Get Mystery Box with random crypto!

የኡስታዝ አቡ ሀይደር ትምህርቶች ስብስብ

የቴሌግራም ቻናል አርማ abuhyder — የኡስታዝ አቡ ሀይደር ትምህርቶች ስብስብ
የቴሌግራም ቻናል አርማ abuhyder — የኡስታዝ አቡ ሀይደር ትምህርቶች ስብስብ
የሰርጥ አድራሻ: @abuhyder
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 17.46K
የሰርጥ መግለጫ

ኡስታዝ አቡ ሀይደር በፌስቡክ ያስተማራቸው የኦዲዮ የጹሁፍ እና የቪዲዮ ትምህርቶች ተሰባስበው የሚገኙበት ቻናል ነው።

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2023-01-03 20:33:09
1.3K views17:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-16 15:15:38
3.0K views12:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-16 15:15:22 የትብብር ጥያቄ

270,000 ብር ብቻ

''እኛ መስማት የተሳናቸው ሙስሊሞች ዙርያ የምንሰራ ኢማን የኢትዮጵያ መስማት የተሳናቸው ልማት ድርጅት እንባላለን። ከማህበራት ማደራጃ ፍቃድ ያለን ህጋዊ ተቋም ነን።

ህዳር 19 ላይ አለም አቀፍ የመስማት የተሳናቸው ሙስሊሞች ኮንፈረንስ ጋምቢያ ላይ እንድንሳተፍ የጥሪ ደብዳቤ ተልኮልናለን። ስብሰባው ለመላው ኢትዮጵያዊ ሙስሊም መስማት የተሳናው ይጠቅማል ብለንም እናምናለን። ግን አሁን እኛ የደርሶ መልስ የአየር ጉዞ ቲኬት ለመክፈል አቅሙ የለንም። የምንሄደው 3 ሰዎች ነን።

ለያንዳንዳችን ከ80 እስከ 90ሺህ ብር ወይም ለ3ታችን 270ሺህ ብር ገደማ ይጠበቅብናል። የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት የትብብር ደብዳቤ ፅፎልናል። እባካችሁ በኮንፈረንሱ ላይ እንድንሳተፍ ለአላህ ብላቹ ተባበሩን ይላሉ'' መልዕክታቸው።

ሁላችንም ብንተባበራቸው ቀላል ገንዘብ ናት። መስማት የተሳናቸውን፣ አይነ ስውራንን የመሳሰሉ ወገኖቻችንን በእምነታቸው እንዲጠነክሩ ማገዝ የሁላችንም ግዴታ ነው።

ከታች ባሉ አካውንቶች ድጋፍ በማድረግ እናግዛቸው።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት
1000461347936
IMAN ETHIO DEAF DEVT ORGA (IEDDO)

ሒጅራ ባንክ
1002450020001
IMAN ETHIO DEAF DEVT ORGA (IEDDO)

ዘምዘም ባንክ
0009389910301
IMAN ETHIO DEAF DEVT ORGAN
3.0K views12:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-20 15:35:37
የምስራች
...
ማዕከላችን ሒዳያ ኢስላማዊ ማዕከል በአሏህ ﷻ እገዛ ከዚያም በታች በብርቱ ወንድሞችና እህቶች ጥረት ህጋዊ ሒደቱን አጠናቆ በይፋ ስራዎችን ጀምሯል። በሀገራችን እየተንሰራፋ የሚገኘውን የአክፍሮተ ሀይላት እንቅስቃሴ በዳዕዋ ለመመከትና እስልምና ያልደረሰባቸው አካባቢዎች ሪሳላውን ለማስፋት ትኩረት አድርጎ የሚሰራው ማዕከላችን ስራውን በተጠናከረ መልኩ ለመስራት ጉዞውን በአሏህ ﷻ ፍቃድ ጀምሯል።
...
በተጨማሪም የበጎ አድራጎት ስራዎች የሚያስፈልግባቸው አካባቢዎች ላይ ስራዎችን ለመስራት ራሱን የቻለ ህጋዊ የበጎ አድራጎት ፍቃድ ያለው ሲሆን በተለያዩ ቦታዎች በወገኖቻችን ላይ ለሚደርሱ እምነት ፈታኝ መከራዎች በተቻለው መጠን ለመስራት እንቅስቃሴውን ጀምሯል። የማዕከላችን አባል በመሆን በጉልበት እንዲሁም በገንዘብ የአቅማችሁን መደገፍ ለምትፈልጉ ከዚህ በታች ባለው የጎግል ፎርም አባል እንድትሆኑ እየጠየቅን በቀጥታ ለመደገፍ ከዚህ በታች ያለውን የማዕከሉ ኦፊሺያል አካውንት መጠቀም ትችላላችሁ።

አካውንት - 1000499318212
የአካውንት ስም - Hidaya Islamic Center
በአጭር ቁጥር - 8212 መጠቀም ይችላሉ።
____
በተሰማሩበት መስክ የሒዳያ ኢስላማዊ ማዕከል አባል በመኾን ዳዕዋውን ማገዝ ከፈለጉ በሚከተለው ማስፈንጠሪያ የአባልነት ቅፅ በመሙላት ሊቀላቀሉን ይችላሉ፦

https://bit.ly/3r7DhoY
2.9K views12:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 16:29:45 ◉ ይህ▸

የኡስታዝ ኢልያህ ማሕሙድ ይፋዊ የዩቲዩብ ቻናል ነው። የተለያዩ ኢስላማዊ እና ንፅፅራዊ ትምህርቶች የሚለቀቁበት ብቸኛው ገጹ ስለሆነ Subscribe/Like/Share በማድረግ ዳዕዋውን ለወገኖቻችን በፍጥነት ያድርሱ።

Ustaz Eliyah Mahmoud Telegram Channel.
1.6K views13:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 15:04:14
3.4K views12:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 15:04:07 እህታችን በብድር ተይዛ ተጨንቃለች፣ከእዳ ብድር ጭንቀት አላህ ይጠብቃችሁ ፣የቻልነውን ያህል እንተባበራት እህታችን እንዲህ ትላለች

አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱሁ
የአላህ እዝነትና ቸርነት በናንተ በወገኖቼ ላይ ይሁን እኔ እህታቹ ወ/ሮ ሀናን ጀማል በጓደኞቼ እና ባመንኩዋቸው የስራ ባልደረቦቼ የደረሰብኝን መከዳትና መጭበርበር ስገልፅላችሁ አላህ ከእንደዚህ አይነት ነገር እንዲጠብቃችሁ በመመኘት ጭምር ነዉ
ወገኖቼ ያዋጣኛል ነገ ህይወቴን ይቀይርልኛል ብዬ አስቤ ከብዙ ሰዎች ላይ ተበድሬ የሰጠዃቸዉን 3,200,000 (ሶስት ሚሊየን ሁለት መቶ ሺህ) ብር ይዘዉብኝ ተሰዉረዋል አበዳሪዎቼ ደግሞ ወደ ክስ ሄደዉ ከ አንዴም ሁለቴ ታስሬ አሁን ላይ በዋስ ወጥቼ በፍጥነት አምጥቼ እንድከፍል አ ስጠንቅቀዉኛል አሁን ላይ ደሞ የ 7 ወር ነብሰ ጡር ነኝ በዛ ላይ ደግሞ ታምሚያለሁ በዚህ ሰአት ደሞ ይሄንን ገንዘብ የመክፈል አቅም የለኝም ይሄን ገንዘብ ካልከፈልኩ ደሞ በድጋሚ ለእስር እንደምዳረግ አስጠንቅቀውኛል:: ውድ ወገኖቼ እንደኔ ካልታሰበ ኪሳራ እና ችግር አላህ ይጠብቃችሁ እያልኩ እዳዬን እንድከፍል የበኩላችሁን ታደርጉልኝ ዘንድበ አላህ ስም እጠይቃችሁአለዉ
የባንክ አካዉንት Nigd bank 1000491549916 ሀናን ጀማል ሽፋ
abysinya 88569048 ሀናን ጀማል ሽፋ
Awash 01425589998100 ሀናን ጀማል ሽፋ
4.3K views12:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-23 12:32:47 የዱራሜው መስጂድ ቢላል ጉዳይ ከምን ደረሰ?

በአቡ ሀይደር

በአላህ ሥም እጅግ በጣም ሩህሩኅ በጣም አዛኝ በሆነው

ከሁሉ በፊት አማኝ ባሪያዎቹን በማነሳሳትና በማገዝ: ከፊሉ በገንዘቡ፣ ከፊሉ በዕውቀቱ፣ ከፊሉ በማስተዋወቅና የተቀረው ደግሞ በቦታው ላይ በመሳተፍ ለመስጂዱ ህልውና አስተዋጽኦ እንዲያደርግ: ተውፊቁ (እገዛው) ላልተለየን ጌታ አላህ ምስጋና ይድረሰው። ያለሱ እገዛና ፈቃድ ምንም ነገር ሊከሰት አይችልምና።

በመቀጠልም: የዱራሜው ቢላል መስጂድ ሁኔታ፤ ሙአዚንና ኢማም በሆኑት ሰውዬ ብቻ ሶላት መከናወኑ: እረፍት የነሳው ወንድማችን የ Islam Selam አካውንት እና የዚህ ዩቱብ https://youtube.com/channel/UC1phBbwcq_sXeSKKV_JtUMg ባለቤት ጉዳዩን በፌቡ በመልቀቅ ለሙስሊሞች መነሳሳት ሰበብ ስለሆንከን ጀዛከላሁ ኸይራ።

በመሰለስም: ይህ ጉዳይ ለሁሉም ወንድምና እሕቶች በሰፊው እንዲዳረስና ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል በተደጋጋሚ በመፖሰት ሰፊ ተደራሽነት እንዲኖረው ለለፋኸው ወንድም አቡ ዳዉድ ዑሥማን ጀዛከላሁ ኸይራ።

በመረበዕም:– በተለያዩ የሶሻል ሚዲያዊች (በፌቡ፣ በቴሌግራም፣ በዋትስአፕ፣ በቲክቶክና በዩቱብ) ስርጭቱ እንዲስፋፋ ላደረጋችሁ ወንድምና እሕቶች በመላ ጀዛኩሙላሁ ኸይራ።

በመጨረሻም:– በሀገር ውስጥም ከሀገር ውጭም በመሆን ይህ የዱራሜው ቢላል መስጂድ ጉዳይ የኔ ጉዳይ ነው በማለት በገንዘባቹ የተሳተፋችሁ ወንድምና እሕቶች: ገንዘብና ልጆች በማይጠቅሙበት ቀን አላህ ባወጣችሁት ገንዘብ ተጠቃሚ ያድርጋችሁ።

እንዲሁም ቦታው ድረስ በመገኘት ለተሰበሰበው ሕዝብ ኢስላማዊ ትምሕርት የሰጣችሁ (ኡስታዝ ዐብዲ፣ ኡስታዝ ጁንዱላህ፣ ኡስታዝ መሐመድ ሸምሱ)፣ በቦታው በመገኘት የፕሮግራሙ ድምቀት የሆናችሁ ተሳታፊዎች በሙሉ (በተለይ የሐላባ ጀመዓዎች)፣ ቦታውን በማበጃጀት ላስተካከላችሁ በመላ (በተለይ ወንድም ሱልጣን ናሲር፣ ወንድም መሐመድ ኢብራሂም እና ወንድም ፉአድ) ጀዛኩሙላሁ ኸይራ።

አዲስ ነገር ምን ተሰራ ምንስ ቀረ?

1/ በመስጂዱ ላይ ሙአዚን እና ኢማም ከነበሩት አባት በተጨማሪ: ለመስጂዱ ቋሚ ኢማም (በመግሪብ፣ ዒሻእና ፈጅር ላይ አሰጋጅ) ተመድቧል። ይህ ኢማም ከኢማምነት በተጨማሪ:– የአካባቢውን ህፃናት ቁርኣን ማስቀራት፣ ከመግሪብ እስከ ዒሻእ ለመጣው ሰው ቋሚ የሙሐደራ ፕሮግራም መስጠት፣ በግላቸው የተለያየ ኪታብ መቅራት የሚፈልጉ ወንድሞችን ማቅራት ሥራው ይሆናል።

2/ ቅዳሜና እሕዱ (ከ 14/12/14—15/12/14) ለሁለት ቀናት በመስጂዱ ላይ ለተሰበሰበው ህዝብ ኢስላማዊ ት/ት መስጠት። በዳዕዋው ሰበብም ወደ 9 ሰዎች ሸሀዳ በመስጠት ሰልመዋል። ለተሰበሰበው ሰውም በሁለቱ ቀናት የምሳ ግብዣ ፕሮግራም ተካሂዷል።

3/ የመስጂዱ ውስጣዊ ችግር (ኮርኒስ) እደሳ ተካሂዷል።

በአሁን ሰአት ከአዲሱ ኢማም በደረሰኝ መረጃ መሰረት ከ10 እስከ 15 የሚደርሱ ሰዎች ወደ መስጂዱ በመመላለስ የጀመዓ ሶላት እንደሚሰግዱ ማወቅ ተችሏል። ቁርኣን መማር የጀመሩ ህፃናትም (ወንድና ሴትን ጨምሮ) ወደ 15 ደርሰዋል።
የቀረው ሥራ ደግሞ:– መስጂዱን ዙሪያውን ማጠር: በሶስት ወይም በየ አራት ወራት በመስጂዱ ላይ የዳዕዋ ፕሮግራሞችን ማዘጋጀት።

ምን ያህል ገንዘብ ተሰበሰበ? ምን ያህልስ ወጪ ተደረገ?

የተሰበሰበው ገንዘብ ከገመትነውና ከጠበቅነው በላይ ነው። በአጠቃላይ እስካሁኑ ሰአት ድረስ የተሰበሰበው ገንዘብ 2,585,113·32 ሳ (ሁለት ሚሊየን አምስት መቶ ሰማንያ አምስት ሺህ፣ አንድ መቶ አሥራ ሶስት ብር ከሰላሳ ሁለት ሳንቲም) ነው።

ወጪ የተደረገው ደግሞ:– 242,997 ብር ነው። ከወጪ ቀሪ የሚሆነው:– 2,342,116·32 ሳ ይሆናል።

በቀጣይ ምን ታሰበ?

ይህ የተሰበሰበው ገንዘብ ለቢላል መስጂድ ሙአዚን እና ኢማም እንዲሁም ኡስታዝ ለሆኑት በተጨማሪም ለአጥር ግንባታው ከሚያስፈልገው በላይ የተረፈ በመሆኑ: ይህ የተረፈ ገንዘብ ለሌላ ኸይር ሥራ እንዲውል:–

1/ በዋንኝት በአካባቢው የሚገኘውን የካምፓሱ ሙስሊም ተማሪዎችን ማገዝ። የዱራሜ ካምፓስ ሙስሊም ተማሪዎች ከካምፓሱ ፊትለፊት ወደ ውስጥ ገባ ብሎ የሰሩትን መስጂድ ጎብኝቼዋለሁ። መስጂዱ ቀሪ ሥራዎች (በተለይ በሴቶች በኩል ምንጣፍ፣ በርና መስኮት እንዲሁም ችፑድና መፀዳጃ ቤት)፣ መድረሳው ሙሉ እድሳት ያስፈልጉታል። እንደተነገረኝ ከሆነ ወደዚህ መስጂድ በመመላለስ የሚሰግዱ ወንድምና እሕቶች ወደ 300 ይጠጋሉ። ስለዚህ እነዚህ ሰጋጆች: ከሶላት በተጨማሪ መንፈሳዊ ማንነታቸውን የሚያጠናክርላቸው ሁለት ኡስታዞችን መቅጠር ያስፈልጋል።

2/ በዛው ዱራሜ ከተማ: ከቢላል መስጂድ ራቅ ብሎ በገጠራማው ክፍል ለሚገኙ ሙስሊም ነዋሪዎች የኡስታዝ እጥረት ያለባቸውን ቦታዎች ጥናት በማድረግ ኡስታዞችን መቅጠር ዋነኛ ስራችን ይሆናል።

3/ ገንዘቡ የሚተርፍ ከሆነ ከሀላባ ከተማ ወደ ከንባታ በሚወስደው መንገድ 12 ኪ ሜ ርቃ የምትገኘውን የአቦኪቾ ከተማ በኡስታዞችና በዳዕዋ መድረስ ሌላው ስራችን ይሆናል። ይህ ከተማ ከ1000–1,500 የሚደርሱ አባወራዎች አሉት። 85 በመቶ የሚሆነው ሙስሊም ነው። ያሉት መስጂዶች ብዛት በጭቃ የተሰሩ 3 ብቻ ናቸው። መደረሳ ማፊ፣ ኡስታዝ ማፊ!! ስለዚህ ቦታው የኡስታዝና የመድረሳ ትኩረት ይሻል።

ወንድምና እሕቶቼ ሆይ!

ይህ የኸይር ሥራ ቀጣይነት እንዲኖረው የናንተን እገዛ ይሻልና: በቻላችሁት መጠን አሁንም ከመተባበር ወደ ኋላ አትበሉ። አላህ ያግዛችሁ ወሰላሙ ዐለይኩም ወራሕመቱላሂ ወበረካቱሁ
6.1K views09:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-03 21:01:01
9.4K views18:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-03 21:00:48 አስቸኳይ የድጋፍ ጥሪ

በሰጋጆች ድርቅ የተመታውን የዱራሜውን ቢላል መስጂድ ሁላችንም ለመታደግ እንረባረብ

አቡ ዳውድ ኡስማን

መዕክቱን አንብበው ሲጨርሱ ለሌሎችም ሼር ያድርጉት

በደቡብ ክልል በከምባታ ጠምባሮ ዞን በዱራሜ ከተማ በካሻ ቀበሌ አሮጌ ሰፈር የሚገኘው ቢላል መስጂድ አካባቢው የነበሩ ሙስሊሞች እንዲሁም የመስጂዱ ኢማም ሚስታቸው እና ልጃቸው ሳይቀር ከፍረው የመስጁዱ ሙዓዚን እና ኢማም የሆኑት ሼይኽ መሐመድ ኑር ብቻቸውን በመስጂዱ እየሰገዱ እንደሚገኙ መገለፁ ይታወሳል::

በዚህ ትልቅ መስጂድ ውስጥ ብቻቸውን አዛን እያወጡ ብቻቸውን ኢቃም ብለው እንደሚሰግዱ መገለፁን ተከትሎ ከፍተኛ ቁጭት እና ሀዘን በሁላችንም ላይ ተፈጥሯል::

መስጁዱ በእድሳት እጥረት በመጎዳቱ ዝናብም እያፈሰሰ እንደሚገኝ እንዲሁም ሌሎች እድሳቶችም እንደሚያስፈልገው ተገልፆ ነበር::

የአካባቢውን ሙስሊሙ ማህበረሰብ ወደ ዲናቸው እንዲመለሱ፣ ባዶ የሆነው መስጂድም በጀምዓ እንዲሞላ፣ የከፈሩትንም ለመመለስ ህዝበ ሙስሊሙ በአንድነት ትብብር እንዲያደርግ ጥሪ ቀርቦ ነበር::

ይህን አሳሳቢ ጉዳይ ቀድሞ መረጃው የደረሳቸው በደቡብ ክልል የአክፍሮት ሃይላትን የኩፍር ዘመቻ ለመመከት መሬት ላይ የወረዱ በርካታ ፕሬጀክቶችን፣ መስጂዶችን እና መድረሳዎችን እያሰሩ የሚገኙት ተወዳጁ ኡስታዛችን ኡስታዝ ሷዲቅ መሐመድ(አቡ ሐይደር) ይህንንም የዱራሜ መስጂድ ጉዳይ መፍትሄ እንዲያገኝ እየለፉ ይገኛሉ::

በዚህም መሰረት ይህን መስጂድ ለመታደግ እና የአክፍሮት ሃይላትን እንቅስቃሴ በመመከት የአካባቢውን ህዝበ ሙስሊም ወደ ዲኑ ለመመለስ ይቻል ዘንድ ሁሉም ህዝበ ሙስሊም ያቅሙን ያህል ድጋፍ የሚያደርግበት ሁኔታ ተመቻችቷል::

በኡስታዝ ሷዲቅ መሐመድ (አቡ ሃይደር ) አስተባባሪነት
በዱራሜ ከተማ በካሻ ቀበሌ አሮጌ ሰፈር የሚገኘው በዚሁ የቢላል መስጂድን ማዕከል የሚያደርግ እንቅስቃሴ ተጀምሯል::

በቀዳሚነት ለመስጂዱ ቋሚ ኡስታዝ መቅጠር እንዲሁም መስጂዱ በሚገኝበት በዱራሜ ከተማ በዱራሜ ዩኒቨርሲቲ ለሚገኙ የዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች በዚህ መስጁድ ላይ ታላቅ የዳዕዋ ኮንፍረንስ ለማካሄድ ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል::

ይህ ኮንፍረንስ ከነሐሴ 13-15/2014 ለሶስት ቀናት ኢማሙ ብቻቸውን ሲሰግዱበት በነበረው ቢላል መስጂድ የሚሰጥ ይሆናል::

ይህ ታላቅ ኮንፍረስ ሙስሊም የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ማዕከል በማድረግ በአካባቢው ያለውን የኩፍር ዘመቻ ለመመከት እና ሰዎች ወደ ዲናቸው እንዲመለሱ እንዲሁም የመስጁዱን ጀምዓ በማጠናከር ሰፊ ስራዎችን ለመስራት የሚያግዝ ነው::

አሁን ላይ የሁላችንንም ርብርብ እና ድጋፍ የሚሹ ወጪዎች ያሉ ሲሆን እነዚህም:-

1/ ቋሚ የኢማም ደሞዝ ክፍያ
2/ የመሰጂዱ አጥርን ማሳጠር
3/ መስጁዱ የጎደለውን ነገር ሁሉ ማሟላት እና
4/ ለታሰበው ታላቅ የዳዕዋ ኮንፍራንስ ወጪውን መሸፈን ይገኝበታል:

በአሁኑ ሰዓት ብቸኛ የነበሩትን ሼይኽ መሐመድኑርን የሚያግዝ በመስጁዱ በቋሚነት ሊያገልግል የሚችል ብቁ ኡስታዝ የተገኘ ሲሆን በዋናነት ኡስታዙም የመስጁዱ ኢማም በቋሚነት በመሆን እንዲያገለግል፣ ከዐሱር በኋላ ልጆችን እንዲያቀራ እንዲሁም ለካምፓሱ ተማሪዎች ኪታብ እንዲያቀራ ታስቧል::

እነዚህን አስቸኳይ ስራዎች በመስጂዱ ለመስራት በሀገር ውስጥም ሆነ ከሃገር ውጪ ያላችሁ የበኩላችሁም ድጋፍ ታደርጉ ዘንድ በአላህ ስም እንጠይቃለን::

በተከሰተው ነገር ከንፈር መምጠት እና ማዘን ብቻ ሳይሆን የመፍትሄ ሃሳብ ሲቀርብም ሁላችንም በቻልነው ያህል ማገዝ ይጠበቅብናል:: መፍትሄው በአንድነት መሬት ላይ ሊወርድ የሚችል ስራ መስራት ስንችል ብቻ ነው::

ለተዘረዘሩት ወጪዎች ድጋፍ ማድረግ ለምትፈልጉ ሁሉ በኡስታዝ ሷዲቅ መሐመድ ስም በተከፈተው አካውንት ድጋፍ ማድረግ ትችላላችሁ

1. COMMERCIAL BANK OF ETHIOPIA
1000317507589
SADIK MOHAMMED AHMED

2. ABYSSINIA BANK
83047178
SADIK MOHAMMED AHMED

3. ኦሮሚያ ህብረት ሥራ ባንክ
1011300008645
SADIK MOHAMMED AHMED

ለበለጠ መረጃ በዚህ ስልክ መደወል ትችላላችሁ
0911103231

ይህን መልዕክት ሁላችንም ሼር በማድረግ እናዳርስ!
12.2K views18:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ