Get Mystery Box with random crypto!

Albastros Ministries

የቴሌግራም ቻናል አርማ albastrosministries — Albastros Ministries A
የቴሌግራም ቻናል አርማ albastrosministries — Albastros Ministries
የሰርጥ አድራሻ: @albastrosministries
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 13.83K
የሰርጥ መግለጫ

"መልህቄ" የተሰኘው አልበሜን ዳውንሎድ በማድረግ ይባረኩበት:: ሊንኩን ለሌሎችም ያካፍሉ::

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-07-23 18:51:14 በረጅሙ የህይወት ጎዳና ጉዞ ውስጥ በተለያዩ ምክንያቶች "ድክም: ትክት ብሎኛል “የምትሉ ይህችን መዝሙሬን ልጋብዛችሁ:: ዛሬ ለአንድ ሰው መልእክት ቢሆን ሼር አድርጉት

10.4K viewsedited  15:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-19 17:47:18
የሰላም አለቃ ሆይ
ሰላም ለእናንተ ይሁን በለን
11.6K views14:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-14 09:39:25 ማልኮስ

ማልኮስ ማነው?

በዮሃ 18 ላይ ከይሁዳ ጋር አ'ብ'ሮ: ኢየሱስን ሊይዙ ከካህናት አለቆችና እና ከፈሪሳውያንም ሎሌዎች መካከል ወይ ጦር እና ጋሻ አልያም ችቦ እና ፋና ይዞ የመጣ ነው::

ኢየሱስን ያውቅ ነበር?
በፍፁም::
እንደውም ኢየሱስ:- ማንን ትፈልጋላችሁ? ብሎ ሲጠይቃቸው.... እነርሱም፡— የናዝሬቱን ኢየሱስን፡ ብለው ሲመልሱለት እርሱም : እንግዲህ፡— እኔ ነኝ ባላቸው ጊዜ ወደ ኋላ አፈግፍገው በምድር ሲወድቁ መፅሃፍ ቅዱሳችን ይነግረናል::

ታድያ በዚህ መካከል ስምዖን ጴጥሮስ 'ሰይፍ ስለነበረው' ሰይፉን ሲመዝዘው፥ የሊቀ ካህናቱንም ባርያ/ማልኮስን መትቶ ቀኝ ጆሮውን ሲቈርጠው እንመለከታለን::

"ስምዖን ጴጥሮስም ሰይፍ ስለ ነበረው መዘዘው"
ዮሃ 18:10

ሰይፍ ስላለ አይመዘዝም
ጥቅስ ስላለ አይጠቀስም
ድንጋይ ስላለ አይወረወርም
ከኢየሱስ ይህን አልተማርንም

ወዳጆቼ
"እስቲ አጠገባችሁን ያለውን ሰው ጎሰም አድርጉትና: ሰይፍ ስላለህ አይመዘዝም በሉት" የሚለን ሰባኪ ያሻናል::
እንኩዋንስ ኢየሱስን እያወቀ ያጠፋ: የሳተ: የተሳሳተ:የወደቀ....ወንድማችን ይቅርና ኢየሱስ የማያውቀው ማልኮስን እንድንመታ: እንድንወግር ሰይፋችንን እንድንመዝዝ አልተፈቀደልንም::

ይህን ስል ያጠፋ አይመከር:አይገሰፅ እያልኩ አይደለም:: ነገር ግን በሰይፍ አይመከርም ነው ሃሳቤ!! አስባችሁታል ጥፋትን ያጠፋ ሰው: ሰይፍን ግራ ቀኝ እያወናጨፋችሁ "ልመክርህ ነው ስማኝ!!" ብትሉት ?? ይህ ሰው እየተመከረ በመሃል: ሳይጨርስ ወይ ጆሮ አልያም አንገቱ ሊ'ቀ'ላ ይችላል:: ተመካሪውም ላይሰማ እና ላይመለስ እስከወዲያኛው ልናጣው እንችላለን::

መልእክቴ ይህ ነው:
ኢየሱስም ጴጥሮስን፡— ሰይፍህን ወደ ሰገባው ክተተው እንዳለው: ሰይፋችንን ወደ ሰገባችን ከትተን: እጃችንን ለማቀፍ እና ለመርዳት ይዘርጋ::

ሳሙኤል ተስፋሚካኤል ብዙነህ
3.3K views06:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 20:10:29
4.2K views17:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-12 18:05:43
5.3K views15:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-01 03:52:57 https://fb.watch/dZ-KCY41FK/
9.9K views00:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-28 23:41:03 ወደ ፀጋው ዙፋን መቅረብ ዕብ4:16 (ክፍል 2)

መቼም እግዚአብሔር ባለንበት ሆነን መባረክ: መስጠት: መፈወስ አቅቶት አይደለም:: እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ ወደ እኔ ኑ: እኔም አሳርፋችዋለው ሲል: ባለንበት ሆነን ሸክማችንን መውሰድ: ማሳረፍ አቅቶት አይደለም::: አንድያ ልጁ ክብሩን ትቶ እንዲወርድ የጨከነበት ምክንያት ወደ እርሱ እንድንቀርብ ከእርሱም ጋር ህብረትን እንድናደርግ እንደ ተወደዱ ልጆች በቤቱ እንድንኖር: ከእግሩ ስር እንድንሆን ነው::

እናም ፀጋን: ምህረትን: በረከትን ማንኛውንም የሚያስፈልገንን ነገር ስንጠይቀው አሁንም "ቅረቡ" ይለናል:: ወደ ፀጋው ዙፋን :ወደ መገኘቱ ወደ ህልውናው እንድንቀርብ ይፈልጋል:: የምንፈልገውን ነገር ይዘን እንድንሄድ ሳይሆን: እርሱ ጋር እንድንኖር: ከምንፈልገው ነገር በላይ እሱን እንድንሻ: የምንፈልገው ነገር ግዜአዊ :እርሱ ግን የዘላለም ፍላጎታችን መሆኑን ልናሳየው ይወዳል:: ስለዚህ እንቅረብ: ከትላንትናው ይልቅ ወደ ፀጋው ዙፋን እንቅረብ::

ታድያ ወደ ዙፋኑ ሲቀረብ: በብዙ አክብሮት በመፍራት: የሚገባውን ክብር በመስጠት: በመገዛት በአጠቃላይ በአምልኮ ነው:: በአምልኮ ወደ ፀጋው ዙፋን ስንቀርብ: የምናየው ችሎታውን ነው:: የማድረግ ችሎታ: ጉልበቱን አቅሙን::

ያንን ሁሉን ቻይነቱን ስናይ: ይዘን የመጣነው ችግር: ድካም: አቅም ማጣት: እንረሳዋለን:: ከጉልበቱ ጉልበትን: ከአቅሙ አቅምን እናገኛለን:: ያኔ አቤቱ ጕልበቴ ሆይ፥ እወድድሃለሁ።እግዚአብሔር ዓለቴ፥ አምባዬ፥ መድኃኒቴ፥ አምላኬ፥ በእርሱም የምተማመንበት ረዳቴ፥ መታመኛዬ እንለዋለን:: እርሱ ደግሞ በእርሱ የሚታመኑትንም ያውቃል። ለእነርሱም መልካም ነው፥ በመከራ ቀንም መሸሸጊያ ነው::

ኢየሱስም ሃዋርያቱም አገልግለው ያለፉት: ሰዎች ወደ እግዚአብሔር በእምነት እንዲቀርቡ ነውና: እኛም አገልግሎታችን ሰዎች ወደ እኛ ሳይሆን ወደ እርሱ እንዲቀርቡ ይሁን::

አባት ሆይ: ወደ ፀጋህ ዙፋን በእምነት እቀርባለው

ሳሙኤል ተስፋ ሚካኤል ብዙነህ
10.2K viewsedited  20:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-27 06:10:00
ፀጋን ለማግኘት ወደ ፀጋው ዙፋን መቅረብ::

ፀጋ ነፃ ስጦታ ነው:: ነፃ የሆነው በገንዘብም ሆነ በየትኛውም ውድ ነገር የማይለወጥ ወይንም የማይገዛ ስለሆነ የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ ፀጋ እና እውነትን ተሞልቶ: በእኛ አድሮ:በፀጋ ላይ ፀጋን ሰጠን:: ከዚህም የተነሳ በፀጋው ውስጥ ከሰው ያልሆነ በቃል የማይገለፅ አቅም/ ችሎታ አለ::

ታድያ በተለያየ ምክንያት ይህን መረዳት እና በህይወታችን መተግበር ቢያቅተን: ተስፋን አንቁረጥ:: አሁንም ፀጋን ለማግኘት ወደ ፀጋው ዙፋን በእምነት እንቅረብ:: በአቅማችን: በገንዘባችን እንዲሁም በሰው ባልቻልነው ነገር ላይ: ብዙ በሚያታግለን ነገር ላይ: የመጨረሻ የሚባለውን አቅማችንን: ትግሉ ላይ ሳይሆን: የሚረዳንን ፀጋ ለማግኘት ወደ ፀጋው ዙፋን ለመቅረብ እንጠቀምበት::

ስንቀርብ ደግሞ በማጉረምረም: አታየኝም ወይ በሚል ኩርፍያ እና ንዝነዛ ሳይሆን: በራሴ አልቻልኩትም አንተ ግን ትረዳኛለህ: በሚል እምነት ይሁን:: ያኔ እሱ በእምነት ስለቀረብን ደስስ ይለዋል:: መልሶም በአባታዊ ድምፁ "ፀጋዬ ይበቃሃል/ይበቃሻል" ይለናል::

በመጨረሻም የሚረዳው ፀጋ ከፀጋው ዙፋን በእምነት ሲገኝ ያኔ አሸናፊ ብቻ ሳይሆን ከአሸናፊዎች በላይ ያደርጋል::

ዛሬ ማነው ከእኔ ጋር ፀጋ ይብዛልኝ የሚል?
ሳሙኤል ተስፋሚካኤል ብዙነህ
9.5K viewsedited  03:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-25 18:22:20
የነፍስን:የውስጥን ጩሀት ፀጥ ሊያደርግ: መልስ ሊሆን የሚችል የእግዚአብሔር ክብር ብቻ ነው:: ስለዚህ DMV አከባቢ ያላችሁ ኑ አብረን ፊቱን እንፈልግ:: "ክብርህን አሳየን" ብለን እንጩህ እርሱ ይሰማናል ሰምቶም ይመልስልናል:: July 2 @6pm
8.9K views15:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-24 12:35:03
9.6K views09:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ