2022-08-29 09:33:28
#ኢትዮጵያ_የዓለም_ብርሃን_እምነት_ተስፋ_ፍቅር_ትምህርት
❖ የእውነት ሰው፣ የእምነት ሰው፣ የእግዚአብሔር ሰው ጽኑና የማይፈራ፣ የማይነቃነቅ መሰረቱ የጠበቀ አለት ማለት ነው።
አለቱ ክርስቶስ አይደል እሱ ላይ የተመሰረተ ስለሆነ አለት ነው።
የእግዚአብሔርን ፈቃድ አድርጋችሁ ❖ የተሰጣችሁን የተስፋ ቃል እንድታገኙ መጽናት ያስፈልጋችኋልና ይለናል ቃሉ።
#ልብ_በሉ.....
❖ አምናችሁ አይደል በእምነት ውስጥ አይደል ያላችሁት ካመናችሁ በኋላ የእግዚአብሔር ድምጽ ወደ እናንተ ይመጣል። በቃሉ ይናገራችኋል፣ በራዕይ ይናገራችኋል፣ በሕልም ይናገራችኋል።
ማን? #እግዚአብሔር_የአብርሃሙ_ሥላሴ!!!
❖ ዛሬም ምድሪቱን የሚያጽናናው ከሦስቱ አካል አንዱ የሆነው እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ዘውትር ስለ እውነት ይናገራችኋል፣ መንገዱን ያሳያችኋል፣ ያጸናችኋል። ምንም ጨለማ ቢሆን ምንም ማዕበል ቢፈስ፣ ቢጠርግ ልትነቃነቁ አይገባም፣ ልትጨነቁ አይገባም።
የተሰጣችሁን የተስፋ ቃል እንድታገኙ መጽናት ያስፈልጋችኋል።
❖ የተስፋውን ቃል የጠበቀ ከእምነት ተነስቶ ተስፋ ያደረገ የጸና ነው ባለድል የሚሆነው።
#ልብ_በሉ
''....ገና በጣም ጥቂት ጊዜ ነው ሊመጣ ያለው ይመጣል፣አይዘገይም፤ ጻዲቅ ግን በእምነት ይኖራል''።
#ኢትዮጵያ_የዓለም_ብርሃን...#እምነት_ተስፋ_ፍቅር ክፍል ሁለት ትምህርት 'ሠ' ከ 00: 10: 16 - 00: 12: 02 ደቂቃ ላይ የተወሰደ።
ከመልካሙ እረኞ ንጉሰ ነገስት ሣልሳዊ ቴዎድሮስ
702 views06:33