Get Mystery Box with random crypto!

Affini Media and Communication

የቴሌግራም ቻናል አርማ affinimedia — Affini Media and Communication A
የቴሌግራም ቻናል አርማ affinimedia — Affini Media and Communication
የሰርጥ አድራሻ: @affinimedia
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.18K
የሰርጥ መግለጫ

This media aims to deliver intellectual ideas &alternative ways to create a strong Sidaama nation, promote its culture, language, advocate inclusiveness, coexistence, advance economic&social development.
https://youtu.be/Vyk-UrJeXQQ

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-30 09:33:01
311 views06:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 09:32:55 በደቡብ ከልል Human Africa Trypanosomiasis (sleeping sickness) የተባለ አዲስ በሽታ መከሰቱ ተገልጿል፤
========================
አፊኒ ነሐሴ 25፣2014
ሀዋሳ

አፋጣኝ የህክምና እርዳታ ካልተገኘ የሰው ልጆችን በህይወት የመቀጠል ጉዳይ እጅግ ፈታኝ ያርገዋል ወይም ገዳይ ነው የተባለለት በሽታ Human Africa Trypanosomiasis (sleeping sickness) መከሰቱን የደ/ብ/ብ/ህ/ክ/መንግስት ጤና ቢሮ የሕብረተሰብ ጤና ኢኒስቲትዩት ባካሄደው የሳምንታዊ ውይይት አስታውቋል።

በአሁኑ ወቅት Human Africa Trypanosomiasis (sleeping sickness) ክስተት በጋሞ ዞን በቁጫ አልፋ ወረዳ የኦሞ ወንዝ ሸጥ ከሆኑ ቀበሌያት ወደ ሰላምበር መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በወባ በሽታ ተጠርጥረው ለህክምና በመጡ ታካሚዎች ላይ በተወሰደ ናሙና ውጤቱን ለማወቅ ተችሏል ብሏል።

በመሆኑም በክልሉ በየትኛውም አካባቢዎች መሰል የህመም ምልክቶች ክስተት ዙሪያ በህረተሰቡ ዘንድ ግንዛቤ እየተፈጠረ መሄድ ስላለበት እና በተለይ አሁን ክስተቱ በተፈጠረባቸው አከባቢዎች ጋር አጎራባች የሆኑና አና በማህበራዊ ትስስር የሚገናኙ ሁሉም ቀበሌዎች ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ በየአከባቢው ባሉ የጤና መዋቅር በአስቸኳይ ሪፖርት እንዲደረግ ጥሪውን ኢኒስቲትዩቱ አቅርቧል።

በአገራችን ትኩረት የሚሹ አሩራማ በሽታዎች ከመከላከልና ከመቆጣጠር አንፃር ከዓለም ጤና ድርጅት እና ከተለያዩ አጋር ድርጅቶች ድጋፍ የፌዴራል ጤና ሚኒስቴር ከኢትዮጲያ ህብረተሰብ ጤና ኢኒስቲትዩት እና ከጤና ቢሮ ጋር በመተባበር በተለያዩ የጤና ፕሮግራሞች በተቋማትና በማህበረሰብ አቀፍ እየተከናወኑ ይገኛሉ ፡፡

@via ደ/ብ/ብ/ህ/ክ/መንግስት ጤና ቢሮ
አፊኒ_ሚዲያና_ኮሙኒኬሽን
#Affini_Media_Communication
ትኩስ እና እውነተኛ መረጃዎችን ለማግኘት ይከታተላሉ
ዩቲዩብ:https://youtube.com/channel/UCzxVCZUtW-XmosukNkCXZEA
telegram:https://t.me/affinimedia
https://t.me/affinihasaaw
276 views06:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 07:44:25
508 views04:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 07:44:06 በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ከ 3 ሚልዮን በላይ ህዝብ ለከፍተኛ ረሀብ አደጋ እንደተጋለጠ ተመለከተ፤
==================================:=
አፊኒ ነሐሴ 24፣2014
ሀዋሳ
በዘንድሮው ዓመት የአየር ንብረት ለውጥ ባስከተለው አደጋ በክልሉ 17 ወረዳዎች የግብርና ምርት ሙሉ በሙሉ ውጤት አልባ መሆናቸውን ተከትሎ በሚሊዮኖች የሚቆጠር ህዝብ ለከፍተኛ ረሀብ ተጋልጧል። ይሁን እንጂ እስከአሁን የክልሉ ግብርና ቢሮ መረጃውን ለሚመለከታቸው አካላት እንድሁም ለፌደራል መንግሥት ለመስጠት ፈቃደኛ ባለመሆኑና አስፈላጊ ትኩረትና ድጋፍ ማግኘት ባለመቻሉ ህዝቡ የመኖር እና ያለመኖር ፈተና እንደተጋረጠበት ለአሚኮ አሳውቋል።

የሲዳማ ህዝብ ለብዙ ዘመናት የምግብ ዋስትናውን ያለ ማንም እርዳት ያረጋገጠ፣ ከእራሱ አልፎ ሌላውን የሚመግብ መሆኑ የሚታወቅ ቢሆንም እራሱን በእራሱ የማስተዳደር የፓለቲካ ጥያቄው በተመለሰ ማግስት ትኩረት ያላገኘ የረሀብ አደጋ፣ የህዝብን ፍላጎት ያማከለ ልማት እጦት፣ የመልካም አስተዳደር ችግር እየተፈታተነው ይገኛል። ለዚህም ማሳያዎች ሰሞኑን የክልሉ ኦድት ቢሮ ይፋ ባደረገው ሪፖርት መሠረት በአንድ አመት ውስጥ 197,025,436.32 ብር ጉድለት ተገኝቷል።

ከዚህም ባሻገር የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ በዞን መዋቅር ወቅት የነበረ እና የአንድ አመት የክልሉ ፋይናንሻል ሪፖርት መረጃ በማሸሽ ተጠያቂነት እንዳይኖር ማድረጉ ይታወሳል። የሆነ ሆኖ የክልሉ መንግስት ለተከሰተው ረሀብ ፈጣን ምላሽ ለመስጠት መስጠትና መረጃውን ለፌደራል መንግሥት፣ ለብሔራዊ አደጋ እና ስጋት፣ ለሰብአዊ መብት ኮሚሽን እንድሁም ለተራድኦ ድርጅቶች እንድሁም ለሚመለከታቸው ሁሉ እንዲያሳውቅና አስቸኳይ ድጋፍ ልደረግላቸው እንደሚገባ የአደጋው ተጋላጮች ለአፊኒ ገልፀዋል። ፈጣን ምላሽ እንዲሰጣቸው እየጠየቅን እንደየአስፈላጊነቱ በቪዲዮ የተደገፈ መረጃ ይዘን እንቀርባለን።

አፊኒ_ሚዲያና_ኮሙኒኬሽን
#Affini_Media_Communication
ትኩስ እና እውነተኛ መረጃዎችን ለማግኘት ይከታተላሉ
ዩቲዩብ:https://youtube.com/channel/UCzxVCZUtW-XmosukNkCXZEA
telegram:https://t.me/affinimedia
https://t.me/affinihasaaw
388 views04:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 09:33:40
204 views06:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 09:33:14 የቅጥር ማስታወቂያ!!
አዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ከዚህ ቀጥሎ በተዘረዘሩት ክፍት የስራ መደቦች ላይ አመልካቾችን አወዳድሮ በቋሚነት ለመቅጠር ይፈልጋል።
204 views06:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 22:04:45
499 views19:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 22:04:34 አላታ ወንዶ በከተማው የመጀመሪያ የህዝብ መድኃኒት ቤት የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በዛሬው ዕለት አስመርቀዋል ፤
=======================================
አፊኒ ቀን ነሐሴ 16፣2014 ዓ.ም
ሀዋሳ
የአለታ ወንዶ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የረጅም ጊዜ የማህበረሰብ ጥያቄ የሆነውን የመድኃኒት አቅርቦት እና ተደራሽነት ለማረጋገጥ በአጭር የተሰራው ስራ የሚያስመሰግን እንደሆነ ተገልጿል ፡፡ በቋሚነት ይህንን መድኃኒት ቤት ሕዝቡ በባለቤትነት መምራት እንዳለበት አጽዕኖት ተሰጥተዋል ።፡

እንደ ከተማው ከንቲባ ጌዲዎን ጋቢሶ በበኩላቸው አሁን እየተሰሩ ከሚገኙ ስራዎች በተሻለ የህዝቡን ጥያቄ ለመመለስ ሌት ከቀን እንሰራለን ሲሉ መልዕክታቸውን ያስተላለፈው ስሆን ፣ የሆስፒታሉ ስራ-አስኪያጅ አቶ ፍጹም ዳንጉራ ህዝብ መድኃኒት ቤቱን ወደ ስራ ለማስገባት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ለተባበሩ፣ድጋፍ ላደረጉ ሁሉ በተገልጋይ ማህበረሰብ ስም አመስግነዋል ። በመጨረሻም አገልግሎቱ መጀመሩን በማብሰር ፣በሀገር ሽማግሌዎች ተመረቀው በይፋ አግልግሎት ጀምረዋል ።
እንዲህ አይነት መልካም ተሞክሮ በክልሉ በሁሉም አከባቢ መስፋፋት እንዳለባቸውም ተጠቅሷል ።
አፊኒ_ሚዲያና_ኮሙኒኬሽን
#Affini_Media_Communication
ትኩስ እና እውነተኛ መረጃዎችን ለማግኘት ይከታተላሉ
ዩቲዩብ:https://youtube.com/channel/UCzxVCZUtW-XmosukNkCXZEA
telegram:https://t.me/affinimedia
https://t.me/affinihasaaw
454 views19:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-21 09:39:02
464 views06:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-21 09:38:56 በጦርነቱ ጉዳት ከደረሰባቸው 536 የጤና ተቋማት 463ቱ አገልግሎት መስጠት ጀምረዋል፤
=====≡===================
አፊኒ ነሐሴ 16፣2014
ሀዋሳ
በአሸባሪው የሕወሓት ወረራ በአፋርና አማራ ክልሎች ጉዳት ከደረሰባቸው 536 ጤና ተቋማት ውስጥ 463 የሚሆኑት አገልግሎት መስጠት መጀመራቸውን ጤና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

ከዚህ ውስጥ 319 ጤና ተቋማት በከፊል አገልግሎት የጀመሩና ወደ ተሟላ አገልግሎት ለመመለስ ተጨማሪ ሥራ የሚጠይቁ መሆናቸውንም ጠቁሟል፡፡

የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ እንደገለጹት፤ በአሸባሪው የሕወሓት ወረራ በአፋርና አማራ ክልሎች ጉዳት ከደረሰባቸው 536 ጤና ተቋማት ውስጥ 463 የሚሆኑት አገልግሎት መስጠት ጀምረዋል፡፡

ከዚህ ውስጥ 319 ጤና ተቋማት በከፊል አገልግሎት የጀመሩና ወደ ተሟላ አገልግሎት ለመመለስ ተጨማሪ ሥራ የሚጠይቁ መሆናቸውንም አስታውቀዋል፡፡

በሰሜኑ የአገራችን ክፍል በተከሰተው ጦርነት ጉዳት ከደረሰባቸው ተቋማት ውስጥ የጤና ተቋማት ከፍተኛውን ድርሻ ይይዛሉ ያሉት ሚኒስትሯ፤ ለዚህ ምላሽ ለመስጠት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የተለያዩ የድንገተኛ ምላሽ ሥራዎችን ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር ሲሠራ ቆይቷል፡፡
ይህን ለማስተግበር እቅድ ተዘጋጅቶ እንደ ሴክተርና ከሌሎችም ሴክተሮች ጋር በገንዘብ ሚኒስቴር በሚመራ የተጀመሩ የመልሶ ግንባታ ሥራዎች ሲሠሩ መቆየታቸውን ጠቁመዋል፡፡

በአማራ ክልል ከተጎዱት 40 ሆስፒታሎችና 453 ጤና ጣቢያዎች 10 ሆስፒታሎችና 134 ጤና ጣቢያዎች ወደ ሙሉ አገልግሎት መመለሳቸውን ጠቅሰው፤ 25 ሆስፒታሎችና 273 ጤና ጣቢያዎች ደግሞ ከፊል አገልግሎት መስጠት ጀምረዋል ብለዋል፡፡

በተጨማሪም በክልሉ በርካታ ጤና ኬላዎች በመልሶ ግንባታ ወደ ሥራ መግባታቸውን አስታውሰው፤ አምስት ሆስፒታሎች እና 46 ጤና ጣቢያዎች አሁንም ድረስ አገልግሎት መስጠት እንዳልቻሉ አክለው ገልጸዋል፡፡

በአፋር ክልል ጉዳት ከደረሰባቸው ሁለት ሆስፒታሎችና 41 ጤና ጣቢያዎችም አንድ ሆስፒታልና 20 ጤና ጣቢያዎች ታድሰው በከፊል አገልግሎት መጀመራቸውን አመልክተው፤ አንድ ሆስፒታልና 21 ጤና ጣቢያዎች እስካሁን ወደ ሥራ መመለስ አልተቻለም፡፡

በሁለቱም ክልሎች ወደ ሥራ ያልገቡ ቀሪዎችን ተቋማት ወደ ሥራ ለመመለስ የጸጥታ ችግር እንቅፋት መሆኑንም መግለጻቸውን የኢፕድ ዘገባ ያመለክታል፡፡

ከክልል ጤና ቢሮዎች፣ ከፌዴራል ሆስፒታሎች፣ ኤምባሲዎች፣ ከልማት አጋር ድርጅቶች፣ ዳያስፖራዎችና የኢትዮጵያ ወዳጆች በመተባበር በተሠራው ሥራ መሠረታዊና ሕይወት አድን የሆኑ ጤና አገልግሎቶች በግጭቱ በተጎዱ ጤና ተቋማት ውስጥ ማስጀመር ተችሏል ያሉት ዶክተር ሊያ፤ እስካሁን ድረስ ከባለድርሻ አካላት በግብአት፣ በመሳሪያ በገንዘብ 600 ሚሊዮን ብር የሚገመት ሀብት ተሰብስቧል ብለዋል፡፡

እስካሁን ድረስ በግለሰብና ተቋም ደረጃ እገዛ ላደረጉ ባለድርሻ አካላት ምስጋና አቅርበው፤ በርካታ ጤና ተቋማት ወደ ሥራ መመለሳቸው አበረታች ቢሆንም ሁሉም ተቋማት የተሟላ አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ ከፍተኛ ሥራ ስለሚጠይቅ አሁንም ሁሉም ባለድርሻ አካላት ርብርብ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል፡፡
(ኢዜአ)
አፊኒ_ሚዲያና_ኮሙኒኬሽን
#Affini_Media_Communication
ትኩስ እና እውነተኛ መረጃዎችን ለማግኘት ይከታተላሉ
ዩቲዩብ:https://youtube.com/channel/UCzxVCZUtW-XmosukNkCXZEA
telegram:https://t.me/affinimedia
https://t.me/affinihasaaw
427 views06:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ