Get Mystery Box with random crypto!

የጥያቄዎቻችሁ መልስ

የቴሌግራም ቻናል አርማ apostolicsuccession — የጥያቄዎቻችሁ መልስ
የቴሌግራም ቻናል አርማ apostolicsuccession — የጥያቄዎቻችሁ መልስ
የሰርጥ አድራሻ: @apostolicsuccession
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 16.61K
የሰርጥ መግለጫ

የዚህ ኦርቶዶክሳዊ ገጽ ዋና ዓላማ የወጣቱን ጥያቄ መመለስ ነው። ወጣቶች ማንኛውም በሕይወታቸው የገጠማቸውንም ይሁን መንፈሳዊ ጥያቄ በሚረዱት መልክ መልስ ይሰጥበታል
YouTube
https://www.youtube.com/channel/UCPLJimNlqTFBnlbsh_vccgg
ለጥያቄዎችና ለአስተያየቶች
@AbuNak
@Rhripsime

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 14

2022-08-22 12:55:17 ቅዳሴ ማርያም

ቅዳሴ ማርያም በምእመናን እና በካህናት ዘንድ እጅግ ተወዳጅ እና በዚሁ ፆመ ማርያም ወቅት በሁሉም ቀናት የምትቀደስ ቁጥሯ ከአኮቴተ ቀርባን መጽሐፍት ውስጥ ስትሆን ቅዳሴ ጎሥዐ ተብላም ትታወቃለች ምክንያቱም ቅዳሴው በዚሁ ቃል ስለሚጀምር አንዳንድ መጽሐፍት በጀመሩበት ቃል የመጠራት ልምድ አላቸውና ነው።

#ደራሲው #ማን #ነው
ስደራሲዎ የተለያዩ አስተያየቶች ይሰጣሉ እነሱም
፩ የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ሊቃውንት መጽሐፉ በአባ ሕርያቆስ መደረሱን ሲናገሩ(፩)
፪ መጽሐፉን ያጠኑ የሥነ ድርሳን ሙህራን ወይ በአባ ጊዮርጊስ አልያም ስማቸውን መጥቀስ ባልፈለጉ ኢትዮጵያዊያን ሊቃውንት ተደርሷል ብለው ይናገራሉ ።

#አባ #ሕርያቆስ #ማን #ነው?
በቤተክርስቲያን ውስጥ ታዋቂነት ያለው አባት ሲሆን ከእርሱ ጋር ተያይዞ የሚተረኩ ትውፊቶች አሉ
፩ ቅዱስ ያሬድ ማኅሌታይ በማይ ኪራህ ሳለ እመቤታችን ተገልፃለት ከቅዱስ ኤፍሬም እና ከአባ ሕርያቆስ ጋር ሆኖ እንዳወደሳት ይነገራል (፪)
፪ የታሪኩ መቼት ልክባይሆንም በድርሳነ ዑራኤልም ሌላ ታሪክ ይተረክለታል።

በቅዳሴ ማርያም ብቻ ሳይሆን በላሐ ማርያም ፣በመጽሐፈ ዕርገታ ለማርያም፣በመጽሐፈ ዶርሆ እና በስምዐ ጲላጦስ ድርሰቶቹም ይታወቃል።
የእረፍት በዓሉ የቤተክርስቲናችን ስንክሳር እንደሚነግረን ጥቅምት ፪(2) ሲሆን በግብፅ ባለችው ቤተክርስቲያናችን ባለው ስንክሳር ግን በእለተ ቀኑ ቅዱስ ሳዊሮስ ዘአንጾኪያ ብቻ ያስባል እንጂ በዚያ እለት ይህን አባት አያነሳም።
ምንአልባት በእነርሱ ዘንድ ስሙ ሌላ ሆኖ ይሆን? በእርግጥ ስማቸው ከስንክሳሩ የሌሉ ቅዱሳንን ቤተክርስቲያኒቱ ስለምታከብር የዚህን አባትም ጉዳይ ከእዚያው ጋር አያይዘን ማየት እንችላለን።
ሐገረ ስብከቱ ብሕንሳ ግን በሌላ ስሟ መኑፍ ትባላለች።

ስለ እዚህ አባት ያጠኑ ምሁራን እንዲህ ይላሉ "አባ ሕርያቆስ የኖረበት ዘመን ዐረበኛ የግብፅ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የሥርዓተ አምልኮ ቋንቋ ከሆነበት ከ12ኛው ምእት ዓመት በኋላ ነው የሚል አስተያየት የሰጡ ምሁራን አሉ አንዳንዶቹም ዘመኑን ከ14-15ኛው ከፍ አድርገዋል።
ነገርግን በአንዳንድ ጽሑፎች ውስጥ በዘመነ አትናቴዎስ (4ኛው ምእት ዓመት) እንደኖረ ስለተናገረና Sahidic በተሰኘው የኮፕቲክ ቋንቋ የተጻፉ ጽሑፎቹ ስለተገኙ አባ ሕርያቆስ የኖረው በ4ኛው ምእት ዓመት ወይም Conti rossni በመጽሐፈ አክሱም እንደነገረን በ6ኛው ምእት ዓመት ነበር ወደሚል ድምዳሜ ተደረሷል"(፫)
ቅዳሴ ማርያም በቤተክርስቲያናችን ትውፊት መሰረት ከጥንትም ጀምሮ በአባ ሕርያቆስ ስም ነው የሚጠራው (ባለቤትነቱን ለአባ ሕርያቆስ ነው የሚሰጠው።)
ለዚህም ገድለ አቡነ ዳንኤል ዘገርዓልታን መጥቀስ ይቻላል።

#የቅዳሴ #ማርያም #ምንጮች
አንድ ጽሑፍ ሲጻፍ ምንጭ አለው በተለይም የቤተክርስቲያን መጽሐፍት መገለጫቸው የቤተክርስቲያንን ቅዱስ ሕያው ትውፊት በየትውልዱ ሁሉ ማስቀጣላቸው እና በምእመናን ኅሊና መሳል ነው።
በዚህ ረገድ ይህ መጽሐፍ ቤተክርስቲያን ለአስተምህሮዋ መጽሐፍ ቅዱስን ቅዱስ ትውፊትን ቅዱሳን ሊቃውንት አበውን...እንደምትጠቀም ሁሉ ይህ ድርሳንም መጽሐፍ ቅዱስን በምንጭነት ይጠቀማል መነሻውን ከመዝሙር ፵፭(45) አድርጎ ይነሳል እያንዳንዱን ክፍል ከመረመርን በመጽሐፍ ቅዱስ ውኃነት የለመለመ ተክል ሁኖ እናገኘዋለን እንዲሁም መጽሐፈ ቀሌምንጦስን አበው ስለ ድንግል ማርያም ስብዕና እና የቅድስና ሕይወቷ ከጻፉት ድርሳናት ምንጭ አድርጓል(በዚህም ከProtovangelium of james ቅዱስ አትናቴዎስ ቅዱስ አምብሮስ ቅዱስ ኤጲፋንዮስ ሊቁ አርጌንስ እና ሌሎች አበው ሊቃውንት ስለ እርሷ ስብዕና ጽፈዋል) እናም የዚህ መጽሐፍ ደራሲ ከእነዚህ አበው ድርሳናት ተጠቅሟል እንዲሁም ሌሎች አበው ሌሎች ስለ እመቤታችን እና ነገረ መለኮት የተነገሩ የተጻፉ ትውፊቶችን ተጠቅሟል።

#ይዘቱ
ቅዳሴ አንዱ የቤተክርስቲያን የአስተምህሮ ምንጭ ነውና እንዲሁም ቤተክርስቲያን የምታምነውን ትጸልያለችና ቤተክርስቲያን ስለ ድንግል ማርያም ያላትኔ ክብር (Veneration of the virgin mary) እና አስተምህሮ እንዲሁም አጠቃላይ የቤተክርስቲያንን አስተምህሮዎች ስለ ነገረሥላሴ ስለ ነገረሥጋዌ ስለ ሚስጢራተ ቤተክርስቲያን ልቡናን ንፁህ ስለማድረግ እና ስለሌሎች ጉዳዮች ያለውን የቤተክርስቲያን አቋም እና ዶግማ ቅዳሴ ሕያው ወንጌል ነውና ስለእነዚህ ሁሉ ይህ ድርሳን ያስተምራል ይመሰክራል።

በረከተ ማርያም ድንግል ይደርብን
በረከተ አባ ሕርያቆስ ይደርብን !

ማጣቀሻዎች
፩ ቅዳሴ ማርያም ትርጓሜ ገፅ፩ -፲(1-10
፪ ዝኒ ከማሁ
፫ ድርሳነ ዑራኤል ዘጥር
፬ ቀሲስ ዶክተር መብራቱ ኪሮስ አኮቴተ ቁርባን ገፅ ፫፻፴፯ (237)
፭ገድለ አቡነ ዳንኤል ዘገርዓልታ ዘወርኃ ሐምሌ
4.0K views09:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-18 17:25:08 Eurocentric ይዘት ያላቸው የኢትዮጵያን ታሪክ በተለይም የኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያናችንን ታሪክ የሚፅፉ ፀሀፊያን ቤተክርስቲያናችንን አውጣኪያዊት (Monophysite) ናት ብለው ሲፅፉ እናያለን ነገርግን ትክክለኛው የቤተክርስቲያናችን የነገረ ክርስቶስ አስተምህሮ ቄርሎሳዊው Miaphysite (አሀዱ እምክልኤቱ) እንደሆነ የቤተክርስቲያናችን አስተምህሮ ይነግረናል ነገርግን በኢትዮጵያ ያለችውን ቤተክርስቲያን ብቻም ሳይሆን መላው የኢ-ኬልቄዶናውያን አብያተክርስቲያናትን(Non-Chalcedonian) የሆኑትን የኦሬንታል ኦርቶዶክስ አብያተክርስቲያናትን Monophysite እና አውጣኪያዊ ብሎ መጥራት ተለምዷል ይህግን የተሳሳተ አመለካከት ነው ምክንያቱም ቤተክርስቲያናችን አውጣኪን ያወገዘች እና የነጠላ አስተምህሮን አጥብቃ የምትኮንን ስለሆነች አውጣኪያዊ ብሎ መጥራት ስምየማጥፋት ዘመቻ ነው ማለት ነው አንድም የቤተክርስቲያናችንን አስተምህሮ ካለመረዳት የመነጨ ችግርነው ምክንያቱም ቤተክርስቲያንን ምን ታስተምሪያለሽ ብሎ ከመጠየቅ ይልቅ በግምት ያላለችውን ትላላች ታስተምራለች ብሎ መፃፍ ግዴለሽነትም ነው።
ለእንደዚህ አይነት ግዴለሾች ደግሞ በሚፅፉበት ቋንቋ ፅፎ የቤተክርስቲያንን አስተምህሮ ለዓለም መግለጥ የተገባ ቅዱስ ተግባር ነው

ለዚህም ደግሞ "Miaphysite Christstology An Ethiopia Perpective" የተሰኘው ቀሲስ ዶክተር መብራህቱ የማስተርስ ጥናታቸውን(MA Thesis) የሰሩበትን ድንቅ የነገረ ክርስቶስ መ
መፅሐፋቸው እነዚህን ሰዎች የሚያሳፍር እና ስህተታቸውን እንዲያርሙ ዕድል የሚሰጥ መፅሐፍ ነው።

#የመፅሐፉ #ይዘት
፩ ከእኅት አብያተክርስቲያናት ጋር ሆነን ነገረ ክርስቶስን የምንገልፅባቸውን ቃላት ማለትም ባህርይ አካል የመሳሰሉትን ቃላት አገራዊ እና ውጫዊ ምንጮችን ዋቢ በማድረግ በሚገባ ያብራራል።
ባህርይ እና አካል የተሰኙት ሁለቱ ቃላት ሰፋ ያለ ትርጉም ያላቸው ናቸው በጥንቷ ቤተክርስቲያንም አበው ሊቃውንት ሰፋ አድርገው ተጠቅመውባቸዋል ለእዚህም የቀሲስን Miaphysite Christologyን መፅሐፍ ከቀሲስ ታድሮስ ያዕቆብ ማለቲ Physis and Hypostatis In Early Church ከሚለው መፅሐፍጋ Parallel አድርጋችሁ ብታነቡት ጥሩ ነው።

፪ ከካቶሊኮች ጋር ስላደረግናቸው ክርክሮች እንዲሁም ስለ ፀጋ እና ቅብዐቶች የነገረክርስቶስ አስተምህሮአቸው ይዳስሳል ስለዚህም መፅሐፉን ፅንአ ተዋህዶ ከተሰኘው የመምህር በዐማን ነፀረ መፅሐፍ ጋ ብታነቡት ጥሩነው።
፫ ቄርሎሳዊውን የተዋህዶ አስተምህሮ ከጥንት አበው እየጠቀሰ ሃይማኖተ አበውን የመልዐከ ብርሀን አድማሱ ጀንበሬን መድሎተ አሚን እና የአለቃ አያሌው ታምሩን መችተለመደና ከተኩላ ዝምድናን እንዲሁም ሌሎች አገራዊ ምንጮችን እንዲሁም በEnglish የተተረጎሙ የአበው ፅሁፎችን ዋቢ አድርጎ ያስተምረናል።
በዚህም በEnglish ከተተረጎመው የአቡነ ሽኖዳ Nature Of Christ መፅሐፍ ጋ ስለሚመሳሰል አብራችሁ አንብቡት።

፬ በዚህ ዘመን ቤተክርስቲያናችን በነገረ ክርስቶስ ዙሪያ ከኬልቆዶን አብያተክርስቲያናት ጋር ከአርሁስ ዴንማርክ-ቻምቤዚ ስዊዘርላንድ ድረስ ሰባት ጉባዔዎችን አድርጋለች ስለእነዚህ ስላደረገቸው ውይይቶች እና በምን ነጥብ እንደተስማማን ይገልፃል በዚህም ቀሲስ ታድሮስ ራሳቸው ግብፅ በተደረገው የምስራቅ እና የኦሬንታል ኦርቶዶክሳውያን የአንድነት ጉባዔ ላይ የተገኙ ሲሆን በምን ነጥብ እንደተስማማን Physis and Hypostatis In Early Church በተባለው መፅሐፋቸው ላይ ገፅ ፵፩(41) እንዲሁም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እምነት እና ስርዓተ አምልኮት እና የውጭ ግንኙነት በሚለው የቤተክርስቲያን ይፋዊ መፅሐፍ ላይ ከገፅ ፻፴፬ - ፻፴፰(134-138) ላይ በሚገባ ተገልጿል።
እንዲሁም ከእኛ ቤተክርስቲያን ሊቃውንት አቡነ መልከፄዴቅ፣ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ፣ቀሲስ ዶክተር ምክረሥላሴ ገብረ አማኑኤል፣አቡነ ገብርኤል፣ከሀሊ አለሙ፣አባ ገሪማ እና ሌሎችም የቤተክርስቲያናችን መልዕክተኞች በተለያየ ጊዜ በመሄድ ጉባዔዎቹን ተሳትፈዋል።

መፅሐፉን ታነቡት ዘንድ ጋበዝኳችሁ።
4.5K views14:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-17 10:05:29 በዚህ ቪዲዮ ነግሪያችሁ የነበረው ልጅ ትላንት ወደ ልዩ ክትትል ሊገባ ወደ አመሻሽ እህቱ ጸሎት እንዲደረግለት ጠይቃን አባት ይዘን ሄደን ፀሎት አድርገውለት በጸበል ባርከውት ተመልሰዋል። አሁን ግን ተደውሎልኝ በሰላም አርፏል ተባልኩኝ። እግዚአብሔር ነፍሱን ከቅዱሳን ጋር ያድርግልን። ለእህቱም ለቤተሰቦቹም ሁሉ መጽናናትን ያድልልን።
4.5K views07:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-14 09:36:33 ለኪዳነ ምህረት ወዳጆች የቀረበ የበረከት ጥሪ

በሐዋሳ የኪዳነ ምህረት ጽዋ ማኅበር የተዘጋጀ ለነሐሴ 16/2014 ዓ.ም ለኪዳነ ምህረት ዓመታዊ ዝክር የነድያን ምገባ የሚያስፈልጉ ዝርዝር
አይነት ብዛት ዋጋ
እንጀራ.........150..........1500
ዘይት............ 5Lit.........900
በርበሬ.......... 1:30........500
ሥጋ.............. 3kg..........1500
ምስር............ 3kg...........500
ሽንኩርት........15kg.........1000
ድንች............ 10kg........ 300
እንጨት......... ......... 500
ነጭ ሽንኩር....2kg............120
ቅመማቅም ...................200

ከነዚህ መካከል አቅማችሁ የፈቀደውን አንዱን በመቻል የበረከቱ ተሳታፊ እንድትሆኑ በኪዳነ ምህረት ስም ጥሪያችንን እናስተላልፋለን

1000359175508
የአብስራ ዓለም

ለበለጠ መረጃ
0985124428
6.1K viewsedited  06:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-13 20:52:52
አለምፀሐይ ጅፋር
1000020000997
(አሥርሺ ሀያሺ ዘጠናዘጠኝ ሰባት)
ንግድ ባንክ

ሼር ይደረግ
5.7K views17:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-11 10:39:22 የወንድሜ ብስራት መዝሙር ተለቋል ሁላችሁም እየገባችሁ ተመልከቱ



6.4K views07:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-06 21:42:10
የወንድሜን ጥዑም መዝሙር ሰሞኑን በማኅቶት ቲዩብ ጠብቁ
8.0K viewsedited  18:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-21 11:07:39
ተሳተፉ
11.5K views08:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-12 08:46:51
ምን ለማለት ነው ፆም አናበላልጥ
ለማንኛውም እንኳን ለበዓለ ሐዋርያት በሰላም በጤና አደረሳችሁ።
2.9K viewsedited  05:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ