2022-09-05 20:25:24
ሰበር የድል ዜና
ጠንካራውና የመጨረሻው የሸረሪማ ምሽግ ተሰበረ!!
ጥቅምት 30/2013 ዓ.ም ሳምረ የተባለው የትህነግ አሸባሪው ቡድን በማይካድራ ይኖሩ የነበሩ ወደ 2000 የሚጠጉ ንጹሃን የአማራ ተወላጆችን በአማራነታቸው ምክንያት ብቻ በግፍ ጨፍጭፎ፣ የኢትዮጵያ ጥምር ጦር ሲደርስበት ወደ ሱዳን መፈርጠጡ አይዘነጋም። ከዚያም የአሸባሪው ቡድን ታጣቂ በሱዳን የሽብር ስልጠና ሲወድ መቆየቱ ይታወቃል። ሽብርተኛው ቡድን ከታሪካዊ የኢትዮጵያ ጠላቶች ጋር በማበርና ተልኮ በመቀበል የወልቃይት ጠገዴን ኮሊደር ለማስከፈት በተደጋጋሚ ትንኮሳ ሲፈጽም ቆይቶል። ቢሆንም ግን በእየ ጊዜው የጀግኖቹን ክንድ እየቀመሰ ተመልሷል።
አሸባሪው ትህነግ ሰሞኑንን በይፋ ሶስተኛውን ወረራ መጀመሩን ተከትሎ በሱዳን የሽብር ስለጠና ሲወስድ የነበረውን በርካታ ሽብርተኛ በሰሜን ምዕራብ ጎንደር ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን በሚገኙት በበረከትና ልጉዲ ግንባር አሰልፎ ጦርነት ከፍቶ ሰንብቷል። ይሁን እንጂ ጀግናው የኢትዮጵያ ጥምር ጦር የመጣውን አሸባሪ በዕርሳስ አረር ቆልቶ፣ በቦምብ አንድዶ፣ በመድፍ አዳፍኖ፣ በብሬንን ረፍርፎ፣ በስናይፐር ነድሎ...ወደ አፈርነት ቀላቅሎታል። አመድ አድርጎ በትኖታል። ምሽጉ ተደርምሷል።
ዛሬ ደግሞ በሰሜን ምዕራብ ጎንደር ወልቃይት ጠገዴ በረከት ፊት...ለፊት ግዴማ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ልዩ ስሙ ሸረሪማ ወይም ነጭ ድንጋይ እየተባለ በሚጠራው ቦታ አሸባሪው ትህነግ በከፍተኛ ሁኔታ ገንብቶት የነበረው ጠንካራ ምሽግ በጀግናው የኢትዮጵያ ጥምሮ ጦር ክንድ ተደርምሷል። የአሸባሪው ተወጊ ከምሽጉ ጋር አብሮ ተደምስሷል። የሸረሪማው ወይም የነጩ ዲንጋይ ምሽግ የአሸባሪው ትህነግ በግንባሩ ጠንካራውና የመጨረሻው ምሽግ እንደነበር ታውቋል።
2.7K views17:25