Get Mystery Box with random crypto!

ወርቃማዎች

የቴሌግራም ቻናል አርማ werkamaa — ወርቃማዎች
የቴሌግራም ቻናል አርማ werkamaa — ወርቃማዎች
የሰርጥ አድራሻ: @werkamaa
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 351

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2023-02-21 10:50:50 «ምንም ስህተት አልሰራንም ነገር ግን በሆነ መንገድ ተሸንፈናል»

――«――――――――――――――»――

የNOKIA ዋና ስራ አስፈፃሚ ከሁሉም የማኔጅመንት አባላት ጋር በመሆን ለብዙ አመታት የለፉበት ድርጅት በማይክሮሶፍት መጠቅለሉን ለማሳወቅ እና ጋዜጣዊ መግለጫ ለመስጠት አዳራሽ ውስጥ ተሰይመዋል። ከብዙ በሃዘን የታጀቡ ንግግሮች በኋላ ንግግራቸውን እንዲህ በማለት ቋጩ፦ «ምንም ስህተት አልሰራንም፤ ነገርግን በሆነ መንገድ ተሸንፈናል»

ኖኪያ የተከበረ ኩባንያ ነው። በንግድ ስራቸው ውስጥ ምንም ስህተት አላደረጉም። ሆኖም ግን ተፍካካሪያቸው በጣም ኃይለኛ ስለነበሩ ዓለም ጥሏቸው ሄደ።

ተምሮ የመስተካከል፤ ተስተካክሎ የመለወጥ እድል በማሳለፋቸው ትልቅ የመሆን የማደግ እድሉን ለሌሎች አሳልፈው ሰጥተዋል። ብዙ ገንዘብ የማፍራት ብሎም የማትረፍ እድል ብቻ ሳይሆን የመትረፍ እና በሕይወት የመቀጠል እድላቸውን አጥተዋል።

«በቶሎ ካልተቀየርክ፤ ከፉክክሩ ትወጣለህ» የታሪኩ መልእክት ነው። አዳዲስ ነገሮችን መማር አለመፈለግ ስህተት አይደለም። ነገር ግን ሃሳብህ እና አስተሳሰብህ ከጊዜን ጋር ካልናኘ ከውድድር አለም ትወገዳለህ። ከውድድር አለም መወገድ ብቻ ሳይሆን በሕይወት የመቆየት እድልህ የተመናመነ ይሆናል።

∴ ሲጠቃለል፦

① ትላንትና የነበርክበት የተጠቃሚነት ደረጃ ነገ በሚፈጠሩ የተለዩ ዝንባሌዎች ይተካሉ። ተፎካካሪዎችህ ማዕበሉን እስኪይዙና በትክክለኛው መንገድ እስኪያስኬዱት የመሸነፍ እና የመውደቅቅ አዝማሚያ ልታሳይ አትችልም። እነዚህ አዳዲስ ዝንባሌዎች እስኪፈጠሩ የሰራሃው ስህተት ፍንትው ብሎ አይታይህም።

② ራስህን ለመለወጥ እና ለማሻሻል ለራስህ ሁለተኛ እድል ስጥ። በሁኔታዎች ተገዶ መለወጥ እንደ መወገድ ይቆጠራል። ለመማር ብሎም ራስን ለማሻሻል አሻፈረኝ ያሉ፣ በእርግጠኝነት አንድ ቀን ራሳቸውን ከኢንዱስትሪው ውጪ ያያሉ። ውድ እና ከባድ በሆነ መንገድም ትምህርት ይወስዳሉ።

መልካም ቀን
@WERKAMAA
11 views@ñwăř, 07:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-20 18:15:58 አባት ወንድም፣ ለሁሉም አሳቢ፣
እቅፍ አርጎ፣ ከጉያው ሰብሳቢ፣
ትልቅ ትንሽ፣ ሁሉንም ተግባቢ፣
ፍቅር እዝነት፣ ሰላምን መጋቢ።

የሁሉ አጋር፣ የሁሉ አለኝታ፣
የእውነት ወንድም፣ አባት ነው መከታ፣
የተከዘን፣ ቀና ሚያደርግ ደርሶ፣
ተስፋ ሚሰጥ፣ እንባውን አብሶ።
@WERKAMAA
37 views@ñwăř, 15:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-20 06:47:42 ይሆናል ያሉት ላይሆን ይችላል
አይሆንም ያሉት ሆኖ ይገኛል

ያስቀመጡትን ሄደው ያጡታል
የት ይገኝ ያሉት እዛው ይመጣል

በህይወት ቀመር
ድምር ይዞራል
ዞረ ያልነውም
ላይዞር ይችላል!!!

እና ፈተና ፣ ውድቀት ፣ ድህነት ምርጫ ወይስ እጣ ፋንታ...???
@Werkamaa
47 views@ñwăř, 03:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-17 06:15:41 ሰላም ለእናንተ ይሁን እንዴት አደራችሁ

"የተሳሳተ አካሄድ እንጂ የተሳሳተ መንገድ የለም"

ሁለት ወጣቶች ወደ ቤታቸው ለመሄድ የታክሲ ሰልፍ ላይ ቆመዋል፡፡ ታክሲው መጣና ሁለቱም ተሳፈሩ፡፡ ከ30 ደቂቃ ጉዞ በኀላ "መጨረሻ" በማለት ረዳቱ ሲናገር ሁሉም ከታክሲው ወረዱ፡፡ በዚህ ወቅት አንደኛው ወጣት በትክክል ሰፈሩ ሲደርስ ሌላኛው ግን በስተት ካለሰፈሩ ነበር የመጣው፡፡

በስተት ሌላ ሰፈር የሄደው ወጣት "የተሳሳተ መንገድ ነው የመጣውት" ብሎ ማማረር ጀመረ፡፡
ነገር ግን የተሳሳተው መንገዱ ነው ወይስ ወጣቱ?

መንገዱማ ትክክለኛ ስለሆነ ሌላኛውን ወጣት በትክክል ሰፈሩ አድርሶታል፡፡ ነገር ግን መንገዱ ሳይሆን ተሳፋሪው የተሳሳተ በመሆኑ አንዱን ደሞ የማይፈልገው ሰፈር አምጥቶታል፡፡

የአብዛኞቻችን ህይወትም ተመሳሳይ ነው፡፡ መሆን የምንፈልገው ዶክተር ነው፡፡ ነገር ግን የምንማረው አካውንቲንግ ነው፡፡ መሆን የምንፈልገው ታዋቂ ሀብታም ነው ነገር ግን የተሳፈርነው በኢንጅነሮች ታክሲ ነው፡፡ በህይወታችን ደስተኛ መሆን ከፈለግን ወደ ምንፈልገው ቦታ የሚያደርሰንን ትክክለኛ መንገድ ፈልገን መጓዝ ይጠበቅብናል፡፡ ነገር ግን ወደ እኛ ፍላጎት በማይወስድ መንገድ በመገኘታችን ብቻ ያ መንገድ ተሳስቷል ማለት አንችልም፤ ምክንያቱም በዛ መንገድ ተጉዘው ካሰቡበት የሚደርሱ ብዙ አሉና፡፡

"ውሏችን ባሰብነው መልኩ የተሳካና ቀና ይሁንልን"
መልካም ቀን

ይ ቀ ላ ቀ ሉ ን

@Werkamaa
15 views@ñwăř, 03:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-15 06:41:23 ሙላህ ነስሩዲን ጥቂት ፍራፍሬ ይዞ ልጆች በበዙበት መንደር ሲያልፍ እንዲሰጣቸው ጠየቁት:: ሙላህ የውሸቱን << እዚያ ጋር እየታደለ ስለሆነ ሄዳችሁ ውሰዱ >> ሲል አንዱ ልጅ ወደተባለው አቅጣጫ ሮጠ:: ሁለተኛ ልጅ ተከተለ:: ሌሎች ልጆችም ግር እያሉ ሲሮጡ ሙላህም <<ይህ ነገር ዕውነት ይሆን እንዴ?>> ብሎ በሩጫ ተከተላቸው::
በአሁን ወቅት እንኳን ቡድንህ ቀርቶ የራስህን ውሸት እንኳ ውሸት መሆኑን እያወቅክ መንጋ ካገኘህ አንተም ታምናለህ::
@Werkamaa
34 views@ñwăř, 03:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-11 07:27:22 ማንም ሰዉ ወደ ህይወታቹ ገብቶ ምን ያህል እንደሚያፈቅራቹ ሊነግራቹ ይችላል ነገር ግን አንድ ልዩ ሰዉ ብቻ ነዉ አብሮ እየኖረ ፍቅርን የሚያሳያቹ።


@Werkamaa
4 views@ñwăř, 04:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-07 23:08:34 በህይወት መንገድህ ውስጥ የተለያዩ ልምዶች ያልፋሉ! . . . ላጋጠመህ እና ለሚያጋጥምህ ልምዶች አመስጋኝ ሁን!
. . . ለሚፈጠሩት ነገሮች ሁሉ አመስጋኝ ሁን።ያለህበትን ቦታ መውደድን ተማር! . . .



@tebebmaraki
72 views@ñwăř, 20:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-04 07:27:59 ፡፡፡፡፡፡፡፡ የመኖር አባዜ፡፡፡፡፡፡


ሰው በሰውነቱ ሳይሆን በሀብቱ ይወደዳል
በቀኝ ስሞላው በግራ ይጎድላል፣
በዚህ ስጠግነው በዚያ ይሰበራል፣
የዚች አለም ህይወት ከቶ መች ይሞላል፡፡

ወረት እንደሰማይ፣
እጅግ እርቆኛል፡፡
ዛሬን ሳይሆን ነገን ተስፋ አድርጌ ስኖር፣
በልቼ ለማደር፣
ስጥር ስንፈራፈር፣
መግባት ላይቀር አፈር፣
ሁልጊዜ መቸገር ፣
ከልኩ አያልፍ ነገር፡፡
ያሰብነው ሊሞላ አምላክ ባለው ጊዜ፣
ትርፉ መጎዳት ነው ይቅርብን ትካዜ፣
ድሮም እንደዚህ ነው የመኖር አባዜ፡፡

ከወደዱት ለወዳጆ ያጋሩ
@Werkamaa
28 views@ñwăř, 04:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-04 06:50:00 ዱለት የሚለው ቃል ከምን እንደመጣ ታውቃላቹህ?

ድሮ ጌቶችና እመቤቶች ሽንጥና ሻኛ እንጂ ጨጓራና ጉበት አይበሉም ነበር አሉ። ለአሽከሮች ደግሞ ደህና የሚባል ስጋ አይሰጣቸውም ነበር።
መቼስ መፍትሄ ከችግር አይደል ሚመጣው?
ታዲያ በስጋ አምሮት የተሰቃዩት አሽከሮች ተሰባስበው በወቅቱ ከማይፈለገው ጨጓራ፤ ጉበትና አንጀት አንድ የሆነ ምግብ አንፈላሰፍም ብለው ተነጋገሩና የሆነ ጣፋጭ ምግብ ሰሩ። ያንን ጣፋጭ ምግብ ሰርተው ሲበሉ እመቤቲቱ ደረሱና ምንድነው የምትበሉት? እስኪ አምጡት አሉና ሲቀምሱት እጅ ያስቆረጥማል።
"ይሄን እየበላችሁ ነው ስጋ አይሰጡንም የምትሉት? ወይ ድሎት! " አሉ።

ያ ምግብም ከዚያ በኋላ #ድሎት ከሚለው ሸርተት ብሎ #ዱለት እየተባለ ከነጌቶችና እመቤቲቱ ቡፌ ላይ የማይጠፋ ሆነ።
እየበላቹ ጎበዝ!!!
@WERKAMAA
33 views@ñwăř, 03:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-02 22:49:03 አንተ ''ትክክል ነኝ'' የማለት መብት
ለራስህ እንደሰጠህ ሁሉ ሌሎችም
በተመሳሳይ መልኩ ''ትክክል ነኝ"
የማለት መብት እንዳላቸው አትዘንጋ።
___________


@Werkamaa
74 views@ñwăř, 19:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ