራሱ፣ ሚስቱ፣ ልጆቹና ንብረቱ ሁሉ ተሽጠው ዕዳው እንዲከፈል ጌታው አዘዘ።
“በዚህ ጊዜ አገልጋዩ እግሩ ላይ ወድቆ፣ ‘ታገሰኝ፣ ያለብኝን ዕዳ ሁሉ እከፍልሃለሁ’ ሲል ለመነው። ጌታውም አዘነለትና ማረው፤ ዕዳውንም ትቶለት አሰናበተው።
“ያ አገልጋይ ከጌታው ፊት እንደ ወጣ አንድ መቶ ዲናር የእርሱ ዕዳ ያለበትን አገልጋይ ባልንጀራውን አግኝቶ እንቅ አድርጎ በመያዝ፣ ‘ያለብህን ዕዳ ክፈለኝ!’ አለው።
“ባልንጀራው አገልጋይም ከፊቱ ወድቆ፣ ‘ታገሠኝ እከፍልሃለሁ’ ብሎ ለመነው።
“ነገር ግን ሊታገሠው ፈቃደኛ ስላልነበረ፣ ያለበትን ዕዳ እስኪከፍለው ድረስ ወህኒ ቤት አስገባው። 31የሆነውን ነገር ያዩ ሌሎች አገልጋዮችም በጣም አዘኑ፤ ሄደውም ሁኔታውን በሙሉ ለጌታቸው ነገሩት።
“በዚህ ጊዜ ጌታው አገልጋዩን አስጠርቶ እንዲህ አለው፤ ‘አንተ ክፉ አገልጋይ፤ ስለ ለመንኸኝ ያን ሁሉ ዕዳ ተውሁልህ፤ እኔ እንደ ማርሁህ አንተም ባልንጀራህን ልትምረው አይገባህም ነበርን?’ በቍጣም ያለበትን ዕዳ ከፍሎ እስኪጨርስ ድረስ ለአሳሪዎች አሳልፎ ሰጠው።
“ስለዚህ እያንዳንዳችሁ ወንድሞቻችሁን ከልባችሁ ይቅር ካላላችሁ፣ የሰማዩ አባቴም እንደዚሁ ያደርግባችኋል።” ማቴ 18፡ 25- 35
አምስተኛ፣
“እንዲሁም ለጸሎት በምትቆሙበት ጊዜ፣ የሰማዩ አባታችሁ ኀጢአታችሁን ይቅር እንዲልላችሁ፣ እናንተም በሰው ላይ ያላችሁን ሁሉ ይቅር በሉ። ይቅር ባትሉ ግን የሰማዩ አባታችሁ ኀጢአታችሁን ይቅር አይላችሁም።” ማር 11:25፣ 26
ስድስተኛ፣
“አትፍረዱ፤ አይፈረድባችሁም፤ አትኰንኑ፤ አትኰነኑም። ይቅር በሉ፤ ይቅር ትባላላችሁ።” ሉቃ 6:37
ሰባተኛ፣
“ወንድምህ ቢበድል ገሥጸው፤ ቢጸጸት ይቅር በለው። በቀን ሰባት ጊዜ ቢበድልህና ሰባት ጊዜ፣ ‘ተጸጽቻለሁ’ እያለ ወደ አንተ ቢመለስ ይቅር በለው።” ሉቃ 17፡ 1,4
አባት ሆይ፣ ይቅር ባይ ልብ ስጠን።
262 views04:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-09 07:41:07
233 views04:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 07:18:03 ምዕራፍ 13 - በጌታ መደሰት
ክፍል ዘጠኝ
የእግዚአብሔር ልጆች «እናንተ የአባቴ ብሩካን ኑ ዓለም ሳይፈጠር በፊት የተዘጋጀላችሁን የእግዚአብሔር መንግስት ውሰዱ» (ማቴ. 25:34) የሚሉ በጆሮአቸው የሚያስተጋቡ ፣ ሙዚቃዊ ቃና ያላቸው ፣ ከንጉሱ አፍ የሚፈሱ ክቡር የባርኮት ቃላትን እያደመጡ ሳለ የገነት ደጆች እነርሱን ለመቀበል ወለል ብለው ይከፈታሉ።
በዚያን ጊዜ የተዋጁት ይገቡበት ዘንድ አስቀድሞ ለእነርሱ በኢየሱስ ወደተዘጋጀላቸው ስፍራ «እንኳን ደህና መጣችሁ!» ይባላሉ፡፡ በዚያ ስፍራ አብረዋቸው የሚሆኑት የምድር ከንቱነት የተጠናወታቸው፣ ውሸታሞች፣ ጣዖት አምላኪዎች፣ እራሳቸውን ያላነፁና ያላመኑ ሳይሆኑ፣ ሰይጣንን አሸንፈው በመለኮታዊ ፀጋ ፍፁም የሆነውን ባህሪ ያገኙ ናቸው:: በዚህ ምድር ሲያጎሳቁላቸው የነበረው የኃጢአት ዝንባሌ፣ ኃጢአትና ግሳንግሱ ሁሉ በክርስቶስ ደም ከእነርሱ ተወግዷልና የእርሱ ልሒቅነት እና ከፀሐይ ብርሃን የሚልቀው የክብሩ ብርሃን ይከብባቸዋል፡፡ የክርስቶስ ውበት፣ የባህሪው ፍፁምነት በእነርሱ ውስጥ ያበራል:: ይህ በእነርሱ ላይ በሚሆን ጊዜ በውጭ ከሚታይ ውበት በእጅጉ ይበልጣል፡፡ በታላቁ ነጭ ዙፋን ፊት የመላዕክትን ክብርና በረከት በመጋራት ያለነቀፋ ይሆናሉ፡፡
ከተዘጋጀልን ዘላለማዊና ባለ ታላቅ ግርማ ውርስ አንጻር ሲታይ «ሰው ስለነፍሱ ምን ዋጋ ሊከፍል ይችላል? ሰው ስለ ነፍሱ ቤዛ ምን ይሰጣል?» (ማቴ. 16:26)፡፡ አንድ ሰው እጅግ ድሃ ቢሆንም ዓለም ፈፅሞ ሊያገኘው የማይችል ሃብትና ክብር ሊኖረው ይችላል:: ከኃጢአት ተዋጅቶ እና ነፅቶ በሙሉ ኃይሉ ሕይወቱን ለእግዚአብሔር አገልግሎት የሰጠ ሰው በእግዚአብሔር ዓይን ታላቅ ዋጋ አለው:: እንደዚሁም አንዲት ነፍስ በተዋጀች ጊዜ በላይ በሰማይ በእግዚአብሔር ማደሪያ እና በመላዕክት ዘንድ በቅዱስ የድል ዝማሬ የሚገለጽ ታላቅ ደስታ ይሆናል፡፡ ወደ ክርስቶስ የሚመራ መንገድ 122.1
አባት ሆይ፣ ሊገለጥልን ያለው ክብር ከዘመኑ ስቃይ ጋር ሲነጻጸር ምንም እንዳይደለ በማሰብ ወደዚያ ክብር «እንኳን ደህና መጣችሁ!» ከምትላቸው መካከል እንድሆን እስከመጨረሻ በእምነት የጸናን እንድንሆን በጸጋህ እርዳን። አሜን።
272 views04:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 07:17:53
241 views04:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 08:30:06 ምዕራፍ 13 - በጌታ መደሰት
ክፍል ዘጠኝ
በዚህ ዓለምም ቢሆን ክርስቲያኖች ከክርስቶስ ጋር ባላቸው ህብረት ደስታ አላቸው:: የፍቅሩ ብርሃን በውስጣቸው ደስታን ይሰጣቸዋል፡፡ የእርሱ አብሮነት የማይቋረጥ መፅናናት ይሰጣቸዋል፡፡ ወደ ኢየሱስ የሚያቀርበን እያንዳንዱ የሕይወት እርምጃ የእርሱን ፍቅር በጥልቅ እንድንለማመድ እና ወደተባረከው የሰላም ቤት አንድ ደረጃ እንድንቀርብ ያደርገናል፡፡ ስለዚህ መተማመናችንን አንጣ ይልቁንም አብልጠን ዋስትናችንን ከበፊት ይልቅ እናፅና፡፡ «እስከአሁን ድረስ ጌታ እረድቶናል» እርሱ እስከፍፃሜም ይረዳናል (1ኛ ሣሙ. 7:12)፡፡ ከአጥፊው እጅ ሊያድነንና ሊያፅናናን ጌታ ለእኛ ያደረገልንን አስደናቂ ነገሮች ጌታ የሚያሳስቡንን ታላላቅ የመታሰቢያ ሃውልቶቻችንንና ማስታወሻዎቻችንን ድረስ እንይ፡፡ እግዚአብሔር ለእኛ ያሳየውን ርህራሄ፣ ያፈሰሰልንን እንባ፣የፈወሰንን ቁስል፣ የወሰደልንን ሀዘን፣ ያስወገደልንን ፍርሃት፣ የሞላልንን ፍላጎት፣ ያበዛልንን በረከት፣ ሁልጊዜ በየዕለቱ እናስብ፡፡ ይህንን ማሰብ በሚቀረን መንፈሳዊ ጉዙአችን ሁሉ ለጥንካሬያችን ይረዳናል፡፡ ክየመ 120.3
ከፊት ለፊታችን ባለን የሕይወት ዘመን ውስጥ የሚገጥመንን ውጣ ውረድ ከማሰብ ይልቅ ያለፈውንና መጪውንም እያሰብን «እስከአሁን ድረስ ጌታ እረድቶናል» «እንደ እድሜህ እንዲሁ ጥንካሬህ ይሆናል» በማለት እናውጅ (ዘዳ. 33:25)፡፡ የሚገጥሙን ፈተናዎች እነርሱን ልንቋቋምበት ከሚሰጠን ጥንካሬ አይበልጡም:: ምንም ቢመጣ ከዚያ ተግዳሮት የበለጠ ጥንካሬ እንደሚሰጠን በማመን የተሰጠንን ስራ ባገኘንበት ሁሉ ለመስራት እንትጋ፡፡
ወደ ክርስቶስ የሚመራ መንገድ 120
አባት ሆይ፣ እስከዚህ ያደረስከን አንተ እሰከ አለም ፍጻሜ ላትተወን የገባህልንን ቃል በማሰብ በፍርሃት ሳይሆን በእምነት እንድንኖር በጸጋህ እርዳን።
283 views05:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 08:29:53
250 views05:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-06 07:36:27 ምዕራፍ 13 - በጌታ መደሰት

ክፍል ስምንት

ክርስቶስ ለደቀመዛሙርቱ የሰማይ አባት ለሰው ልጆች ያለውን ፍቅር ለማሳየት ለአበቦች በቀላሉ እንዲያምሩ የሰጣቸውንውበት እና ብልፅግና በማመላከት ወደ አበባዎች ጠቁሟቸዋል፡፡ እርሱ «የሜዳ አበቦችን እንዴት እንደሚያድጉተመልከቱ» ብሏል:: የእነዚህ አበቦች የተፈጥሮ ጸጋና አንጸባራቂ የሆነ ውበት ሰለሞን በዛ ሁሉ ሀብቱ እንኳንእንደእነርሱ ሊለብስ እና ሊዋብ አልቻለም:: እጅግ በጣም ውብ የሆነ በእጅ ጥበብ ክህሎት የተሰራ ሥዕልየእግዚአብሔር ፍጥረት የሆኑ አበቦችን ውበት ሊያገኝ አይችልም፡፡ኢየሱስ «እናንተ እምነት የጎደላችሁ እግዚአብሔርዛሬ ታይቶ ነገ በእሳት የሚጠፋን ሳር እንዲህ ካለበሰ እናንተን የበለጠ እንዴት አያለብሳችሁም?» (ማቴ. 6:28 ና 30)፡፡መለኮታዊ ጥበብ የተሞላው እግዚአብሔር ታይተው ለሚጠፉ አበቦች እንዲህ የሚያሳሳ እና የተለያዩ ቀለማት ሰጥቶእንዲያምሩ ካደረጋቸው በእርሱ አምሳል ለተፈጠሩ እንዴት የበለጠ ክብካቤ አያደርግላቸውም? እንዲህ ዓይነቱንየክርስቶስ ትምህርት የማያምን ልብ ያላቸውን፣ በተዘበራረቀ ሃሳብ እና በጥርጣሬ የተሞሉትን ክርስቶስ ይገስጻቸዋል፡፡

ጌታ ሴቶችና ወንዶች ልጆቹን ደስተኛ፣ ሰላም የሞላቸው እና ታዛዥ እንዲሆኑለት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ ኢየሱስ እንዲህአለ፡- «ሰላምን እተውላችኋለሁ፣ ሰላሜን እሰጣችኋለሁ እኔ የምሰጣችሁ ዓለም እንደሚሰጥ አይደለም፡፡» «ደስታዬበእናንተ እንዲሆን ደስታችሁም እንዲፈፀም ይህን ነግሬአችኋለሁ» ዮሐ 14:27 ና 15:11)፡፡

ከራስ ወዳድነት ስሜትና ኃላፊነት የጎደለው ጎዳና የሚገኝ ደስታ ሚዛናዊነት የጎደለው፣ አጥፊ እና አላፊ ነው፡፡ ይህ ደስታባለፈ ጊዜ ነፍስ በብቸኝነትና በሀዘን ትሞላለች:: እግዚአብሔርን በማገልገል ግን ደስታና እርካታ አለ፡፡ ክርስቲያኖችባልተረጋገጠ መንገድ እንዲጓዙ አልተተውም፤ ለፀፀትና ለተስፋ መቁረጥ አልተተውም፡፡ አሁን ባለው ሕይወት ደስተኞችባንሆን እንኳን ከዚህ ባሻገር በሚኖረው ሕይወት ደስታ እናገኛለን፡፡ ክየመ 120.2



አባት ሆይ፣ አንተ ለእኛ ያለህን ፍቅር በመረዳት ባንተ ሰላም የተረጋጋ ህይወት ስጠን። አሜን።
298 views04:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-06 07:36:12
256 views04:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ