Get Mystery Box with random crypto!

Bahir Dar University,Ethiopia

የቴሌግራም ቻናል አርማ bahir_dar_university — Bahir Dar University,Ethiopia B
የቴሌግራም ቻናል አርማ bahir_dar_university — Bahir Dar University,Ethiopia
የሰርጥ አድራሻ: @bahir_dar_university
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 18.56K
የሰርጥ መግለጫ

It is a channel about Bahir Dar University all Campuses!

www.bdu.edu.et

Ratings & Reviews

4.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 10

2022-10-24 12:04:06
ማስታወቂያ
ለሁሉም መደበኛና የማታ ተማሪዎች በሙሉ
@bahir_dar_university
@bahir_dar_university
6.6K viewsedited  09:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-15 20:47:28
10.1K views17:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-15 20:47:28
9.1K views17:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-15 20:47:27 #ጠቅላይ_ሚኒስትሩ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲን ጎበኙ

ጥቅምት 5/2015 ዓ/ም [ባዳዩ] 10ኛውን የጣና ፎረም ለመታደም ባሕር ዳር የገቡት የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከሚገኙት ግቢዎች መካከል አንጋፋውን የፔዳ ግቢ ጎብኝተዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጉብኝታቸው ዩኒቨርሲቲው የሰራቸውን ስራዎች ተዘዋውረው የተመለከቱ ሲሆን በጉብኝታቸው ከተመለከቷቸው ስራዎች መካከል በተለይም የአረንጓዴ ልማትና የግቢ ውበት ላይ በተሰሩት ስራዎች እጅግ መደሰታቸውንና የተሰራው ስራ ዩኒቨርሲቲውን የገነት ተምሳሌት ያደረገው መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማር ስራዎች ጎን ለጎን ግቢዎችን በአትክልትና ፍራፍሬ በማስዋብ ያደረገው ጥረት ለከተሞችና ለሌሎች ዩኒቨርሲቲዎችም አርአያ የሚያደርገው መሆኑን በመግለጽ ተምሳሌትነቱን አጠናክሮ እንዲቀጥል መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ፍሬው ተገኘ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ለተመራው ልዑክ ስለ ዩኒቨርሲቲው የስራ እንቅስቃሴ በተለይም በቅርብ ጊዜ ዩኒቨርሲቲው የሰራቸውን የአርንጓዴ ልማትና የግቢ ውበት ስራዎችን በተመለከተ ገለጻ አድርገዋል፡፡
በጉብኝቱም የኢፌዲሪ ም/ጠ/ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን፤ የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ/ር) እና ሌሎች የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ ባለስልጣናት እንዲሁም የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል፡፡

https://t.me/bahir_dar_university
8.0K viewsedited  17:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-14 19:05:27
#TANA_FORUM pre - conference event commences today in the afternoon at Wisdom Hall, Bahir Dar University, Bahir Dar, Ethiopia.
Welcoming all to this big event, we would like to wish you a pleasant and fruitful stay in the beautiful city of Bahir Dar.

https://t.me/bahir_dar_university
7.1K viewsedited  16:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-09 20:42:07
1.2K views17:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-09 20:40:36 ነገ መስከረም 30/2014ዓ/ም ከሚጀመረው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና አስፈፃሚዎች ጋር ምክክር ተደረገ

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከተመደቡ የሁለተኛ ደረጃ ት/ት ማጠናቀቂያ ፈተና አስፈጻሚዎች ጋር በጥበብ አዳራሽ በበይነ መረም የታገዘ ገለፃ ተደረገ።

በመክፈቻውም የበይነ መረብ ቴክኖሎጅን በመጠቀም የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ በሄድንባቸው ጉዞዎች ሁሉ ፈተናዎች ታልፈው ብዙ የልማት ስኬቶች እንደተመዘገቡ ጠቁመው በዚያው ልክ በትምህርት ጥራት ያልተስተካከሉ ነገሮች ቢኖሩም ፈተና አስፈፃሚዎች ይህን ትልቅ እና አገራዊ ኃላፊነት በትጋትና በታማኝነት እንዲወጡ አሳስበዋል፡፡

የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በበኩላቸው የትምህርት ጥራት ከተበላሸባቸው አንዱ ምክንያት ከአንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሚመጡ ተማሪዎች የጥራት ማነስ እንደሆነ አውስተዋል፡፡ ይህን ለመቅረፍ በምንሰራቸው ስራዎች ትምህርት በስርቆት በአቋራጭ የሚገኝ ሳይሆን ደክሞ፣ ለፍቶና አጥንቶ የሚገኝ መሆኑን በተማሪዎቻችን ስነ አዕምሮ ላይ መቅረፅ አንዱ እና ትልቁ ስራ ነው ብለን፤ ይህን አድካሚ ስራ ለመስራት በጋራ የገባንበት ነው ብለዋል፡፡

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዚዳንት ዶ/ር እሰይ ከበደ በውይይቱ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ዩኒቨርሲቲው 35,822 አካባቢ ተፈታኞች እና ከ1,520 በላይ ፈተና አስፈፃሚዎችን መቀበሉን በመግለፅ ይህን ያህል ቁጥር መቀበል ጫና ቢኖረውም ለስራ በተቋቋመው ግብረ ሀይል ያልተቋረጠ ጥረት አሁን ላይ ፈተናውን በተሳካ ሁኔታ ለመጨረስ የተደረገው ዝግጅቱ ውጤታማ ነው ብለዋል፡፡

በትምህርት ሚኒስቴር በኩል የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን ለማስተባበር የተገኙት ዶ/ር ኢዶሳ ተርፋሳ አሁን የመጣንበት ዋና ዓላማ የፈተና ላይ ስርቆትን በማስቀረት መንግስትን ለማገዝ ነው፡፡ ፈተናውን በማስፈፀም ሂደት ውስጥ ትኩረት ሊደረግባቸው የሚገቡ ነጥቦችን ፈተና ከመጀመሩ በፊት ተማሪዎችን ከ1 ስዓት በፊት ተፈትሸው መግባታቸውን ማወቅ፣ ተፈታኞች በመፈተኛ ክፍል መታወቂያ እና ሌሎች ደጋፊ መረጃ መያዙን ማረጋገጥ፣ ወደ መፈተኛ ክፍላቸው ሲገቡ የራሳቸው መለያ ኮድ የተጻፈባቸው ቦታዎች መቀመጣቸውን ማወቅ፣ ወደ ፈተና ቦታ ሲገቡም ሆነ ሲወጡ ድምፅ ማሰማት እንደሌለባቸው ማሳወቅ፣ ተማሪዎች ወደ መፈተኛ ክፍል ሲመጡ እርሳስ፤ላጲስና መቅረጫ ይዘው መቅረባቸውን ማረጋገጥ ይገባል፡፡ በዋናነት ወደ ፈተና ክፍል ከገቡ በኋላ የሚሰጣቸውን ፎርም እንዴት መሙላት እንዳለባቸው ማገዝ እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል፡፡

https://t.me/bahir_dar_university
https://t.me/bahir_dar_university
1.3K viewsedited  17:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-09 20:37:05
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ለተፈታኝ ተማሪዎች መልእክት አስተላለፉ

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዘዳንት ዶ/ር ፍሬዉ ተገኘ ነገ የሚጀመረዉን ፈተና አስመልክተዉ ለተፈታኝ ተማሪዎች በተሰጠው የግንዛቤ ማስጨበጫ (Orentation) መድረክ ላይ በመገኘት ተማሪዎች ተረጋግተዉ እንዲፈተኑ አሳሰቡ፡፡

በዩኒቨርሲቲዉ ግብርናና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ (ዘንዘልማ ግቢ) የተገኙት ፕሬዘዳንቱ ፈተናዉ ከቦታ ለዉጥ የተለየ ነገር እንደሌለዉ በመግለፅ ተማሪዎች ተረጋግተዉ ፈተናዉን በመዉሰድ በቀጣይ ለዩኒቨርሲቲ መግቢያ ዉጤት እንዲያስመዘግቡ አደራ ብለዋል፡፡

በዩኒቨርሲቲዉ ፈተና ከሚሰጥባቸው ስድስት ግቢዎች አንዱ በሆነው ግብርናና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ 6,358 ተማሪዎች እንደሚፈተኑ ከፈተናዉ አስተባባሪዎች ለማወቅ ተችሏል፡፡

https://t.me/bahir_dar_university
1.3K viewsedited  17:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-09 13:40:33
1.9K views10:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-09 13:40:33
1.5K views10:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ