Get Mystery Box with random crypto!

ዳንኤል ገብረማርያም

የቴሌግራም ቻናል አርማ zedaniel24 — ዳንኤል ገብረማርያም
የቴሌግራም ቻናል አርማ zedaniel24 — ዳንኤል ገብረማርያም
የሰርጥ አድራሻ: @zedaniel24
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 322
የሰርጥ መግለጫ

በየዕለቱ ከማገኛቸው ሰዎች፣ ከማነባቸው መጻሕፍት፣ ከማያቸው አጋጣሚዎችና ከሕሊናዬ ገጾች ከማገኛቸው ሐሳቦች መካከል መልካሙንና የወደድሁትን መርጬ ለእናንተ የማጋራበት ገጽ ነው።
💚 💛 ❤️
(ሐሳብ ለመስጠት @yedanibot ን ይጠቀሙ።)

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-04-20 17:42:20 EOTC TV እና MK TV የት ናቸው?
ዴር ሡልጣንን አስመልክቶ CTV (Coptic TV) የተባለው የግብጽ ቤተክርስቲያን ጣቢያ በየዕለቱ መረጃዎችን በዐረብኛ እየዘገበ ለግብጻዊያን ያደርሳል። ይህ ጣቢያ የግብጽ መነኮሳት ዴር ሡልጣንን የግብጽ ቀለም ከሚቀቡበት ጊዜ ጀምሮ የኢትዮጵያዊያንን ተቃውሞ እንዲሁም አሁን የተቀባው የግብጽ ባንዲራ እስኪጠፋ ድረስ ቶሎ ቶሎ ከቦታው መረጃ በማድረስ ግብጻዊያንና ሌላው ዓለም ጉዳዩን እንዲያውቅ እያደረገ ቆይቷል። በዘገባዎቹ ኢትዮጵያ የግብጽን ይዞታ ለመውረር እንደሞከረች አድርጎ በማቅረብም የኢትዮጵያን ስም እያጠለሸ ነው። ሌሎች የግብጽ የማኅበራዊ ሚዲያ ገጾችም በተመሳሳይ በንቃት ስለዴር ሡልጣን በዐረብኛና በእንግሊዝኛ ሲዘግቡ ሰንብተዋል።

ወደአገራችን ስንመለስ ግን የጉዳዩ ባለቤት ከኾነችው ከኢኦተቤክ ቴቪ ጣቢያ ጀምሮ አንድም የኢትዮጵያ ሚዲያ ስለዴር ሡልጣን አልዘገቡም። የማኅበረ ቅዱሳን ቴቪም ኾነ ኢኦተቤክ ቴቪ በዴር ሡልጣን ስለተፈጠረው ነገር ለኢትዮጵያዊያን አንድም መረጃ ማድረስ አለመቻላቸው በጣም የሚያሳዝን ነው። የመንግሥት ሚዲያዎች ኾነ ብለው ዝም ቢሉም የቤተክርስቲያን ሚዲያዎች ግን ሊዘግቡት ይገባቸው ነበር። በዚህ ዘመን ሚዲያ ታላቅ ዐቅም አለው። እናም ቅድስት ቤተክርስቲያን በደል ደርሶባትም የተገላቢጦሽ ተከሳሽ ስትኾን የግብጽ መነኮሳትን ትንኮሳ የሚያጋልጡ ዘገባዎችን ሠርቶ ለዓለም ማስተዋወቅ የእኛ ቤተክርስቲያን ሚዲያዎች ግዴታ ነበር። ነገርግን አንዳቸውም ስለጉዳዩ ማውራት አልሞከሩም።

በእርግጥ የግብጽ ቤተክርስቲያን ዴር ሡልጣንን ከኢትዮጵያ ነጥቃ ለመጠቅለል በዕቅድ ነው እየሠራች ያለችው። ለዚህም ደግሞ የግብጽ መንግሥትን ጨምሮ አክራሪ የእስልምና ቻናሎች ሳይቀር ድጋፍ እያደረጉላት ነው። ጉዳዩን ከመንፈሳዊ ቦታ ይዞታ በላይ ፖለቲካዊ አድርገውታል። ግብጽ በራሳችን አገር የምታበላላንና የምትበጠብጠን አንሶ በእስራኤል ሀገርም በየጊዜው አባቶቻችንን ዕረፍት እያሳጣች ትገኛለች። ታዲያ የቤተክርስቲያን አካላትም ኾኑ የመንግሥት አካላት ጉዳዩን በዝምታ ማለፋቸው ለምን ይኾን? ይህ ዝምታ የሚቀጥል ከኾነ ለሦስት ሺህ (2974) ዓመታት ገደማ በእጃችን የቆየውን ዴር ሡልጣንን በቅርብ ጊዜያት ውስጥ ማጣታችን የማይቀር ነው። ስለኾነም ሁሉም ኢትዮጵያዊ በተለይም ኦርቶዶክሳዊያን ለጉዳዩ ትኩረት ልንሰጠውና ልንታገል ይገባል። ቅዱስ ሲኖዶስም ተፈጻሚ የሚኾኑ መመሪያዎችን አውጥቶ ከሚመለከታቸው አካላት ጋርም በመነጋገር ችግሩ ለመጨረሻ ጊዜ እንዲፈታ ቢያደርግ መልካም ነው። ይህ ካልሆነ ግን በየጊዜው የሚነሡ የወረራ ሙከራዎች ዋጋ ያስከፍሉናል።

በእኛ ንዝህላልነትና ግዴለሽነት ሁልጊዜ ቤተክርስቲያንን ተሸናፊ የምናደርጋት እስከመቼ ይኾን?
225 viewsedited  14:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-19 18:42:46
ሰበር ዜና
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤት እና የውጭ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ እንዲሁም የድሬዳዋና ጅቡቲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የኾኑት ብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶ/ር) በጸና ታመው በኮርያ ሆስፒታል በጽኑ ሕሙማን ክፍል ሕክምና እየተደረገላቸው ይገኛሉ። እግዚአብሔር ብፁዕነታቸውን በምሕረቱ ይጎብኝልን።
222 views15:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-09 15:48:43
302 views12:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-09 12:04:27 ለለበሳችሁት ቆብና ቀሚስ፣ ለጨበጣችሁት መስቀል፣ ለተቀበላችሁት ክህነትና፣ ለተሾማችሁት እረኝነት ታምናችሁ ለመፍትሔ ሥሩ። ቸሩ አምላክ ይርዳችሁ።

ለማስታወስ ያህል አባቶቼ ሆይ በመግለጫ የሚቆም ግድያ እና በልመና የሚረጋገጥ የቤተክርስቲያን ፍትሕ ከቶ የለም። ግድያና መፈናቀሉ፣ ስደትና መከራው የሚያበቃው ፍትሕም የሚመጣው በሥራ እንጂ በልምምጥ አይደለም። ስለኾነም ቤተክርስቲያንን በሚመጥንና ዘመኑን በዋጀ መልኩ የተጠና የመፍትሔ ሥራ ይሠራ። ያሉን አማራጮች ኹለት ብቻ ናቸው፦ "ወይ ሥራ መሥራት ወይም ደግሞ በዝምታ ውስጥ ኾኖ መጥፋት"። እናም እኛ ልጆቻችሁ ስለቤተክርስቲያን አብዝተን እንጨነቃለንና ሥራ አሠሩን፣ በሚገባ ምሩን፣ እንደሥርዓቱና እንደትውፊቱ አስተዳድሩን። እባካችሁ አታሳፍሩን፣ አታስመርሩን፣ ለመከራ አትስጡን ተስፋም አታስቆርጡን። ልጆች ነንና ብንሳሳት አርሙን፣ ቡራኬያችሁም ዘወትር ይድረሰን። አሜን።

"እስመ በልዓኒ ቅንዓተ ቤትከ" እንዲል ቅዱስ ቃሉ በድፍረት ያይደለ በፍርሃት፣ በትዕቢት ያይደለ በትሕትና ስለቤተክርስቲያን በሚያቃጥል ፍቅር ውስጥ ኾነን እንዲህ ጠየቅን፣ ገና እንጠይቅማለንና እንደድፍረት አይቆጠርብን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!

@zedaniel24 @zedaniel24
294 viewsedited  09:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-09 12:04:26 በመግለጫ የሚፈታ የቤተክርስቲያን ችግር የለም!
(ዳንኤል ገብረማርያም)
====================
ዓርብ ዕለት የተሰበሰበው ቋሚ ሲኖዶስ ባለፈው እሑድ (መጋቢት ፳፭ ቀን) በአዲስ አበባ አቃቂ ቃሊቲ ወረዳ በመንግሥት ታጣቂ በጥይት የተገደለውን ኦርቶዶክሳዊ ወጣት አስመልክቶ መግለጫ አውጥቷል። በመግለጫውም "በአቃቂ ቃሊት ወረዳ በጸጥታ አካላት የተገደለውን ዘመድኩን አማረ ገዳዮች መንግሥት ለፍርድ እንዲያቀርብ ውጤቱንም ለሕዝብ እንዲያሳውቅ" ሲል ነው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ የጠየቀው። እንደው አሁን ይህ መግለጫ ቤተክርስቲያንን ከመግለጫ የዘለለ ኃይል የሌላት ደካማ ኾና እንድትቆጠር ከማድረግ የዘለለ ምን ፋይዳ ይኖረዋል? ለቤተክርስቲያን የሚየስገኘው ረብ ምንድነው?

ለመኾኑ በቋሚ ሲኖዶሱ መግለጫ ላይ ወንጀለኞችን ለፍርድ ያቅርብ ተብሎ የተጠየቀው የትኛው መንግሥት ነው? የብልጽግና መንግሥት? ከዚህ ቀደም በቤተክርስቲያን ላይ ግፍና በደልን የፈጸሙ፣ ምእመናንንና ካህናትን የገደሉ ወንጀለኞችን መቼ ተጠያቂ አድርጎ ያውቅና? እንደው የብልጽግና መንግሥት መቼ ቤተክርስቲያንን ሰምቷት ያውቃልና ነው ቋሚ ሳኖዶሱ ጥያቄ የሚያቀርብለት? እንደው'ኮ አስገራሚ ነው በጣም። በክፍለ ሀገር የተፈጸሙ በደሎችን ትተን በዚሁ በአዲስ አበባ ብቻ ከተፈጸሙት መካከል በጣም ጥቂቶቹን ብንጠቅስ በ24 አካባቢ በሌሊት ቤተክርስቲያን ማፍረሱ ሳያንሰው ኹለት ወጣቶችን (ኦርቶዶክሳዊያንን) የገደሉ የጸጥታ ተቋማት መች ተጠየቁ? መንግሥትስ ለሟቾቹ ቤተሰቦች ካሣ እከፍላለሁ ብሎ የገባውን ቃል መቼ ፈጸመ? ለአብያተክርስቲያናት የይዞታ ማረጋገጫ እሰጣለሁ ያለው መንግሥት መቼ ቃሉን ፈጸመ? እንደው በጣም የቅርቡን እንጥቀስና የወይብላ ሰማዕታትን የገደሉ ወንጀለኞችን መንግሥት ተብዮው መቼ ለፍርድ አቀረባቸው?

ታዲያ ቋሚ ሲኖዶሱ የትኛውን መንግሥት ነው "ወንጀለኞቹን ለፍርድ ያቅርብ" ብሎ የጠየቀው? ወይስ እኛ የማናውቀው የቤተክርስቲያንን ጥያቄዎች የሚሰማ ሌላ መንግሥት አለ? ቋሚ ሲኖዶሱ ለምንድነው ከምእመናን ጋር ድብብቆሽ የገጠመው? ገና ምእመናን "አባቶች ለምን ዝም አሉ?" ይሉናል ተብሎ የወጣ እንጂ ይህ መግለጫ ለቤተክርስቲያን የሚያስገኘው አንድም ትርፍ የለውም። እንደውም ቤተክርስቲያን በደል በተፈጸመባት ቁጥር ከማለቃቀስና በዳዮችን ከመለመን ውጪ ዐቅም የሌላት ደካማ ኾና እንድትቆጠር የሚያደርግ ነው። በእርግጥ ቤተክርስቲያናችን ተንቃና ተዋርዳ እንድትታይ ከተደረገች ቆይቷል። ይኸውም ለአባትነት ያልበቁ አባቶች በውስጧ ስለተሰገሰጉ ነው።

ይህ መንግሥት በምእመናን ላይ እየደረሰ ያለውን ጥቃት እንዲያስቆም የገለጠው ቅዱስ ሲኖዶስ ይቀጥልና "በሃይማኖት ተቋማት የአምልኮ ቦታ መካከል ሊኖር የሚገባው ርቀት በሕግ በተቀመጠው መሠረት እንዲተገበር"ም ጠይቋል። ግሩም ነው በእውነቱ። በአፍሪካ ኅብረት (ከርቸሌ) ሚካኤል ቤተክርስቲያን ላይ የተፈጸመው በደል ተረስቶ ነው? ወይስ አሁንም "አባቶች ተናግረዋል" ለመባል ያህል ነው እንዲህ የተጠየቀው? ለመኾኑ የትኛው መንግሥት ነው የአምልኮ ቦታዎችን እርቀት የሚጠብቀው? የቤተክርስቲያንን ይዞታ እየነጠቀ ለሌሎች የሚያከፋፍለው የብልጽግና መንግሥት? ኧረ ተው አባቶች ተው ልጆቻችሁን እንዲህ እንደሞኝ አትቁጠሩን። ሌላው ቢቀር ከላይ የተጠቀሰውን ቤተክርስቲያን (አፍሪካ ኅብረት ቅዱስ ሚካኤል) ጉዳይ መቼ ፈታችሁትና? መቼ በሕጉ መሠረት መፍትሔ አስገኛችሁና ነው ዛሬ እንዲህ የምትጠይቁ? ያውም ፌዘኛውን መንግሥት!?

ከዚህም በተጨማሪ "መንግሥት ጸጥታ በማስከበር ስም ጥቃት የፈጸሙ አካላትን ለፍርድ ከማቅረብ በተጨማሪ ሌሎች የጸጥታ አካላት ከተመሳሳይ ድርጊት እንዲታቀቡ እንዲያደርግ" ሲልም ቋሚ ሲኖዶስ አስታውቋል። አይ አባቶቻችን! እስኪ እንደው እናንተ እንደጠየቃችሁት ይኹን። የጠየቃችሁት መንግሥት ቃላችሁን ተቀብሎ ተፈጻሚ ለማድረግ ያብቃው። ግን ጥያቄዎቻችሁን እንደማይሰማችሁ አንድ ሺህ በመቶ እርግጠኞች ነን። ምክንያቱም ወንጀለኛው ራሱ የጠየቃችሁት መንግሥት ስለኾነ። በእርግጥ እናንተም ተባባሪዎቹ ናችሁ። ይህን የምንለው ደግሞ በዐይናችን ስላየን፣ በጆሯችንም ስለሰማን እንጂ ከመሬት ተነሥተን አይደለም። ተባባሪዎቹ ባትኾኑማ ለአራት ዓመታት ሙሉ ቤተክርስቲያን ክፉኛ ስትፈተን እየተለማመጣችሁ ዝም ባላላችሁ ነበር። የመንግሥት ተባባሪዎች ባትኾኑማ ለሃያ ሰባት ዓመታት ቤተክርስቲያን ላይ ሴራ ሲሠራ እያያችሁ በዝምታ ባልኖራችሁ ነበር። የመንግሥት ተባባሪዎችና አጎብዳጆች ባትኾኑማ ደፍራችሁ ወጥታችሁ "ቤተክርስቲያን ላይ ግፍ እየተፈጸመ ነው፣ የዘር ማጥፋት እየተፈጸመ ነው፣ መዋቅራዊ ጥቃት እየተፈጸመ ነው፣ ቤተክርስቲያን በመንግሥት እየተሰደደች ነው!" ብላችሁ በሞገታችሁ ነበር። እንደአቡነ ጴጥሮስ እንደቅዱሱ ሰው ከምንም በላይ እረኝነታችሁን አስቀድማችሁ ለምእመኑ አርአያ የሚኾን ለቤተክርስቲያንም መፍትሔን የሚያመጣ በጎ ተጋድሎን ባደረጋችሁ ነበር። አጎብዳጆች ባትኾኑማ ኖሮ "የቤተክርስቲያን መከራ ይቁም!" ብለው የተነሡ ልጆቻችሁ ሲታፈሱ፣ ሲታሰሩ፣ ሲገረፉ እያያችሁና እየሰማችሁ ዝም ባላላችሁ ነበር። የመንግሥት ተባባሪዎች ባትኾኑማ ኖሮ ለቤተክርስቲያን መብትና ህልውና ሆ ብሎ በወጣው ምእመን ስሜት ላይ አንዳች መፍትሔ የማያመጣ ስምምነትን ፈጽማችሁ፣ በጋለው የምእመኑ ቁጣ ላይ በረዶ ባልጨመራችሁ ነበር። መስቀል ዐደባባይ የማንም መፈንጫ ሲኾን የሕዝብን ቁጣ እንዲጠፋ ከማድረግ ይልቅ ከምእመኑ ፊት ተሰልፋችሁ ለቤተክርስቲያን በታገላችሁ ነበር። ዳሩ ምን ያደርጋል፦ መለካዊነት የገዛቸው፣ አድርባይነት የዋጣቸው፣ ግዴለሽነት ያጠቃቸው አባቶች በዙና የቤተክርስቲያን መከራ ማላገጫ በሚመስል መግለጫ ብቻ እየተድበሰበሰ እንዲቀር ይደረጋል። በእውነቱ ከእናንተ መካከል እውነተኛ እረኛ ማን ይኾን?

ብፁዓን አባቶቼ ሆይ ቅድስት ቡራኬያችሁ ትድረሰኝ! ባከብራችሁም፣ ብወዳችሁም፣ ቤተክርስቲያን ለእናንተ ብቻ ሳትኾን ለእኔም ናትና በትሕትና እጠይቃችሁ ዘንድ ግድ ይለኛል። በእውኑ በመግለጫ መከራዋን ማስወገድ፣ ስደቷን ማስቆም የሚቻል ይመስላችኋል? ወይስ ቤተክርስቲያን ያለችበትን ሁኔታ በሚገባ አልተረዳችሁትም? እንደው ዓለማችን የደረሰችበትን ኢትዮጵያችንም ያለችበትን መንገድ የሚገልጽ መረጃ አይደርሳችሁ ይኾን?ይህ ነው እንዳልል ደግሞ ከብዛኞቻችሁ በውጪው ዓለም የኖራችሁ፣ በዓለማዊት ትምህርታችሁ ብዙ ዲግሪ ያላችሁ፣ ዘመናዊ የእጅ ስልኮችን የምትጠቀሙ ናችሁ። ብቻ ቤተክርስቲያንን በተመለከተ የምታሳዩን ነገር ብዙም ደስ አይልም። ምናልባት "አውቆ የተኛን ቢቀሰቅሱት አይሰማም" ከኾነ እያወቃችሁ ተኝታችኋልና የእኛ የምእመናን ለቅሶና መከራም አልቀሰቀሳችሁምና ቸሩ አምላክ እንዲያነቃችሁ እንማጸናለን።

ግድየለሾች ሆናችሁ ነው እንዳንልም ተቸግረናል። ሆድ አደሮች እያስጨነቋችሁ ነው እንዳንል ደግሞ የአቡነ ጴጥሮስ ልጆች ናችሁና ለማመን ይከብደናል። እኛን ልጆቻችሁን ስለሰማዕትነት የምታስተምሩን እናንተ፣ ፍርሃትን በመስቀሉ ኃይል አሸንፉ የምትሉን እናንተ የሚደርስባችሁን ነገር ፈርታችሁ የቤተክርስቲያንን መከራ እንዲሰፋና እንዲቀጥል እያደረጋችሁ ነው ብሎ ለመቀበል ይከብዳል። እንደው የእየሉጣ ፍርሃት ገዝቷችሁ ከኾነ በእርግጥ እኛ ልጆቻችሁ እንደቂርቆስ ልንጸልይላችሁ፣ ኑ ገድላችንን እንፈጽም ልንላችሁም ይገባናልና አሳውቁን። እኛ እናንተን ስንጠብቅ ቤተክርስቲያናችን የማይገባትን መከራ እየተቀበለች ነውና እባካችሁ
231 viewsedited  09:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ