Get Mystery Box with random crypto!

ፅኑ አብሮነት !

የቴሌግራም ቻናል አርማ tinuaberonet — ፅኑ አብሮነት !
የቴሌግራም ቻናል አርማ tinuaberonet — ፅኑ አብሮነት !
የሰርጥ አድራሻ: @tinuaberonet
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 908
የሰርጥ መግለጫ

ፖለቲካዊ፣ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ መረጃዎችን ያገኙበታል።
ሊንኩን ተጭነው ጆይን ይበሉ!
t.me/TinuAberonet
ለማንኛውም አሰተያየት እታች በሚገኘው ቦት ሊያገኙን ይችላሉ።
@Abdulmejid_bot

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-07-20 20:23:45 ጎንደር የአሸባሪዎች ሃገር
===================
ተበዳይ ካሳ ከፋይ የሆነበት "ፍትሕ"

የጎንደር ከተማ ሙስሊም ተዘርፎ ለወደመበት ንብረት ካሳ ማግኘት ሲገባው ስለምን መልሶ ካሳ ሰጭ እንዲሆን ይገደዳል!?

በመርህና በፍልስፍና ደረጃ የህዝብን አደራ የተቀበለ መንግስት በአመራርነት የሚሾማቸው ግለሰቦች በዕውቀታቸው፣ በስራ ልምዳቸውና ችሎታቸው ነፃ ገለልተኛና ፍትሐዊ አስተሳሰብን መነሻ በማድረግ ከአድሎ፣ ከወገንተኝነት፣ ከጥላቻ፣ ከቡድንተኝነት እና ከጎጠኝነት በፀዳ አግባብ የተወከሉበትን የማህበረሰቡን ችግር በአግባቡ አዳምጦ በእኩልነትና በነፃነት መንፈስ መፍትሄ በመስጠት የማገለግል ግዴታ እንዳለበት እሙን ነው።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሀገራችን ኢትዮጲያ በተለይም በአማራ ክልል ጎንደር እና አካባቢዋ እየተስተዋለ የመጣው አብሮነትን እና የመቻቻልን እሴት ገፊ የሆኑ ኃይማኖታዊ ፅንፈኛነት ተበራክተዋል። እነኝህ የፅንፈኛ እሳቦቶች እና ኃይሎች የአንድን ኃይማኖት የበላይነትን ለመጫን በማሰብ ከሌሎች ወገኖቹ ጋር ለዘመናት ተዋዶ እና ተከባብሮ የኖረውን ሙስሊም ማህበረሰብ በተለያዩ ወቅቶች ዘርፈ ብዙ ጥቃቶችን ሲያደርሱበትና ሲገፉት በተደጋጋሚ አስተውለናል።

ባለፉት ዓመታት እነኚህ ፀረ-ብዙሀን ፅንፈኛ ኃይሎች በአካባቢው ሙስሊም ላይ ጥቃት በማድረስ ላጠፉት ተደጋጋሚ ጥፋት የክልሉ መንግስት ጊዜውን እና ወቅቱን በጠበቀ መልኩ አጥፊዎችን ተገቢውን ጥያቄ ጠይቆ ፍትሕን የማስፈን ህጋዊ እርምጃ ባለመውሰዱ ምክንያት አላባራ ያለ ተደጋጋሚ ጥቃቶች በሙስሊሙ ምዕመን ላይ እንዲደርስባቸው ምክንያት ሆኗል።

ከነዚህም ጥቃቶች መካከል (ምንም እንኳ የጥቃቱ ምልክቶች አሁንም ድረስ ባያቆሙም) ከሚያዚያ 18 እስከ 20/2014 ዓ.ኢ ባሉት ተከታታይ ሶስት ቀናት በጎንደር ሙስሊሞች ላይ በታሰበበት እና በተቀናጀ መልኩ የሽብር ጥቃት ደርሶባቸዋል። በጥቃቱም በርካታ ንፁሃኖች ተጨፍጭፈው፣ በመቶዎች የሚቆጠሩት ከባድና ቀላል የአካል ጉዳትን አስተናግደው፣ ከ12 በላይ መስጅዶች የሽብር ጥቃቱ ሰላባ ሆነው በርካታ የሙስሊሙ ማህበረሰብ ንብረቶች ተዘርፈው የቀሩት ንብረቶችም እየተቃጠሉ እንዲወድሙ ተደርገዋል።

በጎንደር ሶስት ወራትን እያስቆጠረ ያለው ይህ ሙስሊሞችን ብቻ በዕምነታቸው ለይቶ የደረሰ የሽብር ጥቃት አሁንም ድረስ በፍትሕ እጦት ሳቢያ የከተማው ህዝበ ሙስሊም መሰደድና መፈናቀልን ዕጣ ፋንታው አድርጎ በመሸሸት ላይ ይገኛል።

ከዝርፊያ እና ከውድመት ተርፈው ያለስራ ተዘግተው የሰነበቱት የሙስሊም ድርጅት ባለቤቶች የሽብር ጥቃት ሰለባ ለሆኑ እህት ወንድሞቻቸው ያለፉትን ሶስት ወራት በሚችሉት አቅም ካላቸው የተዳከመ የኢኮኖሚ ጥሪት ቀንሰው በመርዳት ሲያፅናኑ መሰንበታቸውን ታዝበናል።

በመልካም አስተዳደር እጦት ምክንያት የከተማው አስተዳደር ለጠፋው የንፁሀን ነብስ፣ በሽብር ጥቃቱ አካላቸው ለጎደለው ምዕመኖች እንዲሁም ለወደሙት መስጅዶች፣ ለተዘረፉት እና ለተቃጠሉት የምዕመኖች ንብረት ካሳ መክፈልና ለተጎጅዎችም ፍትሕን አስፍኖ ወደነበሩበት መደበኛ ሕይወታቸው እንዲመለሱ ማድረግ የከተማ አስተዳደሩ መደበኛ ስራው መሆኑ ቢታወቅም ይህንን ማድረግ ተስኖት በእነኚህ ፅንፈኛ ቡድኖች ተጠልፎ አሁንም ድረስ በከተማው ሙስሊሞች ላይ የሚደርሰው በደል አላባራ ብሏል።

በሚያሳዝን መልኩ በከተማው አስተዳደር ፍትሕ እጦት ሳቢያ ተስፋ ቆርጠው ከተማዋን ለቀው ለመውጣት የማጣሪያ ገበያ ላይ ያሉትን ሙስሊም ነጋዴዎች አይዟችሁ ተብለው እንዳይሰደዱ ማድረግ ሽሽታቸውን ማስቆም ሲገባ ጭራሹን ጫና ፈጥሮ በማስገደድ የሽብር ጥቃቱ ሰለባ ለሆኑት ሙስሊሞች <<የካሳ ክፍያ መዋጮ>> በሚል አስገዳጅ ምክንያት በተደጋጋሚ ያለአቅማቸው ላልተገባ ብዝበዛ እየዳረጋቸው እንደሚገኝ የከተማው ሙስሊም ነጋዴ ማህበረሰብ ቅሬታቸውን አሳውቀዋል።

ለዚህም ማሳያው ከሰሞኑ የከተማው አስተዳደር ጉዳዩን በተመለከተ እየሄደባቸው ያለውን አካሄዶች አይቶ መገንዘብ እንደሚቻል አረጋግጠናል።

በመሆኑም ይህንን የከተማውን አስተዳደር የተዛባ የፍትሕ አካሄድ የሚመለከተው የበላይ አካል ተገንዝቦ ተገቢውን ህጋዊ እርማት በማድረግ ፍትሕን እንዲያሰፍን እናስታውሳለን!!
300 views17:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-10 11:08:43
እባካችሁ አጥብቃችሁ እሰሩ¡

በተለይ እንደዚህ የመሮጥ አቅሙ የሌላችሁ¡
433 views08:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 21:10:04 ማስታዎሻ
=========
ነገ ዕለተ ጁሙዓህ ዙል ሒጃህ 9, 1443 ዓመተ ሂጅራ ነው። ይህ የዙል ሒጃህ ዘጠነኛ ቀን የዐረፋህ ቀን ነው።

①) ይህ ቀን ከአመቱ ቀናት ሁሉ በላጩ ቀን ለመሆኑ በዕውቀት ባለቤቶች ዘንድ ቅንጣትም ውዝግብ የለም።
°
②) በዚህ ቀን የሚሠሩ መልካም ሥራዎች ከሌላው በላጭ ናቸው።
°
③) በዕለቱ ከሚሠሩ መልካም ሥራዎች መካከል አንዱና ዋናው ደግሞ ዱዓእ ነው።
°
④) እርሳቸው ይሁኑ ከርሳቸው በፊት ያሉ ነቢያት በዚህ ቀን ካደረጓቸው ዱዓዎች ሁሉ በላጩ «ላ ኢላሃ ኢለ-ል'ሏህ ወሕደሁ ላሸሪከ ለሁ ለሁ-ል-ሙልኩ ወለሁ-ል-ሐምዱ ወሁወ ዓላ ኩሊ ሸይኢን ቀድር» የሚለው መሆኑን ተናግረዋል – ረሱሉ-ል-ሁዳ ﷺ!
ያልሐፈዛችሁ ሐፍዙት!
°
⑤) ይህን ቀን ሐጅ ላይ ካሉ ሰዎች ውጭ ሌላው በጾም ማሳለፉ የሁለት አመታትን (ከኋላውና ከፊቱ ያሉ አመታትን) ወንጀል ያስምራል ብለዋል ውዱ ነቢይ ﷺ።
°
⑥) በዚህ ቀን በተለይም ከዐስር እስከ መጝሪብ ባለችው ወቅት የሚደረግ ዱዓእ እጅግ በጣም ተቀባይነት አለው።
°
⑦) በተጨማሪም ይህ ቀን የዋለው ነገ ጁሙዓህ እንደመሆኑ መጠን፤ በሌላ ሐዲሥ እንደተዘገበው በዕለተ ጁሙዓህ ከዐስር እስከ መጝሪብ ባለው ወቅት የሚደረግ ዱዓእ ተቀባይነት አለው። Imagine ሁለቱ ተቀባይነት ያለባቸው ወቅቶች አንድ ላይ ሲገጣጠሙ → ተቀባይነት² በሉት።
°
⑧) አላህ ይወፍቀንና፤ ሰሑር ላይ ቢነጋብን እንኳ ጹመን ለመዋል ለአንድት ቀን ብንነይት፣ ይህቺን ከዐስር እስከ መጝሪብ ያለች ወቅትም በኸይር ነገር ብናሳልፋት መልካም ነው። መቼም ሁላችንም ይብዛ/ይነስ እንጂ ከወንጀል የጠራን አይደለንምና እንዲህ አይነት ጌታችን እኛን ለመማር ብሎ ያመቻቸልንን የወንጀል ማበሻ ሰበቦችን በአግባቡ እንጠቀምባቸው።
°
⑨) ተክቢራ ማለት የሚጀመረው ከነገ ጠዋት የፈጅር ሶላት ጀምሮ እስከ ዙል ሒጃህ 13ኛ ቀን ዐስር ድረስ ነው።

አላህ እኔንም እናንተንም ለሚወደው ንግግርና ተግባር ይወፍቀን። ወደ መልካም ያመላከተ የሠሪውን ያክል ምንዳ ያገኛልና ቤተሰቦቻችሁን፣ ወዳጅ ዘመዶቻችሁን ለማስታወስ ሞክሩ።


||
t.me/MuradTadesse
468 views18:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-24 15:33:57 The account of the user that owns this channel has been inactive for the last 5 months. If it remains inactive in the next 28 days, that account will self-destruct and this channel may no longer have an owner.
12:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-24 17:42:50

743 views14:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-24 17:42:32

631 views14:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-06 00:35:19
713 views21:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-06 00:29:46
(J4F)
675 views21:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-11-22 17:54:58 #NoMore
1.5K views14:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-08-29 10:58:54 በዞን ደረጃ «ወላይታ ቲቪ» አለ! ሁለት ታላላቅ ዞኖች ያሉት የወሎ ህዝብ የሌሎች ሚዲያዎችን ዘገባ ከመመኘት ይልቅ ተደራጅቶ «ወሎ ቲቪ» ብሎ ቢከፍት መልካም ነው። ወሎ የራሱ ማንነት፣ በቂ ባህልና እምነት ያለው ማህበረሰብ ነው። የራሳቸው ቲቪ ከከፈቱ እንኳን ለራሳቸው ለሌላውም ድምፅ ይሆናሉ።
2.0K views07:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ