Get Mystery Box with random crypto!

የህይወት ቃል / Word of life

የቴሌግራም ቻናል አርማ dailywordoflife — የህይወት ቃል / Word of life
የቴሌግራም ቻናል አርማ dailywordoflife — የህይወት ቃል / Word of life
የሰርጥ አድራሻ: @dailywordoflife
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.80K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የቴሌግራም ቻናል በየእለቱ ህይወት ከሆነው ከእግዚአብሔር ቃል አጠር ያለ መልእክት የሚቀርብበት ነው። ይህንን ቻናል በመቀላቀልና አብረን ይህንን የህይወት ቃል እንድንመረምር እናድማችኋለን። ጥያቄ ወይም አስተያየት ቢኖራችሁ በዚህ አድራሻ ጻፉልን። @melakalex ወይም 254724416340

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2022-08-23 07:00:54 አስተውይ
እርሱ አይለወጥም
እንዳስቀመጥነው እናገኘዋለን፣ እንደጠብቅነውም ይሆናል ያልነው ነገራችን ሲለዋወጥብን፣ ተስፋ ያደረግናቸው ሰዎች ፊታቸው ሲጠቁርብን፣ የምናደርገው ነገር ጠፍቶን ግራ ሲገባን፣ ከስፍራው ወደማይታጣው እግዚአብሔር እንመልከት። “ በእርሱ ዘንድ መለዋወጥ ከመዞር የተነሣ የሚያርፍ ጥላም የለም። ” ያእ 1:16
በማይዋሸው ቃሉ “እኔ እግዚአብሔር አልለወጥም” ካለን በኋላ እኛም ያልጠፋነው ከዚህ የተነሳ እንደሆነ ይነግረናል።
ሁኔታዎች ሲለዋወጡ በማይለዋወጠው አምላክ ላይ ብንደገፍ አንጠፋም።
ዮሴፍ ካየው ህልም በተቃራኒ ነገሮች በህይወቱ ሲቀያየሩ፣ ባልጠበቀው ጊዜና ሁኔታ ራሱን ከአባቱ ቤት ወደ ባርነት ቤት፣ ከዚያም ወደ እስር ቤት ሲገባ ቢያገኘውም፣ ከሁኔታዎች ጋር የማይለዋወጠው እግዚአብሔር ግን ከእርሱ ጋር ስለነበረ አልጠፋም። ይልቁንም ቁልቁል የሚመስለውን ጉዞ እግዚአብሔር ወደ ህልሙ መፈጸሚያ የሚወጣጣበት መሰላል አደረገለት። እኛም ዛሬ ነገሮቻችን እየተክፋፉ ቢሄዱ ከእኛ ጋር ባለው “እኔ አልለወጥም” ባለን ጌታ ላይ እምነታችንን እናድርግ።
የሰዎች ፊት ሲለዋወጥ በማይለዋወጠው አምላክ ላይ ብንደገፍ አንጠፋም።
ዮሴፍ የገዛ ወድሞቹ ፊት ሲለዋወጥበት፣ በፍቅር ሰላም ይሉኛል ብሎ ሲጠብቅ በቁጣና በንዴት ሲገፈታትሩት፣ አልፎም ወደ ጉድጓድ ሲጥሉት ምን ተሰምቶት ሊሆን እንደሚችል መገመት አይከብድም። “እኔ አልለወጥም” ያለው እግዚአብሔር ግን ከእርሱ ጋር ስለነበረ፣ አልጠፋም። እንዲያውም እንደዚያ ፊታቸውን ያዞሩበት ወንድሞቹ፣ ጊዜ ተለውጦ በእርሱ እጅ ወደቁ።
እኛም ተስፋ ያደረግናቸው ሰዎች ጀርባቸውን ሰጥተውን ቢሆን፣ “እኔ እግዚአብሔር አልለወጥም” ወዳለን ጌታ ፊታችንን እንመልስ።
ሁኔታዎችና ሰዎች ብቻ ሳይሆኑ እኛም ራሳችን የምንለዋወጥበትና በተለይም ከእግዚአብሔር ጋር ባለን ግንኙነት ለእርሱ ጀርባችንን ሰጥተን በራሳችን ከንቱ የጥፋት መንገድ እየኮበለልን ሊሆን ይችላል። እንዲህም ባለ ሁኔታ ውስጥ ብንሆን እግዚአብሔር ግን አይለወጥም።
ከአባቱ ቤት ድርሻውን ወስዶ የጠፋው ልጅ በሄደበት አጥፊ መንገድ ለአጉል ኪሳራና ውድቀት በተዳረገ ጊዜ፣ “ወደ አባቴ ቤት ልመለስና የእርሱ ባሪያ ልሁን” አለ። የሚገርመው ታዲያ ወደ አባቱ ቤት ሲመለስ፣ አባቱ በስፍራው ነበር። ፍቅሩ አልተለወጠም። ገና ከሩቅ ሲያየው ሮጦ ሄዶ አቀፈው፣ ሳመው። ወደ ቀድሞ ክብሩም መለሰው። በእርግጥም ያልጠፋው ከማይለወጠው ከአባቱ ፍቅር የተነሳ ነበር። ጌታችን ይህንን ምሳሌ የነገረን እኛም እንደዚያ ልጅ በእግዚአብሔር ላይ ፊታችንን አዙረን ብንሄድ የማይለወጠውን የእርሱን ፍቅር አስበን በንስሃ እንድመለስ ነው።
ከእርሱ ርቀን ቢሆን፣ ዛሬ ወደ እርሱ እንመለስ፣ እርሱንም በስፍራው ላይ እናገኘዋለን። አልተለወጠም፣ አይለወጥምም!
አባት ሆይ፣ በእርግጥም ያልጠፋነው አንተ የማትለዋወጥ አስተማማኝ አምላክ ስለሆንክ ፣ ምህረትህም ለዘላለም ስለሆነ እንደሆነ አስተውለን አሁንም እምነታችን ባንተና ባንተ ብቻ እንዲሆን እርዳን። አሜን።
350 views04:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-23 07:00:40
294 views04:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-14 06:54:02 ለእግዚአብሔ የሚሳነው የለም
የዘጠና አመት መካን ሴትን ልጅ ማሳቀፍ ይቻለዋል፡ የሚሳነው የለምና!
ባሕርን ከፍሎ፣ በባህሩ ወለል ላይ ያለውን መሬት አድርቆ፣ በደረቅ ማሻገር ይቻለዋል፤ የሚሳነው የለምና!
በምድረበዳ ከአለት ውስጥ ውሃ ማፍለቅ ይቻለዋል፤ የሚሳነው የለምና!
በአንበሳ ጉድጓድ ውስጥ የተጣለው፣ የአንበሳውን አፍ ዘግቶ ማዳን ይቻለዋል፤ የሚሳነው የለምና!
ሰባት እጥፍ በነደደ እቶን ውስጥ የተጣሉትን፣ የእሳቱን ሃይል አጥፍቶ፣ ጭስ ጭስ እንኩዋን ሳይሸቱ ማትረፍ ይቻለዋል፤ የሚሳነው የለም!
በሚናወጠው ወጀብ ላይ እየተራመደ፣ ሞገዱን ደግሞ በቃሉ ጸጥ ማድረግ ይቻለዋል፤ የሚሳነው የለምና!
ከሞተ ሶስት ቀን የሆነውን ሬሳ ከመቃብር አውጥቶ በህይወት ማኖር ይቻለዋል፤ የሚሳነው የለምና!
አርሱ ውሆችን በዕፍኙ የሰፈረ፣ ሰማያትን በስንዝሩ የለካ፣ የምድርን ዐፈር በመስፈሪያ ሰብስቦ የያዘ፣ ተራሮችን በሚዛን፣ ኰረብቶችንም በመድሎት የመዘነ ታላቅ አምላክ ነው።
እርሱ ከምድር ክበብ በላይ በዙፋን ላይ ይቀመጣል፤
ሕዝቦቿም እንደ አንበጣ ናቸው።
ሰማያትን እንደ ድባብ ይዘረጋቸዋል፤
እንደ መኖሪያ ድንኳንም ይተክላቸዋል።
የከዋክብትን ሰራዊት አንድ በአንድ የሚያወጣቸው፣ በየስማቸው የሚጠራቸው እርሱ ነው።
ከኀይሉ ታላቅነትና ከችሎታው ብርታት የተነሣ፣ አንዳቸውም አይጠፉም።
እግዚአብሔር የዘላለም አምላክ፣ የምድር ዳርቻ ፈጣሪ ነው።
አይደክምም፤ አይታክትም፤ ማስተዋሉም በማንም አይመረመርም። ለደከመው ብርታት ይሰጣል፤ ለዛለው ጒልበት ይጨምራል።
ኢሳ 40
አባት ሆይ፣ በእርግጥም ሁሉ የሚቻልህ ታላቅ አምላክ መሆንህን በማስተዋል፣ ባንተ ላይ ሙሉ በሙሉ መደገፍና ማረፍ እንድንችል በጸጋህ እርዳን። አሜን።
173 views03:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-14 06:53:51
157 views03:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 07:16:33 ያውቅሃል
ምናልባት ለወላጆቻችን ሳንታሰብ የተጸነስ አጋጣሚ ተደርገን እንቆጠር ይሆናል። ነገር ግን ገና በሆድ ውስጥ ሳይሰራን የሚያውቀን፣ በእርሱ ዘንድ አጋጣሚ የሚባል ነገር የሌለ አምላክ እንዳንለ እናስተውል። እርሱ የራስ ጠጉራችንን በቁጥር የሚያውቅ፣ የእኛ ነገር ከእኛ በላይ ግድ የሚለው አምላክ ነው።
የመኖር ትርጉሙ ሲጠፋን፣ የሕይወታችንን አላማ በግልጽ መረዳት ሲያቅተን፣ ገና ሳንጸንስ እርሱ ግን በአእምሮው ውስጥ ወደ አስቀመጠን፣ ከዚያም በአላማ ወደፈጠረን አምላክ እንቅረብ። እርሱም ጣእም ያጣውን ህይወታችንን ያጣፍጠዋል።
አባት ሆይ፣ ገና በማህጸን ሳትሰራን የምታውቀን፣ ለሕይወታችን ባለህ አላማ የተመራ ኑሮ እንድንኖር እርዳን።
228 views04:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 07:16:27
205 views04:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-12 07:14:54 ብቻችንን አይደለንም
ጌታችን ኢየሱስ “ኑ፣ ተከተሉኝ” ብሎ ሲጠራን መንገዳችን አልጋ ባልጋ እንደሚሆን የሃሰት ተስፋ አልሰጠንም። ይልቁንም “በአለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ” በማለት በግልጽ ነግሮናል። ይሁን እንጂ (1) ወላጅ እንደሌላቸው ሰዎች እንደማይተውን፣ (2)እስከ አለም ፍጻሜ ከእኛ ጋር እንደሚሆንና ደግሞም (3)ተመልሶ መጥቶ እንሚወስደን አስተማማኝ የሆነን ተስፋ ሰጥቶናል።
የጌታችን ደቀ መዛሙርት ይህንን ተስፋ በማመናቸው በገጠማቸው ብዙ ችግር ተስፋ ሳይቆርጡ፣ በድፍረት የተሰጣቸውን ተል እኮ ፈጸሙ።
ጴጥሮስ በእስር ቤት ውስጥ የሞት አደጋ በፊቱ ተጋርጦ በነበረበት ጊዜ እንቅልፉን የለጠጠው፣ በእርግጥም ጌታ ከእርሱ ጋር እንደነበረ በማስተዋሉ ነበር።
ጳውሎስም በእስር ቤት ከብዙ ድብደባና እንግልት በሁዋላ በእኩለ ሌሊት በዝማሬ የተሞላ፣ የደስታው ምንጭ አብሮት ያለው ጌታ ስለነበረ ነው።
እኛም በምንም አይነት ሁኔታ ውስጥ ብንሆን እንዲህ የሚል ተስፋ በሰጠን ጌታ ላይ እንታመን።
ምክንያቱም እግዚአብሔር፣ “ከቶ አልተውህም፤
በፍጹም አልጥልህም” ብሎአል። እብ 13:5
አባት ሆይ፣ አንተ እንዲህ ያለውን የታመነ ተስፋ ስለሰጠከን፣ እኛ ደግሞ በሙሉ ልብ፣
““ጌታ ረዳቴ ነው፤ አልፈራም፤ ሰው ምን ሊያደርገኝ ይችላል?” ማለት እንድንችል እርንዳ። አሜን።
237 views04:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-12 07:14:48
216 views04:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-11 06:58:33 ተከበሃል
መቼም “ተከበሃል” የሚለውን መረጃ ስናገኝ፣ የመጀመሪያው ጥያቄችያን የሚሆነው “በማን?” የሚል ነው። የከበበን ጠላት፣ ዘራፊና አጥፊ ከሆነ ዜናው ያሸብረናል። ነገር ግን የከበበን እኛን የሚረዳ፣ የሚጠብቀንና የሚታደገን ከሆነ ደግሞ ልባችንን ያረጋጋዋል።
በ2ኛ ነገስት ምእራፍ ስድስት ከቁጥር 15-17 ላይ ስለ ከበባ አንድ አስደናቂ ታሪክ ተጽፎአል ፦
“የእግዚአብሔር ሰው (የኤልሳእ) አገልጋይ በማለዳ ተነሥቶ ወደ ውጭ ሲወጣ፣ በፈረሶችና በሠረገሎች የተጠናከረ ሰራዊት ከተማዪቱን ከቧት ነበር። አገልጋዩም “ጌታዬ ሆይ፤ ምን ማድረግ ይሻለናል?” ሲል ጠየቀ።
ነቢዩም፣ “ከእኛ ጋር ያሉት ከእነርሱ ጋር ካሉት ይበልጣሉና አትፍራ” አለው።
ኤልሳዕም፣ “እግዚአብሔር ሆይ፤ ያይ ዘንድ እባክህ ዐይኖቹን ክፈትለት” ብሎ ጸለየ፤ እግዚአብሔርም የአገልጋዩን ዐይኖች ከፈተለት፤ ሲመለከትም፤ የእሳት ፈረሶችና ሠረገሎች በኤልሳዕ ዙሪያ ተራራውን ሞልተውት አየ።”
ምንም እንኩዋን ነብዩና አገልጋዩ ሊጠፏቸው በመጡ በጠላት ጦር አባላት ቢከበቡም፣ ከእነርሱ በሚበልጥ ሰማያዊ ሰራዊት መከበባቸው ደግሞ ፍርሃትን በእምነት እንዲያሸንፉ አቅም ሆናቸው።
እኛም ዛሬ በምንም አይነት ሁኔታ ውስጥ ብንሆን፣ ዙሪያችንን የከበበን ከእኛ ጋር ያለው እግዚአብሔርን በማየት በእምነት እንኑር።
አባት ሆይ፣ በከበብከን ባንተ ከማኛውም የጠላት ከበባ ተጠብቀን መኖር እንደምንችል የሚያምን ልብ ስጠን።አሜን።
268 views03:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-11 06:58:27
243 views03:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ