2022-07-01 08:59:37
እንኳንም ተሳሳትክ!
በአንድ ወቅት አንዲት የሒሳብ መምህርት የሚከተለውን በሰሌዳ ላይ ጻፈች፦
9×1= 7
9×2= 18
9×3= 27
9×4= 36
9×5= 45
9×6= 54
9×7= 63
9×8= 72
9×9= 81
9×10= 90
ጽፋ እንደጨረሰችም ወደ ተማሪዎቿ ዞራ ስትመለከት ሁሉም እየሳቁባት ነው፣ የመጀመሪያውን እኩልታ (equation) ተሳስታለችና።
ይህን ጊዜ መምህርቷ እንዲህ አለች፦ "የመጀመሪያውን ስህተት የጻፍኩት በዐላማ ነው፤ ከነገሩ ጠቃሚ ትምህርትን እንድትወስዱ ስለፈለኩኝ። ይኸውም፥ በውጪ ያለው ዓለም እንዴት እንደሚቀበላችሁ ታውቁ ዘንድ ነው። 9 ጊዜ ትክክለኛ ነገር እንደጻፍኩ ማየት ትችላላችሁ ይሁንና አንዳችሁም ስለዛ አላበረታታችሁኝም፤ ነገር ግን ሁላችሁም ስለ ሠራሁት አንድ ስህተት ሳቃችሁብኝ፣ ነቀፋችሁኝም።
ትምህርቱም ይህ ነው፤
• ዓለሙ፥ ሚሊዮን መልካም ሥራን ብትሠሩ አያበረታታችሁም ግን አንድ የሠራችሁትን ስህተት ይዞ ይነቅፋችኋል። በዚህ ግን ተስፋ ልትቆርጡ አይገባም። ሁልጊዜም ቢሆን ከሳቅና ከነቀፋ በላይ ወጥታችሁ ቁሙ፣ ጽኑ፣ በርቱም!"
ልብ በል፤
• መሳሳትን ከፈራህ መሞከር አትችልም፤ መሳሳት ያንተ መጨረሻ አይደለም የማወቅ መነሻ እንጂ።
• ምናልባት የተማርከውን ትረሳ ይሆናል፣ የተሳሳትከውን ግን አትረሳም።
• ከብዙዎች የስንፍና ፍፁምነት ይልቅ ያንተ የመሥራት ስህተት እንደሚሻል አስብ።
• ከመሳሳትህ በላይ ሰው ምን ይለኛል? የሚለው ነገር ያስጨንቅህ ይሆናል፤ ሰው ግን እንዳንተው የሚሳሳት መሆኑን አትርሳ።
ኖረህ ስላልጨረስክ እንኳንም ተሳሳትክ!፤ ስህተትህ ላይ ከዘገየህ ብዙ ነገሮች ያልፉሃል፣ በቶሎ ከተማርክ ግን አዲስ ነገር ታውቃለህ፣ ትሠራለህ።
ይ ቀ ላ ቀ ሉ ን
t.me/Werkamaa
196 views05:59