Get Mystery Box with random crypto!

የህይወት ቃል / Word of life

የቴሌግራም ቻናል አርማ dailywordoflife — የህይወት ቃል / Word of life
የቴሌግራም ቻናል አርማ dailywordoflife — የህይወት ቃል / Word of life
የሰርጥ አድራሻ: @dailywordoflife
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.80K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የቴሌግራም ቻናል በየእለቱ ህይወት ከሆነው ከእግዚአብሔር ቃል አጠር ያለ መልእክት የሚቀርብበት ነው። ይህንን ቻናል በመቀላቀልና አብረን ይህንን የህይወት ቃል እንድንመረምር እናድማችኋለን። ጥያቄ ወይም አስተያየት ቢኖራችሁ በዚህ አድራሻ ጻፉልን። @melakalex ወይም 254724416340

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-08-28 22:10:08 እርሱ የሚባላ እሳት ነው
“እግዚአብሔር ፍቅር ነው” የሚለውንና “እርሱ የሚባላ እሳት ነው” ተብሎ የተጻፈውን ጎን ለጎን ስናነብ “እንዴት እነዚህን ሁለቱን በአንድ ጊዜ ሊሆን ይችላል? እግዚአብሔር ፍቅር ከሆነ እንዴት የሚባላ እሳት ሊሆን ይችላል?” የሚል ጥያቄ ሊያጭርብን ይችላል።
ለዚህ ጥያቄ መልስ ለማግኘት የእግዚአብሔርን ማንነት የሚገልጸውን ፍቅር በደንብ መረዳት ያስፈልገናል። በ1 ቆሮ 13 ቁጥር 6 ላይ ስለ እውነተኛው የእግዚአብሔር ፍቅር ሲናገር እንዲህ ይላል ፦
“ፍቅር ከእውነት ጋር እንጂ በዐመፅ ደስ አይሰኝም። ”
እውነተኛ ፍቅር በዐመፅ፣ በክፋት፣ በርኩሰት ደስ አይሰኝም። ምክንያቱም ይህ የክፋት ጎዳና የጥፋት ጎዳና ስለሆነ አፍቃሪ የሆነው አምላክ ክፋትን ይጠላል። እናም ክፋት የእርሱ የሆኑትን እንዳያጠፋበት እርሱ ክፋትን የሚያጠፋ እሳት ነው።
አለማችንን በብዙ ስቃይና ሰቆቃ የሞላት የክፋት መንሰራፋት ነው። አምላካችን እግዚአብሔር ይህንን የጥፋት ሁሉ ስር ሆነውን ክፋት በእሳት የሚያጠፋበትና አዲስ ሰማይና ምድርን የሚፈጥርበት ጊዜ እንደሚመጣ ቃሉ ያስተምረናል። ያን ጊዜ እንባ ከአይን ይታበሳል። ደስታና ሰላም የሞላበትን የእረፍት ህይወት መኖር እንጀምራለን።
ክፋትን የሚበላው የእግዚአብሔር እሳት ምድራችንን ከማጥራቱ በፊት ግን እኛም ከክፋት ጋር ተጣብቀን አብረን እንዳንጠፋ ዛሬ ወደ እርሱ በንስሓ እንድንመጣ ጌታ ይጠራናል።
አባት ሆይ፣ አንተ በእርግጥም ክፋትን የምታጠፋ እሳት መሆንህን አስተውለን፣ በፍቅርህ ተማርከን ከክፋት የራቀ ህይወት መኖር እንድንችል በጸጋህ እርዳን። አሜን።
273 views19:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 07:12:40
305 views04:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 07:36:31 እርሱ አይዘበትበትም
እግዚአብሔር አምላክ ለሙሴ ማንነቱን በገለጠለት ጊዜ እንዲህ በማለት ነበር ራሱን ያስተዋወቀው፦
““እግዚአብሔር ሩኅሩኅ ቸር አምላክ እግዚአብሔር ለቍጣ የዘገየ፣ ፍቅሩና ታማኝነቱ የበዛ፣ ፍቅርን ለሺዎች የሚጠብቅ፣ ክፋትን፣ ዐመፅንና ኀጢአትን ይቅር የሚል በደለኛውን ግን ሳይቀጣ ዝም ብሎ አይተውም፤ ” ዘጸ 34:6,7
በእርግጥም እግዚአብሔር ፍቅሩና ታማኝነቱ የበዛ፣ ዐመፅንና ኀጢአትን ይቅር የሚል አምላክ እንደሆነው ሁሉ “በደለኛውን ግን ሳይቀጣ ዝም ብሎ” የማይተው አምላክም ነው። በሌላ አነጋገር ለኀጢአቱ ይቅርታን ለመቀበል በንስሓ ወደ እርሱ ለመመለስ የማይፈቅደውን፣ በክፋት ጎዳና ለመገስገስ የወደደውን ነፍስ ለመረጠው ጥፋት አሳልፎ ይሰጠዋል።
ክፋትን የዘራ ጥፋትን ያጭዳል።
በተለይ ደግሞ በእግዚአብሔር ምህረት እየቀለድን የክፋትን ህይወት ኖረን “መጨረሻ ንስሓ ገብቼ ፍጻሜዬን አሳምራለሁ” ብለን ካሰብን ራሳችንን እናታልላለን። ቃሉ እንደሚለው እግዚአብሔር አይዘበትበትም። እርሱ በንጽሁ ፍቅር የወደደን፣ እኛም በሙሉ ልባችንን እንድንወደው የሚሻ አባት እንጂ ቅጣትን ፈርተን ብቻ ለእርሱ እንድንገዛ የሚፈልግ አይደለም።
አባት ሆይ፣ ክፋትን በመዝራት የጥፋት ፍሬ እንዳንለቅም፣ በሙሉ ልባችን አንተን በመውደድ በመንፈስ ቅስዱ ኀይል የጽድቅን ህይወት መለማመድ እንድንችል እርዳን። አሜን።
321 views04:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 07:36:23
278 views04:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 07:44:07 አስተውል
እርሱ የወደቁትን ያነሳል
ሽንፈት ውድቀት ሳይሆን ወድቆ መቅረት እንደሆነ ተደጋግሞ ሲነገር ሰምንተን ይሆናል። ነገር ግን መፍትሄ የሚያሻው ትልቁ ጥያቄ፣ "ታዲያ ከወደቅሁበት የምነሳው እንዼት ነው?" የሚለው ነው። መልሱም እነሆ!
የወደቁትን የሚያነሳ፣ ለመውደቅ ስንገዳገድ ደግሞ ደግፎ የሚይዘን አፍቃሪ አባት በሰማይ አለን። እርሱም እውነተኛ አምላክ የሆነው፣ እግዚአብሔር አምላካችን ነው። ስሙ የተመሰገነ ይሁን።
እርሱ የተቀጠቀጠውን ሸንበቆ የማይሰብር፣ የሚጤሰውን የጧፍ ክር የማያጠፋ፣ ይልቁንም ሰባራውን የሚጠግን፣ ተስፋ ለተቆረጠበት አዲስ ሕይወትን የሚሰጥ ድንቅ አምላክ ነው።
ጠልፈው በሚጥሉና በወደቅንም ጊዜ መልሰን እንዳንነሳ በሚረጋግጡን ብዙ ሁኔታዎች ውስጥ ተከበን ቢሆን፣ ቀና ብለን ይህንን አምላክ እንይ።
ንጉስ ናቡከደነጾር በት እቢቱ ምክንያት ከታላቅ ስልጣኑ ወርዶ ለሰባት አመት እንደ ከብት በዱር ሳር ከበላበት ከቆየበት እንደገና ወደዙፋኑ የተመለሰው ዐይኖቹን ወደ ሰማይ ባነሳ ጊዜ ነበር። "እኔ ናቡከደነፆር ዐይኖቼን ወደ ሰማይ አነሣሁ፤ አእምሮዬም ተመለሰልኝ፤ ልዑሉንም ባረክሁት፤"
"እግዚአብሔር የሚንገዳገዱትን ይደግፋል፤ የወደቁትንም ያነሳል።"
አባት ሆይ፣ ዛሬ ከወደቅንበት እንድታነሳን፣ ስንገዳገድ ደግፈህ እንድትይዘን፣ ባንተ መከናወን እንዲሆንልን እርዳን። አሜን።
323 views04:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 07:43:56
286 views04:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 07:50:01 እርሱ የዘላለም ዐምባ፣ ጽኑ ዐለታችን ነው
በመጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔር ተመስሎ ከቀረበባቸው ተምሳሌታዊ መግለጫዎች መካከል "ዐለት" አንዱ ነው። እግዚአብሔር ዐለትነት ከሚሰጠን በረከቶች መካከል ጥቂቶችን ቀጥለን እንይ:-
1 ጥላ የሚሆነን ዐለታችን
በተለይ በምድረ በዳ ውስጥ የሚገኙ ትልልቅ ዐለቶች በሃሩር ንዳድ ለተቃጠለው ሰው ጥላን የሚሰጡ ናቸው። በኢሳ 32:2 ላይ “ በተጠማም ምድር እንደ ትልቅ ቋጥኝ ጥላ ይሆናል።” በማለት የዐለትን ጥላ የመስጠት ጥቅም ይናገራል። ታዲያ እግዚአብሔርን ዐለቴ የምንለው እንደ ምድረበዳ በሆነችው በዚህች አለም ስንጓዝ ሳለ ጥላ ስለሚሆነን ነው።
2 ውሃ የሚያፈልቅልን ዐለታችን
ዐለታችን እግዚአብሔር እስራኤላዊያን በምድረ በዳ ሲጓዙ የውሃ ምንጭ ሆኖላቸው እንደነበረም እንዲህ ተብሎ ተጽፎአል:-
“ ሁሉም ከአንድ መንፈሳዊ መጠጥ ጠጡ፤ ይከተላቸው ከነበረው መንፈሳዊ ዐለት ጠጥተዋልና፤ ያ ዐለት ክርስቶስ ነበረ።” 1 ቆሮ 10:4 ዛሬም ቢሆን መንፈሳዊ ጥማችንን ሊቆርጥልን የህይወትን ውሃ ሊያጠጣን ዐለታችን ክርስቶስ “ማንም የተጠማ ቢኖር ወደ እኔ ይምጣና ይጠጣ” በማለት ይጋብዘናል።
3 መሸሸጊያ አለታችን
ዳዊት በንጉስ ሳኦል እየታደነ ህይወቱን ለማትረፍ ሸሽቶ ወደ ምድረ በዳ ሲገባ በተለያዩ ዐለቶች ውስጥ ተሸሽጎ ነበር። ታዲያ መሸሸጊያ ሆነውለት የነበሩት እነዚያ ዐለቶች ዋናውን ዐለቱን አስታውሰውት እንዲህ አለ።
“ እግዚአብሔር ዐለቴ፣ መጠጊያዬና ታዳጊዬ ነው፤
አምላኬ የምሸሸግበት ዐለቴ፤
እርሱ ጋሻዬ፣ የድነቴ ቀንድና ዐምባዬ ነው።” መዝ 18:2
ዛሬም ቢሆን ዐለታችን እግዚአብሔር በብዙ ሽብርና ስጋት እየተናጠች ባላችው አለማችን ውስጥ ስንኖር የምንሸሸግበት ዐለታችን ነው።
ይህንን እውነት በመረዳት እኛም ከመዝሙረኛው ጋር እንዲህ ልንል ይገባል:-
“ ነፍሴ ሆይ፤ ዐርፈሽ እግዚአብሔርን ብቻ ጠብቂ፤
ተስፋዬ ከእርሱ ዘንድ ነውና።
ዐለቴና መድኀኒቴ እርሱ ብቻ ነው፤
መጠጊያዬም እርሱ ነው፤ እኔም አልናወጥም።
መዳኔና ክብሬ በእግዚአብሔር ነው፤
ብርቱ ዐለቴና መሸሸጊያዬ በእግዚአብሔር ነው።
ሰዎች ሆይ፤ ሁል ጊዜ በእርሱ ታመኑ፤
ልባችሁን በፊቱ አፍስሱ፤
እግዚአብሔር መጠጊያችን ነውና።” መዝ 62:5-8
አባት ሆይ፣ አንተ ጥላ የምትሆንን፣ ጥማችንን የምታረካ፣ ደግሞም የምንሸሸግብህ አለታችን ስለሆንክ እናመሰግንሃለን። ሁልጊዜ በአንተ በመታመን ልባችንን በፊትህ እንድናፈስ እርዳን። አሜን።
318 views04:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 07:49:57
263 views04:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 07:46:06 እርሱ መሪያችን ነው
አምላካችን ራሱ በሰጠን የተስፋ ቃል “አስተምርሃለሁ፣ በምትሄድበትም መንገድ እመራሃለሁ፡ አይኖቼን በአንተ ላይ አጠናለሁ” ይለናል።
በአለማችን ከምናየው የእውቀት ፍንዳታና የመረጃ ጎርፍ ጋራ ተያይዞ ትክክለኛውን ትምህርትና ምሪት ማግኘት እጅግ አዳጋች እየሆነ መጥቶአል። እውነት አንጻራዊ ሆኖ፣ ጥርጣሬና ግራ መጋባት የምርምር መደምደሚያ ሲሆኑ ስናይ፣ በእርግጥም ሁሉን በሚያውቀው አምላክ መመራት እጅግ የከበረ እድል ነው። የእርሱ እውቀት የማይመረመር ጥልቅ ሲሆን የመጀመሪያውን ከመጨረሻው ማየት የሚችል አምላክ ስለሆነ ከእርሱ የምናገኘው ትምህርት ዘላለማዊ ዋጋ ያለው የከበረ እንቁ ነው።
ታዲያ ይህ አምላካችን በክፍል ውስጥ መጥቶ መረጃን አካፍሎ እንደሚሄድ አስተማሪ ሳይሆን፣ ደግሞ ባስተማረን በዚያ ህይወታችን መመራት ይችል ዘንድ በምንሄድበት መንገድ የሚመራንም መልካም እረኛ ነው። ከፊታችን ቀድሞ የሚወጣ፣ በመልካም አርአያነት ዱካውን ከፊታችን በማስቀመጥ ጎዳናችንን የሚያቀና ታማኝ መሪያችን ነው። እርሱን ልንከተለው ብንፈቅ “ከእኔ ተማሩ እኔ የዋህ በልቤም ትሁትን ነኝ” ሲለን እንሰማዋለን።
በመንገዳችን በሚገጥመን በማንኛውም አደናጋጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆነን አይኖቻችንን ወደ እርሱ ስናነሳ ደግሞ “አይኖቼን በአንተ ላይ አጠናለሁ” ካለው ጌታ ጋር አይን ለአይን እንገጣጠማለን። እርሱም ትክክለኛውን አቅጣጫ ይጠቁመናል። ወቅታዊና ገጣሚ የሆነ ምሪት ይሰጠናል።
“ወደ ቀኝም ሆነ ወደ ግራ ዘወር ብትል ጆሮህ ከኋላህ፣ “መንገዱ ይህ ነው፤ በእርሱ ሂድ” የሚል ድምፅ ይሰማል።” ኢሳ 30:21።
ይህንን ድንቅ የሆነ የእግዚአብሔርን ምሪት ለማግኘት ቅዱስና ህያው የሆነውን ቃሉን በመንፈስ ቅዱስ ምሪት ልናነብ ይገባናል። መጽሐፍ ቅዱስ እንደ ኮከብ ቆጣሪ (ሆሮስኮፕ) ዛሬ “ይሄ ይገጥምሃል፣ እንዲህ ትሆናለህ፣…” የሚል መረጃ የለውም፤ ነገር ግን ህይወታችን ሊመራበት የሚገባውን መለኮታዊ መርህ ያስተምረናል። መርሆዎቹን ወደ ህይወታችን ዝርዝር ጉዳዮች ለመተርጎም እንድንችል ደግሞ በጸሎት በፊቱ ስንቀርብ መንፈስ ቅዱስ ለመንፈሳችን በመመስከር ልባችን የሚያርፍበትን ውሳኔ እንድንወስን ይረዳናል።
እዚህ ላይ ልብ ልንለው የሚገባን ውሳኝ እውነታ እግዚአብሔር የሚመራን ከሆነ መንገዳችን አልጋ ባልጋ ይሆናል ማለት እንዳልሆነ ነው።
አብርሃምን ታላቅ ተስፋ አሰንቆ ከተወለደበት ምድር ሲያወጣው በመንገዱ ላይ ረሃብና ሌሎችም አስቸጋሪ ሁኔታዎች ገጥመውት ነበር።
ዮሴፍ ገና በልጅነት ያየው ህልም ከከፍታ ላይ ጉብ አድርጎት የነበረም ቢሆን ከዚያ ጫፍ ለመድረስ ግን በባርነትና በእስርቤት ሸለቆ ውስጥ ማለፍ ነበረበት።
እስራኤላውያን ከግብጽ ወጥተው ወደ ተስፋይቱ ምድር ወደ ከንአን ለመድረስ የሄዱበት መንገድ በብዙ ተግዳሮቶች የተሞላ ነበር።
ዳዊት በጎቹን ከሚጠብቅበት ሜዳ ተጠርቶ ለንጉስነት ቢቀባም በዙፋኑ ላይ ከመቀመጡ በፊት “በእኔና በሞት መካከል እንድ ስንዝር ቀረ” እስከሚል ድረስ በከባድ መከራ ውስጥ አልፎ ነበር።
የጌታችን ደቀ መዛሙርትም “መንገድ እውነትና ህይወት”የሆነው ኢየሱስን በመከተል በተጓዙት ጎዳና ብዙ መከራ ደርሶባቸዋል።
ይሁን እንጂ እነዚህና ሌሎች ብዙ ምሳሌዎችን ስንመለከት ጌታችን ልጆቹን በመንገዳቸው በሚገጥማቸው ነገር ሁሉ እየመራ የሚያሻግር፣ እርሱ ካሰበላቸውም ፍጻሜ የሚያደርስ አምላክ መሆኑን እርግጠኞች ሆነን ማመን እንችላለን።
እኛም ዛሬ የእርሱን ምሪት ፍለጋ ወደ እርሱ እንቅረብ፣ እርሱ በሚመራን መንገድ ላይ በሚያጋጥመን ማንኛውም አይነት ችግር አንደናገጥ፣ ይልቁንም አይኖቹን በእኛ ላይ ወደ አጠናው ጌታ አይኖቻችንን በማንሳት የእርሱን ምሪት እንከተል።
አባት ሆይ፣ ልጆችህን በመምራት እንደ አንተ ያለ ማንም የለምና እናመሰግንሃለን። እኛም ባንተ በመመራት መኖር እንድንችል እርዳን። አሜን
324 views04:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 07:45:50
281 views04:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ