Get Mystery Box with random crypto!

አዲስ ዘመን ጋዜጣ |Addis Zemen Vacancy

የቴሌግራም ቻናል አርማ amhara_media_corporation — አዲስ ዘመን ጋዜጣ |Addis Zemen Vacancy
የቴሌግራም ቻናል አርማ amhara_media_corporation — አዲስ ዘመን ጋዜጣ |Addis Zemen Vacancy
የሰርጥ አድራሻ: @amhara_media_corporation
ምድቦች: ስፖርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 20.11K

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2021-08-17 18:13:01
#Facebook

ፌስቡክ ታሊባንን እንደ አሸባሪ ቡድን እንደሚመለከተውና ከቡድኑ ጋር የተያያዙ መልዕክቶችን እንደሚያቅብ አስታወቀ።

ፌስቡክ ታሊባንን የሚያደንቁ ይዘቶችን፣ የቡድኑን መልዕክቶችን አግዳለሁ ብሏል።

ይህን ሳንሱር እንዲሠሩለት አንድ ልዩ የአፍጋኒስታን ባለሙያዎች ቡድን ማዋቀሩን እና በእነዚህ ባለሙያዎች እየታገዘ የታሊባን ይዘቶችን ወዲያውኑ ከፌስቡክ ሰሌዳዎች ላይ እንደሚያጠፋ ፌስቡክ ዝቷል።

ታሊባን ለዓመታት መልዕክቶቹን በመላው ዓለም ለማድረስ ፌስቡክን እንደ አንድ መገናኛ ብዙኃን ሲጠቀምበት ቆይቷል።

ታሊባን አሁን የመንግሥትን መዋቅር መቆጣጠሩ ማኅበራዊ የትስስር መድረኮች ቡድኑን እንዴት ማስተናገድ እንዳለባቸው በድጋሚ እንዲያጤኑ እያደረጋቸው ነው።

የፌስ ቡክ ቃል አቀባይ ፥ "በአሜሪካ ሕግ ታሊባን አሸባሪ ቡድን ነው። ይህ ሕግ እኛም በዚያው ሁኔታ እንድናያቸው የሚያደርገን ነው። በመሆኑም ከታሊባን ጋር የሚያያዙ ማናቸውንም መልዕክቶች እናቅባለን" ብለዋል።

ፌስቡክ ዋንኛ የአፍጋኒስታን ቋንቋ የሆኑትን ዳሪ እና ፓሽቶን የሚናገሩ አፍጋኒስታዊያን ተወላጆችን ለዚሁ ተግባር ሲል መልምሎ፣ ቀጥሮ እያሠራ እንደሆነ ተናግሯል።

የፌስቡክ ኩባንያ እቀባውን ተግባራዊ የሚያደርገው በእህት ኩባንያዎቹ በኢንስታግራምና በዋትስአፕ የትስስር መድረኮች ጭምር ነው።

ምንጭ፦ ቢቢሲ

@zena_tube11
@zena_tube11
86.9K views15:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-08-15 15:14:14
#Kabul

የታሊባን ታጣቂዎች ካቡል ደጃፍ ቆመዋል።

ለመሆኑን ከሰሞኑ በአፍጋኒስታን ምን ሆነ ? በአጭሩ ...

- "ታሊባን" በአሜሪካ መራሹ ጦር እአአ ጥቅምት 2001 ነው ከስልጣን የወረደው ፤ ቡድኑ ኦሳማ ቢን ላደንን እና ሌሎች መስከረም 11 በአሜሪካ ላይ ከተፈፀመ ጥቃት ጋር ተያያዥነት ያላቸውን ግለሰቦች እና ቡድኖች ዒላማ ያደረገ ነበር።

- ታሊባን ከስልጣን የተገፋው አሜሪካ አፍጋኒስታን ላይ ባካሄደችው ወረራ ነው።

- የአሜሪካ እና ኔቶ ጦር ኃይሎች በአፍጋኒስታ ለ20 ዓመታት ያህል ቆይተዋል።

- የአሜሪካ ፕሬዜዳንት ጆ ባይደን አፍጋኒስታን የነበሩትን የአሜሪካ ወታደሮች የማወጣት ውሳኔ አሳልፈው ወታደሮቻቸውን አስወጥተዋል።

- 20 ዓመታት በአፍጋኒስታን የነበሩት የአሜሪካ እና ሌሎች ኃይሎች /ኔቶ/ ከአፍጋኒስታን መውጣታቸው ተከትሎ ታሊባን የተለያዩ ከተሞችን ከአሁኑ መንግስት ማስለቀቅ ጀመረ።

- አሜሪካ በአፍጋን ያሉ ዜጎቿን ለማስወጣ 5 ሺህ የሚደርሱ ወታደሮችን ልካ በዛው ያሉ ዜጎቿን፣ በኤምባሲ የሚሰሩ ሰራተኞቿን እያስወጣች ነው።

- በአጭር ጊዜ ውስጥ ታሊባን በርካታ ከተሞችን ወሳኝ መስመሮችን ተቆጣጥሯ ፤ አሁን ደግሞ በመንግስት እጅ በብቸኝነት ቀርታለች የተባለችውን ካቡልን (ዋና ከተማ) ከቧል።

- ካቡል ዙሪያዋ በታሊባን ታጣቂዎች ተከባ ምጥ ላይ ነች። የታሊባን ታጣቂዎች በመዲናዋ መውጪያና መግቢያዎች ላይ ታጣቂዎቻቸው እንዲጠብቁ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል።

- የአፍጋኒስታን የሃገር ውሰጥ ጉዳይ ሚኒስትር ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር ይደረጋል ፥ ለሽግግር መንግሥቱም ስልጣን ይሰጣል ብለዋል።

- ታሊባን ካቡልን በኃይል እንደማይወስድ ገልጿል፤ ከመንግስት ጋር ድርድር ላይ መሆኑንም አሳውቋል።

(ከቢቢሲ እና AFP የተውጣጣ)

@zena_tube11
@zena_tube11
70.9K views12:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-08-09 19:13:03
ዩኒሴፍ በአፋር ክልል በተፈናቃዮች ላይ ተፈጸመ የተባለው ግድያ እንዳስደነገጠው ገለጸ

የተባበሩት መንግስታት የህጻናት መርጃ ድርጅት (ዩኒሴፍ) በአፋር ክልል በጤና ተቋም እና ትምህርት ቤት ውስጥ ተጠልለው የነበሩ ከ100 በላይ ህጻናትን ጨምሮ፤ 200 የሚልቁ ተፈናቃዮች ተገድለዋል መባሉ በእጅጉ እንዳስደነገጠው አስታወቀ። በአፋር እና በሌሎች የትግራይ አዋሳኝ ቦታዎች የሚደረገው ውጊያ ተጠናክሮ መቀጠሉ ለህጻናት አስከፊ መሆኑንም ድርጅቱ ገልጿል።

ዩኒሴፍ በአፋር ክልል ተጠልለው በነበሩ ተፈናቃዮች ላይ ባለፈው ሳምንት ሐሙስ ተፈጽሟል የተባለውን ግድያ በተመለከተ መግለጫ ያወጣው ዛሬ ሰኞ ነሐሴ 3፤ 2013 ነው። በድርጅቱ ዋና ዳይሬክተር ሄንሪታ ፎር ስም የወጣው ይኸው መግለጫ፤ የተመጣጠነ ምግብ እጥረት እና የምግብ ዋስትና ችግር አሳሳቢ ደረጃ ላይ በደረሰበት በዚህ አካባቢ፤ ወሳኝ የምግብ አቅርቦቶች ወድመዋል መባሉንም ጠቅሷል።

የተመድ የህጻናት መርጃ ድርጅት በአፋር ክልል ተፈጸመ ስለተባለው ጥቃት እና ስለ ደረሰው ጉዳት በመግለጫው ቢጠቅስም፤ ድርጊቱን የፈጸመው አካል የትኛው ወገን እንደሆነ ከመግለጽ ተቆጥቧል። የአፋር ክልል የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ባለፈው አርብ ሐምሌ 30 ባወጣው መግለጫ ለጥቃቱ የህወሓት ኃይሎችን ተጠያቂ አድርጎ ነበር።

@zena_tube11
@zena_tube11
71.5K views16:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-08-08 17:24:26
#Somali

በሱማሊ ክልል በሻለቃ ከደር መሀሙድ የውትድርና ማሰልጠኛ ማዕከል ሲሰልጥኑ የነበሩ የሶማሊ ክልል ሚሊሺዎች ዛሬ ተመርቀዋል።

የሻለቃ ከደር መሀሙድ የውትድርና ማሰልጠኛ ማዕከል በብርቆድ ወረዳ የሚገኝ ሲሆን በዚህ ማሰልጠኛ ውስጥ ሲሰለጥኑ የነበሩ ሚሊሺያዎች ናቸው ዛሬ ተመረቁት።

የተመረቁት አጠቃላይ የሚሊሻዎች ቁጥር ምን ያህል እንደሆነ መረጃውን ይፋ ያደረገው የክልሉ ብዙሃን መገናኛ ያለው ነገር ባይኖርም በተሰራጩት ፎቶች መመልከት እንደተቻለው በርካታ ናቸው።

በምርቃው ስነስርዓት ላይ ፦
- የሶማሊ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ሙስጠፋ ሙሁመድ፣
- የሰላምና ደህንነት ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር ሁሴን ሃሺ፣
- የሶማሊ ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ሀላፊ ኢ/ር መሀመድ ሻሌ፣
- የሶማሊ ክልል ልዩ ሀይል አዛዥ ም/ኮ መሀመድ አህመድ፣
- የሶማሊ ክልል ፖሊስ ኮ/ኮምሽነርና የዞን አስተዳደሪዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተው ነበር።

Photo Credit : SRTV

@zena_tube11
65.3K views14:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-08-08 16:45:32 በአፋር ክልል አዉሲ-ረሱ ዞን አይሳኢታ ወረዳ በአዋሽ ወንዝ ሙላት በሦስት ቀበሌዎች የጎርፍ አደጋ መከሰቱን የክልሉ የአደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ጽሀፈት ቤት አስታወቀ።

በጽህፈት ቤት የቅድመ-ማስጠንቀቅና ፈጣን ምላሽ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አይዳሂስ ያሲን እንደተናገሩት ከሃምሌ 28 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ በወረዳዉ ሦስት ቀበሌዎች የአዋሽ ወንዝ ሰብሮ በመውጣት ጎርፍ አስከትሏል።

አደጋው ቀድሞ በተከናወኑ የቅድመ-ጥንቃቄቅ ስራዎች ህብረተሰቡ ከአካባቢዉ እንዲወጣ በመደረጉ የተፈናቀሉ ሰዎች ከመቶ አባዋራዎች የማይበልጡ ሲሆን፤ ጎርፉ 50 ሄክታር መሬት በሚሆን የእርሻ መሬት ላይ ጉዳት አድርሷል ብለዋል።

ጎርፍ የተከሰተባቸዉ ቀበሌዎች የከርቡዳ፣ ኮሎዱራና ሂነሌ ቀበሌዎች ሲሆኑ÷ ጎርፉ የሰበረበትን አካባቢ ለመዝጋት ከሚመለከተዉ የተፋሰስ ባለሰልጣን ጋር በመሆን ርብርብ እየተደረገ ነው ሲሉ ገልፀዋል።

በክረምቱ ከፍተኛ ዝናብ እየተመዘገበ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በክልሉ የአዋሽ ወንዝን ተከትለዉ በሚገኙ አስር ወረዳዎች የጎርፍ አደጋ እንደሚከሰት ይጠበቃል ያሉት ዳይሬክተሩ÷ ለዚህም ቀደም ሲል አስፈላጊው የቅድመ ዝግጅት ስራ መከናወኑን አስረድተዋል።

በተለይም በነዚህ ወረዳዎች ስር የሚገኙ 40 ቀበሌዎችን ጨምሮ ከአጎራባች ከፍተኛ ቦታዎች የሚነሱ ተፋሰሶች ምክንያት በነዚህ አካባቢዎች ከ90ሺህ ሰዎች በላይ የጎርፍ ተጠቂዎች ሊሆኑ እንደሚችሉ ገልጸዋል።

@zena_tube
58.1K views13:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ