Get Mystery Box with random crypto!

የነብዩ ☪ሠ,ዐ,ወ☪ ሀዲሶች

የቴሌግራም ቻናል አርማ adnan567mh — የነብዩ ☪ሠ,ዐ,ወ☪ ሀዲሶች
የቴሌግራም ቻናል አርማ adnan567mh — የነብዩ ☪ሠ,ዐ,ወ☪ ሀዲሶች
የሰርጥ አድራሻ: @adnan567mh
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.89K
የሰርጥ መግለጫ

☞ አሊም፣ ሸህ፣ ኡስታዝ፣ ሙፍቲም አይደለሁም፤ ነገር ግን ገና እታች ክፍል ያለሁ
ተማሪ ነኝ።
Telegram የምጠቀመው
«✆አንዲትም መልዕክት ብትሆን ከኔ አድርሱ» የሚለውን ነብያዊ ትዕዛዝ
ለማድረስ ብዮ ነው።
ለአሥተያየት @Adnanmoh_bot
አላህ ይ ቀበለን✔
JOIN 👇
@Adnan567mh
🌐💚💛❤️

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2022-07-09 22:11:49 1)«ዱዓ በምታደርጉ ጊዜ አላህ ዱዓችንን ይቀበለናል ብላችሁ በርሱ ላይ ጥሩ ጥርጣሬን አሳድራችሁ ዱዓ አድርጉ»።
ረሱል (ሶለላሁ ዓለይሂ ወሰለም)
ቡኻሪ ዘግበውታል

2) «አላህ የሆኑ ሰወችን ሲወዳቸው ጊዜ በላእ ያበዛባቸዋል፣ እናም በላእ ሲደርስበት የአላህ ውሳኔ ነው ብሎ አምኖ ወዶ የታገሰ ለርሱ የአላህ ውዴታ አለለት ለተቆጣ ደሞ ቁጣው አለለት»።
ረሱል (ሶለላሁ ዓለይሂ ወሰለም)
ቲርሚዚ ዘግበውታል

3) «አላህ ማስነጠስን ይወዳል ፣ ማፋሸግን ይጠላል»።
ረሱል (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም)
ምንጭ ሶሂሑል በኳሪ 6223
☞ አሊም፣ ሸህ፣ ኡስታዝ፣ ሙፍቲም አይደለሁም፤ ነገር ግን ገና እታች ክፍል ያለሁ
ተማሪ ነኝ።
Telegram የምጠቀመው
«✆አንዲትም መልዕክት ብትሆን ከኔ አድርሱ» የሚለውን ነብያዊ ትዕዛዝ
ለማድረስ ብዮ ነው።
ለአሥተያየት @Adnanmoh_bot
አላህ ይ ቀበለን
JOIN

@Adnan567mh

1.2K views19:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 19:46:43 ዒድ ሙባረክ !!

እንኳን ለ1443 ዒድ አል አድሓ በዓል በሠላም አደረሰን።


(ተቀበለላሁ ሚና ወሚንኩም ሳሊሐል አዕማል)
968 views16:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-06 10:21:00 ወቅታዊ ማስታወሻ ለሙስሊሞች

ውድ ሙስሊም ወንድም ና እህቶች
ይህን ወቅታዊ ማስታወሻዬን ጥቂት ጊዜያችሁን ሰውታቹ እንድታነቡት አደራ አደራ እላለሁ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ አና በጣም አዛኝ በሆነው
ያለንበት ወቅት በ ዱንያ ካሉት ቀናቶች በጣም በላጭ የሆኑ እና አላህ ዘንድ በእነዚህ ቀናቶች የሚሰሩ ስራዎች ከሌሎች በተለየ ና በበለጠ ተወዳጅ የሚሆንበት 10ቱ ቀናት ላይ ነው ያለው

ማስታወሻዬም የሚያተኩረው በእነዚህ ውስጥ በሚገኘው በጣም ታላቅ ና ትሩፋቱ የበዛ ስለሆነው ስለ ዓረፋ
(የዙልሂጃ 9ኛው ቀን) ነው
የአላህ መልዕክተኛ ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም የዚህን ቀን ትሩፋቶች በሚገባ አብራርተዋል

ነብያችን እንዲህ ይላሉ : አላህ ሱ.ወ ከዐረፋ ቀን የበለጠ ባሮቹን ከእሳት ነፃ የሚያወጣበት የሆነ አንድም ቀን የለም
ከዛም በመቀጠል ያሉት :እኔም ከኔም በፊት ከነበሩት ነብያት ካሉት ንግግር በላጩ
لا ﺇﻟﻪَ ﺇﻻَّ ﺍﻟﻠَّﻪ ﻭﺣْﺪﻩُ ﻻَ ﺷَﺮِﻳﻚَ ﻟﻪُ، ﻟَﻪُ ﺍﻟﻤُﻠْﻚُ، ﻭﻟَﻪُ ﺍﻟﺤﻤْﺪُ، ﻭَﻫُﻮ ﻋَﻠَﻰ ﻛُﻞِّ
ﺷَﻲﺀٍ ﻗَﺪِﻳﺮ
ላ ኢላሃ ኢሏሁ ወሕደሁ ላ ሸሪከ ለሁ ለሁል ሙልኩ ወለሁል ሐምዱ ወሁወ አላ ኩሊ ሸይኢን ቀዲር የሚለው ነው::
ይህን ዚክር በብዛት በማለት እንበርታ
ሌላው ነብያችን እንዲህ ብለዋል
በላጬ ዱዓ ማለት የዓረፋ ቀን የሚደረግ ዱዓ ነው

በዚህ በላጭ በሆነው የዓረፋ(ዙልሂጃ 9) ቀን አላህ ሱ.ወ
-ከእሳት ነፃ ከሚያደርጋቸው
-ወንጀላቸው ከሚማርላቸው ባሮቹ መሆን የፈለገ ሰው
የዓረፋን ቀን ይፁም
ነብያችን እንዲህ ይላሉ :
{የዐረፋ ቀን በመፆም አላህ ያለፈውንና የሚመጣውን አመት ወንጀል እንደ ሚምር እተሳሰባለሁ}
{የዐረፋ ቀን የፆመ የሆነ ሰው ተከታታይ የሆኑ የሁለት አመት ወንጀሎቹን ይማርለታል}
የተውሂድ ቃል ዚክር ማለትን ያብዛ
ላ ኢላሃ ኢሏሁ ወሕደሁ ላ ሸሪከ ለሁ ለሁል ሙልኩ ወለሁል ሐምዱ ወሁወ አላ ኩሊ ሸይኢን ቀዲር
አላህ እንዲምረው እና ከእሳት ነፃ ከሚሆነው እንዲያደርገው መለመንን ያብዛ
አሏሁመ አእቲቅ ሪቃበና ሚነን ናር የምትለዋን ዱዓ በማለት አላህን እንለምን
በዚህ ቀን ዱኣ ተቀባይ መሆኑ በጣም የሚከጀልበት ነው
ለዚህም ቀን ኸይር ፈላጊ የሆነ
ሙስሊም ራሱን ባለቤቱን እህት ወንድሞቹንና ልጆቹን ይህንን የተከበረ ቀን እንዲፆሙ ይቀሰቅሳል
አላህ ሱ.ወ የዚህን ቀን ትሩፋቶች ከሚያገኙ እና ወንጀላቸው ከሚማርላቸው ሰዎች እንዲያደርገን እለምነዋለሁ በመልካም ዱዓቹ አትርሱኝ

ይህን አንገብጋቢ ማስታወሻ ለምታውቁትም ለማታውቁትም ሙስሊም ለሆነ አካል እንድታሰራጬ እና የመልካም ስራ ተቋዳሽ እንድትሆኑ እጠይቃለሁ اح
149 views07:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-04 13:33:23 ዘላለም አትኖርም /አትኖሪም
ሞት አለ ወዳጄ

.....አንዳንዴ ጉዳይ አለኝ ብለህ እየተጣደፍክ ምትሄድበት ቦታ ላይ የሞት ቀጠሮህ እዛ ልሆን ይችላል ።
《عن أبي عزة يسار بن عبد الله الهذلي، عن النبي ﷺ قال: إن الله إذا أراد قبض عبد بأرض، جعل له بها، أو فيها حاجة》
የአላህ መልእክተኛ ሰላትና ሰላም በሳቸው ላይ ይሁንና እንዲህ አሉ ፦
{አላህ ሱብሀነሁወተአላ ለአንድ ባሪያ የሆነ ቦታ ላይ ሩሁ እንዲወጣ ሲፈልግ እዛ ቦታ ወይም በዛ ቦታ ውስጥ የሆነ ጉዳይ ያደርግለታል።}}
أخرجه أحمد، والترمذي، وابن حبان

ሀቂቃ እውነታው በጣም ይገርማል
ስንቱ ነው እዛ ቦታ ላይ ጉዳዬን ፈፅሜ መጣሁ ብሎ በሰላም ይወጣል ከትንሽ ሰአት በኋላ የሞት መርዶው ይሰማል

ስንቱ ነው ሀጃውን ፈፅሞ ልክ እቤቱ ጫፍ ሲደርስ ባላሰበው አደጋ ህይወቱ የሚቀጨው

ስንቱ ነው ተውቦ ተጊጦ ለጉዳዩ ሲጣደፍ ቀጠሮው ደርሶ ባላሰበው አደጋ በደም ተነክሮ ሚመለሰው!

.... ይህም የሆነበት ምክንያት ማንኛውም ሰው የሚሞትበት ቦታና ሰአት ስለማያውቅ ነው። አላህ እንዳናውቀው ከሩቅ ሚስጥር ካደረጋቸው ጉዳዮች ውስጥ አንዱ ስለሆነ ነው። ለምን ከተባለ፦
ገና ወጣት ነኝ አሁን አልሞትም
ሙሉ ጤነኛ ነኝ ሞት አያገኘኝም ሳንል በሁሉም ሰአትና ቦታ ሆነን ሞት በድንገት ባላሰብነው ሰአትና ሁኔታ ሊመጣ ስለሚችል በዝግጅት ላይ ሆነን እንድንጠብቀው ነው።
ስንቱ ወጣት ነው ገና በለጋ እድሜው ዱንያን የተሰናበተው
ስንቱ ጀግና ነኝ ማን አለብኝ ሲል የነበረው ሁሉ ሳያስበው በድንገት ቀብር የገባው
ስንቱ ተመራቂ በምረቃው ቀን፣ ስንቱ ወጣት በሚሞሸርበት ቀን፣ ስንቱ ተስፈኛ ተስፋው በሚሳካበት ቀን ሳያስቡት አፈር ስር የገቡት
አስተውል ሌላው ቢቀር ወይ እናት፣ ወይ አባት፣ ወይ አጎት፣ ወይ ልጅ፣ ወይ እህት፣ ወይ አያት ሳትቀብር አትቀርምና በነሱ ትምህርት ውሰድ
እነሱም እንዳንተው ገና አግብተው ወልደው፣ ሀብታም ሆነው፣ ከብረው ተከብረው፣ ወግ ማእረግ አይተው፣ ደና ቤት መኪና ገዝተው የመኖር ህልም ነበራቸው። ኑሮን አሸንፈው ስኬታማ መሆን ይፈልጉ ነበር። ነገር ግን አልሆነም ቀጠሮው ደርሶ ወደ ማይቀረው አለም ሄዱ። ነገ ያንተም ተራ እንደሚደርስ አትዘንጋ።
ግን በጣም ሚገርመው እነሱ ጥለውት በሄዱት በዚህ ዱንያ ተታለን ሞትን መርሳታችን ነው። ለዱንያ ብለው ከፊሉን ከፊሉን መግደሉንና መጨካከናችን ነው። የሸይጧንና የነፍስያችን ባሪያ መሆናችንን ነው። በወንጀል ባህር ሰምጠን ያለ እስቲግፋርና ያለፀፀት በዚሁ አመፅ ላይ ህይወታችን መግፋታችን ነው። ሀቂቃ የብዙዎቻችን ሁኔታ ሲታይ ሞት የለም ዘላለም ነው ምትኖረው የተባልን ወይም አብሽር ጀነት ላይ ቦታ ተይዞልሀልና ዘና በል የተባልን ነው ሚመስለው

ወዳጄ
የቀብር ጨለማ እንዳያገኝህ፣ የሲራጥ ሜንጦ እንዳይቧጥጥህ፣ ኪታብ በቀኝ እጅ እንዲሰጥህ፣ ጀነት በሰላም ግባ አትጨነቅ አትፍራ ትባል ዘንድ በመልካም ስራ በመበርታትና ከመጥፎ ስራ በመቶበት ወደፊት ቀጥልበት
https://t.me/Adnan567mh
377 views10:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-30 16:41:05 ማሳሰቢያ ዙል_ሒጃ ለምትፆሙ


አንድ ሰው የሚሰራው ዒባዳ የተስተካከለና የተሟላ ይሆንለት ዘንድ የዒባዳው ሁክምና ስርዓት ማወቅ ይኖርበታል። ዒባዳው ዋጂብ ይሁን፣ ሱና ይሁን፣ ተወዳጅ ይሁን ሁክሙን ማወቅ አለበት። ይህ ካልሆነ ግን ለምሳሌ ሱና ያልሆነን ዒባዳ "ሱና ነው" ብሎ የሚሰራ ከሆነ ሰውየው ሳያውቀው ቢድዓ ላይ ሊወድቅ ይችላል።

በዚህም መሰረት;
የዙል_ሒጃ 8 ቀናቶች የሚፆም የሆነ ሰው ፆሙ እንደ የትኛውም መልካም ስራ (ዒባዳ) "መልካም ስራ ነው" ብሎ መፆም አለበት እንጂ "እነዚህ ቀናቶች መፆም ሱና ነው።" ብሎ መፆም የለበትም።

ምክንያቱም;
የአላህ መልእክተኛ ﷺ በእነዚህ ቀናቶች የሚሰሩ ዒባዳዎች በላጭነት እንዳላቸው ነግረው አነሳሱን እንጂ ለየት ባለ መልኩ "በእነዚህ ቀናቶች መፆም ሱና ነው።" ብለው አላስተማሩንም። ስለዚህ የምትፆሙ የሆናችሁ ወንድም እህቶች ይህንን ግንዛቤ መያዝና መረዳት ይኖርባችኋል።

NB
"ስምንቱ ቀናቶች" የተባለው፦
ዘጠነኛው ቀን (የዓረፋ ቀን) መፆሙ ግልፅና ትልቅ የሆነ ሱና ነው
አስረኛው ቀን (የእርድ ቀን) ዒድ ነውና መፆም አይፈቀድም
☞ አሊም፣ ሸህ፣ ኡስታዝ፣ ሙፍቲም አይደለሁም፤ ነገር ግን ገና እታች ክፍል ያለሁ
ተማሪ ነኝ።
Telegram የምጠቀመው
«✆አንዲትም መልዕክት ብትሆን ከኔ አድርሱ» የሚለውን ነብያዊ ትዕዛዝ
ለማድረስ ብዮ ነው።
ለአሥተያየት @Adnanmoh_bot
አላህ ይ ቀበለን
JOIN

@Adnan567mh

477 views13:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-30 13:14:54 Channel photo updated
10:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-30 13:10:03 የዱንያ በላጭ ቀናቶች


ሁለት ወይም አንድ ቀን ብቻ ቀርተውታል

"ከዱንያ ቀናቶች ሁሉ በላጭ" የተባሉ የ ዙል—ሒጃ አስርቱ ቀናቶች ሊገቡ በር በማንኳኳት ላይ ናቸው።

የአላህ መልዕክተኛ ﷺ በሓዲሳቸው እንዲህ ይላሉ፦
«أَفْضَلُ أَيَّامِ الْدُّنْيَا أَيَّامُ الْعَشْرِ، يَعْنِي عَشْرُ ذِي الحْجَّةِ»
«ከዱንያ ቀናቶች ሁሉ በላጭ ቀናቶች አስርቱ ቀናቶች ናቸው። =>የዙል_ሒጃ አስር ቀናቶች»

በሌላም ሓዲስ እንዲህ በማለት በእነዚህ ቀናቶች የሚሰራ ስራ ያለውን ደረጃ ያስቀምጣሉ፦
«ما من أيام العمل الصالح فيهن أحب إلى الله من هذه الأيام العشر،
قالوا ولا الجهاد في سبيل الله؟ قال
ولا الجهاد في سبيل الله، إلاّ رجلا خرج بنفسه وماله فلم يرجع من ذلك بشيء»
«ከእነዚህ ከአስር ቀናቶች የበለጠ መልካም ስራ ወደ አላህ የሚወደድበት ቀን የለም አሉ።
ሰሓቦችም
በአላህ መንገድ ላይ መታገል (መጋደል) ቢሆንም? ብለው ሲጠይቋቸው
አዎን! በአላህ መንገድ መታገል ቢሆንም; ግን አንድ ሰው ሲቀር አሉ
እሱም በአላህ መንገድ ለመታገል ነፍሱንም ንብረቱንም ይዞ ወጥቶ እስከ ንብረቱ እዛው የቀረ አሉ።»

እናንተ ሙስሊሞች ሆይ! እነዚህ ቀናቶች ናቸው እንግዲህ ከፊት ለፊታችን እየመጡ ያሉት።
እንግዲያውስ ለራሱ የሚጨነቅና ንቃተ ህሊና ያለው የሆነ ሰው እንዲህ ዓይነት ብርቅዬ አጋጣሚዎች በከንቱ አያሳልፋቸውም።

እኛንም አላህ ደርሰው ከሚጠቀሙ ያድርገንና ለእነዚህ ቀናቶች አላህ ካደረሰን ከዚህ በፊት ስናደርገው ከነበረው ለየት ባለ መልኩ ለመስራትና ለመጠቀም ራሳችንን ካሁኑ እናዘጋጅ


አላህን አብዝተን በማውሳት
ተህሊል
ተክቢር
ተስቢህ እና
ተህሚድ በማድረግ

ሰደቃን በማብዛት
ቁርኣን አብዝተን በማንበብ
አላህን አብዝተን በመለመን
የጀምዐ ሰላትን በመጠባበቅ

ተጨማሪ(ሱና) የሆኑ ሰላቶችን በመስገድ
የቻልነውን በመፆምእና
አጠቃላይ ኸይር ከተባለ ነገር ሰብስበን ተጠቃሚ ለመሆን ካሁኑ ልንዘጋጅ ይገባናል

ኢብኑ ዑሰይሚን አላህ ይዘንላቸው እንዳሉት፦
"ብዙሀን ሰዎች የሚገርሙ ናቸው ከረመዷን አሽረል አዋሂር ላይ የቻሉትን ያህል እየታገሉና እየሰሩ ይታያሉ ዙል_ሒጃ ላይ ግን ምንም የተለየ ነገር ሲያከናውኑ አይታዩም።"

ከፊል ዑለማዎች ከረመዷን አሽረል አዋሂር የዙል_ሒጃ አስር ቀናቶች እንደ ሚያስበልጡስ ስንቶቻችን እናቃለን

ምንም እንኳ መስዐላው ሸይኹል ኢስላም ኢብኑል ቀይም እንዳስቀመጡት
«ከለሊቶቻቸው አንፃር የረመዷን አሽረል አዋሂር ሲበልጡ፤
ከቀኖቻቸው አንፃር የዙል_ሒጃ አስር ቀናቶች የሚበልጡ ቢሆንም።

ማለት የፈለኩት ግን
ምን አልባት አላህ በዚህኛው ካደረሰን በቀጣዩ ዓመት ላንደርስበት እንችላለን
ብዙኃን ለአምናው ደርሰው ለዘንድሮው መድረስ እንደ ተሳናቸው
እናም; አላህ ካደረሰን እድሉን ሳንጠቀምበት ሊያልፈን አይገባም።

ማሳሰቢያ
በመጨረሻም ዙል_ቂዕዳ አልቆ ዙል_ሒጃ ሊገባ የተዳረሰ በመሆኑ
ለዒደል_አድሀ ኡዱህያ ማድረግ የሚፈልግ ሰው ካሁኑኑ ዝግጅቱን መርሳት የለበትም

ምክንያቱም ዙል_ሒጃ ከገባ ከፀጉሩና ከጥፍሩ መንካት ስለ ማይፈቀድለት መጨረስ ያለበት ጣጣው ካሁኑ መጨረስ አለበት።

ልክ መልዕክተኛው እንዳሉት
«فأراد أحدكم أن يضحي فلا يأخذن من شعره ولا من بشرته ولا من ظفره شيئا»
«ከእናንተ አንዳቹ ኡዱህያ ለማድረግ ከፈለገ ከፀጉሩም ይሁን ከጥፍሩ ምንም እንዳይነካ (እንዳይቆርጥ)»

አላህ ሚጠቅመንን ያሳውቀን ባወቅነውም ያስጠቅመን
☞ አሊም፣ ሸህ፣ ኡስታዝ፣ ሙፍቲም አይደለሁም፤ ነገር ግን ገና እታች ክፍል ያለሁ
ተማሪ ነኝ።
Telegram የምጠቀመው
«✆አንዲትም መልዕክት ብትሆን ከኔ አድርሱ» የሚለውን ነብያዊ ትዕዛዝ
ለማድረስ ብዮ ነው።
ለአሥተያየት @Adnanmoh_bot
አላህ ይ ቀበለን
JOIN

@Adnan567mh

393 views10:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-27 16:20:36 የአላህ መልእክተኛ ሶለሏሁ ዓለይሂ ወሰለም ሁል ግዜ ከፈጁር በኋላ የሚሉት ዱኣ…

ﺍﻟﻠﻬﻢ ﺇﻧﻲ ﺃﺳﺄﻟﻚ ﻋﻠﻤﺎ ﻧﺎﻓﻌﺎ، ﻭﺭﺯﻗﺎ ﻃﻴﺒﺎ،ﻭﻋﻤﻼ ﻣﺘﻘﺒﻼ
ትርጉም

ጌታየ ሆይ … ጠቃሚ እውቀትን፣ መልካም የሆነ ሪዝቅን(ሲሳይን)፣ ተቀባይነት ያለውን ስራ…እጠይቅሃለሁ።

(ኢብኑማጃ ዘግቦታል።
☞ አሊም፣ ሸህ፣ ኡስታዝ፣ ሙፍቲም አይደለሁም፤ ነገር ግን ገና እታች ክፍል ያለሁ
ተማሪ ነኝ።
Telegram የምጠቀመው
«✆አንዲትም መልዕክት ብትሆን ከኔ አድርሱ» የሚለውን ነብያዊ ትዕዛዝ
ለማድረስ ብዮ ነው።
ለአሥተያየት @Adnanmoh_bot
አላህ ይ ቀበለን
JOIN

@Adnan567mh

430 views13:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-27 16:11:29 Live stream started
13:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-22 14:35:08 #ሱረቱ አል-ፋቲሀ..........የአላህን ቁጣ
ትከላከላለች::

#ሱረቱ ያሲን .........ከቂያማ ቀን ጥማት
ትከላከላለች::

#ሱረቱ አል-ዱኻን..........ከቂያማ ቀን ጭንቀት
ትከላከላለች::

#ሱረቱ አል-ሙልክ..........ከቀብር ቅጣት
ትከላከላለች::

#ሱረቱ አል-ካፊሩን..........በሞት ሰአት ከኩፍር
ትከላከላለች::

#ሱረቱ አል ኢኽላስ..........ከኒፋቅነት
ትከላከላለች::

#ሱረቱ አል-ፈለቅ..........ከምቀኝነት
ትከላከላለች::

☞ አሊም፣ ሸህ፣ ኡስታዝ፣ ሙፍቲም አይደለሁም፤ ነገር ግን ገና እታች ክፍል ያለሁ
ተማሪ ነኝ።
Telegram የምጠቀመው
«✆አንዲትም መልዕክት ብትሆን ከኔ አድርሱ» የሚለውን ነብያዊ ትዕዛዝ
ለማድረስ ብዮ ነው።
ለአሥተያየት @Adnanmoh_bot
አላህ ይ ቀበለን
JOIN

@Adnan567mh

628 views11:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ