Get Mystery Box with random crypto!

ኢስላማዊ እና ጠቅላላ እውቀት

የቴሌግራም ቻናል አርማ islamawe99 — ኢስላማዊ እና ጠቅላላ እውቀት
የቴሌግራም ቻናል አርማ islamawe99 — ኢስላማዊ እና ጠቅላላ እውቀት
የሰርጥ አድራሻ: @islamawe99
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 335
የሰርጥ መግለጫ

እየተጠያየቅን እውቀታችንን እናስፋ
ማንኛውም ጥያቄ እና አስተያየት ካላችሁ በዚህ ሊንክ ገብታችሁ
@islamawetube_bot ሀሳባቸሁን አካፍሉኝ ጥፋት ሰታዩብኝ አርሙኝ

Ratings & Reviews

1.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-06-29 07:17:33 ወርቃማዎቹ የዙል ሒጃህ 10 ቀናት የፊታችን ሐሙስ ማለትም ሰኔ 23 (በፈረንጆቹ June 30) 1 ብለው ይጀምራሉ።

አላህ ከሚጠቀሙባቸው ያድርገን።
155 views04:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-28 04:46:42
የዙልሂጃ አስር ቀናት ትሩፋት እና በነዚህ ቀናት መተግበር የሚወደዱ ስራዎች

* አላህ እንዲህ በማለት ምሎባቸዋል። [ وَالْفَجْرِ وَلَيَالٍ عَشْرٍ] (በጎህ እምላለው በአስሩ ለሊቶችም) (አል ፈጅር)
* የታወቁ ቀናቶች ናቸው። አላህ እንዲህ ብሏል [وَيَذْكُرُوا اسْمَ اللَّهِ فِي أَيَّامٍ مَّعْلُومَاتٍ] (በታወቁ ቀኖችም ውስጥ የአላህን ስም ሊያወሱ) (አል ሀጅ)
* ከነዚህ ቀናቶች ውስጥ አንዷ የእርድ ቀን ናት። ይህም በአመት ውስጥ ከሚገኙ ቀናቶች ሁሉ ታላቅ ቀን ነው።
[أعظم الأيام عند الله يوم النحر ثم يوم القر]
رواه ابو داود والنسائي
(አላህ ዘንድ ታላቅ ቀን የእርድ ቀን ነው በመቀጠል የውመል ቀር ነው) አቡዳውድ እና ነሳኢይ ዘግበውታል ። የውመል ቀር ማለት የዙል ሂጃ 11ኛ ቀን ነው።
* በእነዚህ ቀናቶች የአምልኮዎች ሁሉ ቁንጮ የተባሉ ተሰብስበው ይፈፀማሉ። ከነሱም መሀል (ሶላት ፣ ፆም ፣ ሀጅ ፣ ሶደቃ)

@islamawe99
@islamawe99
104 views01:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-27 07:02:17 አብደላህ ኢብን መስዑድ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) ክፍል

<< ቁርኣንን በወረደበት ዓይነት ለመቅራት የፈለገ ሰው እንደ ኢብን ኡም አብድ ይቅራ >> (ረሱል ﷺ)

•••✿❒ ❒✿•••

~ ገና ወጣት እያለ የጉርምስና ዕድሜውን ሳይጨርስ ዑቅባ ኢብን ሙዐይጥ የተባለውን የቁረይሽ ሹም የከብት መንጋወች በመጠበቅ በመካ የተራራ ሰርጦች ላይ ብቻውን መመላለስ ልማዱ ነበር። ሰወች "ኢብን ዑም አብድ" (የባሪያ እናት ልጅ) ብለው ይጠሩት ነበር። እውነተኛ ስሙ ዐብደላህ ሲሆን የአባቱ ስም መስዑድ ነበር። ወጣቱ በወገኖቹ መካከል ስለታዩት ነቢይ ወሬወችን ሰምቶ የነበረ ቢሆንም በዕድሜውና ከመካ ህብረተሰብ በመራቁ ምክንያት አንዳችም ትኩረት አልሰጣቸውም ነበር።የዑቅባህን የከብት መንጋ ይዞ ገና ማለዳው ላይ መውጣት ልማዱ የነበረ ሲሆን ካልመሸ ደግሞ አይመለስም።

•••✿❒ ❒✿•••

~ አንድ ቀን መንጋዎቹን እየጠበቀ ሳለ ሁለት መካከለኛ ዕድሜና ግርማ ሞገስ የተላበሱ ሰወች ወደ እሱ ሲመጡ ከርቀት አየ። እንደ ደከማቸው ያስታውቁ ነበር። ከመጠማታቸውም የተነሳ ከንፈሮቻቸው ክው ብለው ደርቀዋል። ወደ እሱ ቀርበው ሰላምታ ከሰጡት በኋላ "አንተ ወጣት፥ የውሀ ጥማታችንን ለመቁረጥና ጉልበት ለማግኘት ብንችል እስኪ እባክህ ከነዚህ በጎች መካከል አንዷን እለብልን አሉት። ወጣቱም "አልችልም! በጎቹ የኔ አደሉም። የኔ ሥራ መጠበቅ ብቻ ነው ሲል መለሰላቸው። ሁለቱ ሰወች አልተከራከሩትም። ምንም እንኳ በውሃ ጥም እጅግ ተሰቃይተው የነበሩ ቢሆንም ቀና በሆነ መልሱ እጅግ ተደሰቱ።

•••✿❒ ❒✿•••

ደስታቸው በፊታቸው ላይ ይታይ ነበር። በእርግጥ ሁለቱ ሰወች የተባረኩት ነቢይና ﷺ ጓደኛቸው አቡበክር ሲዲቅ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) ነበሩ። የዚያን ቀን ወደ መካ ተራራወች የወጡት ከቁረይሽ ግፍና መከራ ለማምለጥ ነበር። ወጣቱም በተራው በነቢዩ ﷺ እና በጓደኛቸው ተደንቆ ወዲያውኑ ከእነሱ ጋር ተወዳጀ።አብደላህ ኢብን መስዑድ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) ሙስሊም ሆኖ ለነብዩ ግልጋሎት ለመስጠት ፈቃደኝነቱን ሲገልፅ ብዙም አልቆየም። ረሱል ﷺ በነገሩ ተስማሙበትና ከዚያ ቀን ወዲህ እድለኛው አብደላህ የበግ እረኝነቱን ተወ። በምትኩም የተባረኩትና የተወዳጁ ነብይ ﷺ የቅርብ አገልጋይነት ዋና ስራው ሆነ።

አብደላህ ኢብን መስዑድ ረዲየሏሁ ዐንሁ ከነብዩ ﷺ ጋር የቅርብ ወዳጃቸው እንደሆነ ቆየ። በቤታቸው ውስጥና ውጭ የሚያስፈልጋቸውን ነገር ሁሉ ያሟላ ነበር። መንገድ ሲሄዱና ዘመቻ ሲወጡ ያጅባቸዋል። ሲተኙ ይቀሰቅሳቸዋል። ሲታጠቡ ግርዶሽ ይሰራላቸዋል። ዕቃቸውንና የጥርስ መፋቂያቸውን ይይዝ ነበር። ሌሎች በግል የሚያስፈልጉ ዋቸውን ነገሮችም ያቀርብ ነበር። አብደላህ ኢብኑ መስዑድ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) በነብዩ ﷺ ቤተሰብ ውስጥ ልዩ ስልጠና (ተርቢያ) ተቀበለ። በረሱል ሶለሏሁ ዐልይሂ ወሰለም አመራር ስር ነበር።

•••✿❒ ❒✿•••

"በፀባይ ረሱልን ﷺ እጅግ በጣም የሚመስል ነበር።" እስከሚባል ድረስ እያንዳንዱን የእርሳቸውን ባህሪ ተላበሰ። አብደላህ በነብዩ ﷺ "ትምህርት ቤት" ውስጥ ነበር የተማረው። ከሶሐቦች መካከል ቁርኣንን በመሸምደድ በላጩ እሱ ነበር።ከሁሉም በተሻለ ሁኔታ ተረድቶትም ነበር። ስለዚህ በኢስላማዊ ሕገ-መንግስት (ሸሪዓ) ላይ ከሁሉም የላቀ ከፍተኛ እውቀት ነበረው። ይህንን ዑመር ኢብኑል ኸጧብ ረዲየሏሁ ዐንሁ በአረፋ ሜዳ ላይ ቆመው ሳሉ ወደ እሳቸው ከመጣውና እንደሚከተለው ከነገራቸው ሰው ታሪክ የተሻለ የሚያብራራ የለም፦ "የምእመናን መሪ ሆይ! ከኩፋ ነው የመጣሁት። የቁርኣኑን ቅጅወች ከአእምሮው እያፈለቀ የሚሞላ ሰው አጋጥሞኛል።" አላቸው። ዑመር እጅግ በጣም ተናደው በግመላቸው አጠገብ ይንጎባለሉ ጀመር። "እሱ ማነው?" ሲሉ ጠየቁት። "አብደላህ ኢብን መስዑድ ሲል መለሰ። የዑመር ቁጣ ወዲያው በረደ። ተረጋጉ። "በአላህ ስም እምላለሁ! በዚህ ጉዳይ ላይ ከእሱ የበለጠ አዋቂ ሌላ ሰው መኖሩን አላውቅም።

•••✿❒ ❒✿•••

ስለዚሁ አንድ ነገር ላጫውትህ" አሉ። ቀጠሉና "አንድ ቀን ማታ የአላህ መልእክተኛ ﷺ ከአቡበክር ጋር ሆነው ስለሙስሊሞች ይነጋገሩ ነበር። እኔም ከእነሱ ጋር ነበርኩ። ከጨረስን በኋላ ነብዩ ﷺ ሄዱ። እኛም ተከትለናቸው መስጊዱን አቋርጠን ስንሄድ እኛ ከሩቅ ያልለየነው በስግደት ላይ የቆመ ሰው ነበር። ነብዩ ﷺ ቆመው ሰውየው የሚለውን ከሰሙ በኋላ ወደእኛ ዞረው " ቁርኣንን በወረደበት ዓይነት ለመቅራት የፈለገ ሰው እንደ ኢብን ኡሙ አብድ ያንብብ" አሉ። አብደላህ ስግደቱን ጨርሶ ተቀምጦ ዱዓ እያደረገ ሳለ የአላህ መልእክተኛ ﷺ "ጠይቅ! ይሰጥሀል" አሉ።

ዑመር ንግግራቸውን ቀጠሉ..."ወደ አብደላህ ኢብን መስዑድ ረዲየሏሁ ዐንሁ። በቀጥታ ሄጀ ፀሎቶቹ ሁሉ ተቀባይነት ስለማግኝታቸው ነብዩ ﷺ የ ተናገሩትን የምስራች እነግረዋለሁ ብየ ወሰንኩ። ነገርኩትም። ነገር ግን ከእኔ በፊት አቡበክር ሄዶ የምስራቹን ነግሮት እንደነበር ተረዳሁ። በአላህ ስም እምላለሁ! አቡበክርን ጥሩ ነገር በመስራት ፈፅሞ ቀድሜው አላውቅም።" አብደላህ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) እንዲህ አይነት ከፍተኛ የቁርኣን ዕውቀት ከማግኘቱ የተነሳ። "ከእሱ በቀር ሌላ አምላክ የሌለ በሆነው እምላለሁ! እያ ንዳንዱ የቁርኣን አንቀፅ የት እንደወረደና የአወራረዱን ሁኔታ (ታሪካዊ አመጣጡን) እኔ ሳላውቅ አንዲትም የቁርኣን አንቀፅ አልወረደም።

•••✿❒ ❒✿•••

በአላህ ስም እምላለሁ! የአላህን መፅሐፍ የበለጠ የሚያውቅ ሰው መኖሩን ካወቅኩ ከእሱ ጋር ለመሆን የምችለውን ሁሉ አደርጋለሁ" ይል ነበር። አብደላህ ረዲየሏሁ ዐንሁ ስለራሱ የተናገረው እያጋነነ አልነበረም። ዑመር ኢብን ኸጧብ ረዲየሏሁ ዐንሁ ኸሊፋ በነበሩበት ወቅት ካደረጉዋቸው ረጅም ጉዞወች መካከል በአንደኛው አንድ "ካራቫን" (ሲራራ ነጋዴ) ያጋጥማቸዋል። ጥቅጥቅ ያለ ጨለማ ስለነበር የንግድ ቅፍለቱ በወጉ አይታይም ነበር። ዑመር ረዲየሏሁ ዐንሁ አንድ ሰው ቅፍለቱን እን ዲያናግር አዘዘ። "ከየት ነው የምትመጡት?" ሲሉ ዑመር ጠየቁ፤ "ከፈጀል-ዐሚቅ" (ከጥልቅ ሸለቆ) የሚል መልስ ተሰማ።

•••✿❒ ❒✿•••

ፈጀል-አሚቅ የሚለው አገላለፅ ቁርኣናዊ ነው። "እና ወዴት እየሄዳችሁ ነው?" ሲሉ ዑመር ጠየቁ፤ "ወደ አል- በይተል-ዓቲቅ (ወዳ ጥንታዊው ቤት) የሚል መልስ መጣ። (አልበይት አልአቲቅ የሚለው አገላለፅም ቁርኣናዊ ነው።) በዚህ ጊዜ ዑመር ኢብኑል ኸጧብ ረዲየሏሁ ዐንሁ "ከነሱ መካከል የተማረ ሰው (ዓሊም) አለ።" ካሉ በኋላ ተጨማሪ ጥያቄ እንዲጠየቅ አዘዙ። " ከቁርኣን ውስጥ ታላቁ ክፍል የቱ ነው?"፦ የሚከተለውን የቁርአን አያት አነበበላቸው.....

#ኢንሻአላህ #ይቀጥላል

የተለያዩ ጣፋጭ አስተማሪና ኢስላማዊ
ታሪኮች የሚቀርቡበት ምርጥ ቻናል ነው።

•════••• •••════•
ሼር JoiN & Share
https://t.me/AAASELEFYA
https://t.me/AAASELEFYA
91 views04:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-25 14:08:42 "ሰዕድ ኢብኑ አቢ ወቃስ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ክፍል " << ረሱል ﷺ እንዲህ አሉ፦ "ፊዳከ አቢ ወ ኡሚ ያ ሰዕድ (ሰዕድ ቀስስት! አባቴና እናቴ መስዋት ይሁኑልህ።>>] •••✿❒ ❒✿••• ሰውንም በወላጆቹ (በጎ እንዲያደርግ) በጥብቅ አዘዝነው፡፡ እናቱ ከድካም በላይ በሆነ ድካም አረገዘችው ጡት መጣያውም በሁለት ዓመት ውስጥ ነው። ለኔም ለወላጆችህም…
86 viewsedited  11:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-24 11:13:27 #የጁመዕ_ቀን_ከፊል_ህግጋቶች

عن أوس بن أوس رضي الله عنه قال :
قال النبي ﷺ :((إنَّ مِنْ أفْضَلِ أيَّامِكُمْ يَوْمَ الجُمُعَةِ فَأكْثِرُوا عَلَيَّ مِنَ الصَّلَاةِ فِيهِ ؛ فَإنَّ صَلَاتَكُمْ مَعْرُوضَةٌ عَلَيَّ))

➧ከአውስ ረዲየላሁ ዐንሁ የተያዘ ሀዲስ
ረሱላችን ሶላለሁ ዐለይሂ ወሰላም እንዲህ
አሉ ፦ ከበላጭ ቀኖቻችሁ ውስጥ ትልቁ ቀን ጁምዐ ነው በዚህ ትልቅ ቀን በኔ ላይ ሰላዋትን በብዛት አውዱብኝ ሰላዋታቹህ እኮ በተመደቡ መለኢካዎች አማካኝነት ወደ እኔ ይደርሰኛል።

رواه أبو داود.
አቡ-ዳውድ ዘግበውታል

اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى نَبِيِّنَا مُحَمَّدٍ

عن أنس بن مالك رضي الله عنه ،
عن النبي ﷺ أنه قال :
((الْتَمِسُوا السَّاعَةَ الَّتِي تُرْجَى فِي يَوْمِ الجُمُعَةِ بَعْدَ العَصْرِ إلَى غَيْبُوبَةِ الشَّمْسِ))

ከአነስ ረዲየላሁ ዐንሁ ከመልዕክተኛው ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰላም ያችን የጁመዕ ቀን ውስጥ ያለችውን ሰዐት ከዐስር ሶላት በኋለ እስከ ፀሐይ መግቢያ ድረስ ባለው ሰዐት ፈልጓት በዚች ሰዐት በዱዓ ጠንከር በሉ።
رواه الترمذي.
ቲርሚዚይ ዘግበውታል

عن زيد بن خارجة رضي الله عنه ،
أن رسول الله ﷺ قال : ((صَلُّوا عَلَيَّ وَاجْتَهِدُوا فِي الدُّعَاءِ ، وَقُولُوا : اللَّهُمَّ صَلِّ عَلَى مُحَمَّدٍ وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ))

➭ከዘይድ ኢብኑ ኸርጀታ አላህ መልካም ስራውን ይውደድለትና ረሱል ሶላላሁ ዐለይሂ ወሰላም እንዲህ አሉ ፦

➼በጁመዕ ቀን በኔ ለይ ሰላዋትን አውርዱ በዱዓ ለይ ታገሉ በሉም አላህ ሆይ በመሊክተኛው ሙሐመድ ሶላላሁ ዐለይሂ ወሰላም እና ባቤተሰባቸውም ለይ ሶለዋትህን ውዳሴህን አውርድ።
رواه النسائي.

«اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى نَبِيِّنَا مُحَمَّدٍ»

عن أبي سعيد الخدري رضي الله عنه ،
أن رسول الله ﷺ قال : غُسْلُ يَوْمِ الجُمُعَةِ وَاجِبٌ عَلَى كُلِّ مُحْتَلِمٍ

➷ ከአቢ ሰዒድ ኹድሪይ ረዲየላሁ ዐንሁ የተያዘ ሀዲስ መሊክተኛው ሶላላሁ ዐለይሂ ወሰላም እንዲህ አሉ፦የጁመዕ ቀን ለይ ትጥበት በሁሉም ለዒባደህ በደረሰ ሁሉ ሰው ላይ ግዴታ ነው።
رواه البخاري.
ኢማሙ ቡኻሪይ ዘግበውታል
76 views08:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-24 11:13:27 ሱረቱል ካህፍ
72 views08:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-23 17:11:38 ወንድሜ ሆይ አንተ ባለቤትህን ኢልምን እንድትማር ታጠናክራታለህን

ውዷ ባለቤትህን ልታበላት፣ ልታጠጣትና ልታስጌጣት ከምትጓጓው በላይ የዲን እውቀት እንድትማርና እንድትቀስም ልትጓጓላት ይገባል።

قَال عَمرُو ابنُ قَيسٍ -رَحمَهُ اللهُ-:
አምር ኢብን ቀይስ አላህ ይዘንለትና እንዲህ ብሏል።

إنَّ المَرأةَ لَتُخاصِمُ زَوجَهَا يَوم القِيامَة عِندَ اللهِ، فَتقُولُ: إنّهُ كانَ لا يُؤدِّبُنِي وَلا يُعلِّمُني شَيئًا، كَانَ يأْتِينِي بِخُبزِ السُّوق

አንድ ሚስት የውመል ቂያማ ባሏን አላህ ዘንድ ትሞግተዋለች። እንዲህም በማለት ትከሰዋለች።

አደብ አያስይዘኝም ነበር
ስለዲኔ ምንም አያስተምረኝም ነበር

ነገር ግን ብቻ ከሱቅ ዳቦ እያመጣ ሲመግበኝ ነበር ትላለች።

تَفسِيرُ السَّمعانِي (٤٧٥/٥)


•════••• •••════•
ሼር JoiN & Share
https://t.me/AAASELEFYA
80 views14:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-22 06:58:29 "ሰዕድ ኢብኑ አቢ ወቃስ
(ረዲየላሁ ዐንሁ) ክፍል "

<< ረሱል ﷺ እንዲህ አሉ፦ "ፊዳከ አቢ ወ ኡሚ ያ ሰዕድ (ሰዕድ ቀስስት! አባቴና እናቴ መስዋት ይሁኑልህ።>>]

•••✿❒ ❒✿•••

ሰውንም በወላጆቹ (በጎ እንዲያደርግ) በጥብቅ አዘዝነው፡፡ እናቱ ከድካም በላይ በሆነ ድካም አረገዘችው ጡት መጣያውም በሁለት ዓመት ውስጥ ነው። ለኔም ለወላጆችህም አመስግን በማለት (አዘዝነው)፣ መመለሻው ወደኔ ነው። ፨ ለአንተ በእርሱ ዕውቀት የሌለህን ነገር በእኔ እንድታጋራ ቢታገሉህም አትታዘዛቸው፡፡ በቅርቢቱም ዓለም፤ በመልካም ሥራ ተወዳጃቸው፡፡ ወደእኔም የተመለሰን ሰው መንገድ ተከተል፡፡ ከዚያም መመለሻችሁ ወደእኔ ነው፡፡ ትሠሩት የነበራችሁትንም ሁሉ እነግራችኋለሁ፤ (አልነው)፡፡ [ሉቅማን፥14-15]

•••✿❒ ❒✿•••

ከዚህ የቁርአን አንቀፅ ጋር የተያያዘ ብርቅዬ ታሪክ ያለው ግለሰብ ነው። ሰዕድ ኢብን አቢ ወቃስ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) ይባላል። ይህ ሶሐባ በጎ ነገር በተንኮል ላይ እምነት (ኢማን) በክህደት (ኩፍር) ላይ ድል ሲመቱ ያሳየናል። ሰዕድ ኢብን አቢ ወቃስ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) የዘር ሀረጋቸው ከልዑላን ጎራ ከሚያስፈርጃቸው ከመካ ወጣቶች አንዱ ነው። ነቢያዊ ብርሀን በመካ በፈነጠቀበት ወቅት ሰዕድ ገና አፍላ ወጣት ነበር። ርህሩህ አዛኝ ወላጆቹን ከመጠን በላይ ያፈቅርና ያገለግላቸው ነበር። በተለይ ከእናቱ ጋር ልዩ ትስስር ነበራቸው።


ሰዕድ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) ገና የ17 አመት ወጣት ቢሆንም አለባበሱ ግን የአዋቂወችና የትልቅ ሰወች ነበር። የዕድሜ አቻወቹ የሚያማልላቸው ነገሮች አያማልሉትም የዘወትር ትኩረቱ የጦር መሳሪያወችን መንከባከብ እና ኢልማ በመምታት ወታደራዊ ብቃቱን ማዳበር ነበር። ራሱን ለአንድ ከፍተኛ ተልዕኮ የሚያዘጋጅ ይመስላል። በአንፃሩ ሰዕድ ህዝቡ ያለበትን የእምነት ክስረትና የሞራል ድቀት ተቀብሎ ለመቆየት ህሊናው አልፈቀደለትም። አንድ ጠንካራ ሰው መጥቶ ህዝቡን ከጨለማ ህይወት ነፃ ማውጣት እንዳለበት ይሰማው ነበር። የመካና የመላው አለም ተጨባጭ ሁኔታ ከፍተኛ ዝቅጠትና ውድቀት ላይ ባለበት ወቅት ነበር...

•••✿❒ ❒✿•••

አላህ (ሱብሃነሁ ወተዓላ) ለሰው ልጅ እዝነትና ክብር ሲል ታላቅ ሰው የላከለት። የፍጡራን ሁሉ የበላይ የሆኑትን ሙሐመድ ኢብን ዐብደሏህ ﷺ እንዲነሱ ያደረገ። ለዚህ ቅንና የሐቅ ጥሪ ሰዕድ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) አስቸኳይ ምላሽ ነበር የሰጠው። ኢስላምን ከእርሱ በፊት የተቀበሉ ሰወች አስራ ሁለት ወይም አስራ ሶስት ሰወች ነበሩ። በከፍተኛ ኩራትም እንዲህ ይል ነበር፦ "ኢስላም ከፈነጠቀ በኋላ በክህደት የቆየሁት ለሰባት ቀናት ብቻ ነው። እኔ የኢስላም ሲሶ ነኝ።" ሰዕድ ሲሰልም ነብዩ ሙሀመድ ﷺ እጅግ በጣም ተደስተዋል። ምክንያቱም ግለሰቡ ከፍተኛ ተስፋ የሚጣልበትና ጀግና ሰው እንደሚሆን ከፊቱ ይነበብ ነበር።

•••✿❒ ❒✿•••

ይህ ጮርቃ ነገ ሙሉ ጨረቃ እንደሚሆን ታምኗል። ሰዕድ ልዑላን የሚባሉ ሰወች ውስጥ የሚመደብ በመሆኑም ወጣቶች የርሱን ተምሳሌት ሊከተሉ እንደሚችሉ እውን ነበር። ከዚህ በተጨማሪም ሰዕድ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) የነቢዩ ﷺ ዘመድም ነው በእናታቸው በአሚና በኩል። የሰዕድ ኢስላምን በቀበል ግን በቀላሉ የሚያልፍ አልሆነም። ብርቱ ፈተናና ውሳኔን ለመለወጥ የሚዳዳ ሙከራ ገጥሞታል። በዚህ ሳቢያም አላህ ተባረከ ወተዓላ የቁርኣንን አንቀፅ አውርዶለታል። ሰዕድ ረዲየሏሁ ዐንሁ ታሪኩን እንዲህ ሲል ራሱ ይገልፅልናል፦

በዚህ ሳቢያም አላህ ተባረከ ወተዓላ የቁርኣንን አንቀፅ አውርዶለታል። ሰዕድ ረዲየሏሁ ዐንሁ ታሪኩን እንዲህ ሲል ራሱ ይገልፅልናል፦ ከመስልሜ ሶስት ቀን በፊት በህልሜ አየሁ። በድቅድቅ ጨለማ በውሀማ አካል ውስጥ ያለሁ ይመስለኛል። ጥልቅ ወደሆነው ውሀ ስደርስ የጨረቃ ብርሃን ታየኝ። ብርሃን ወዳለበት ቦታ ከፊት ለፊት ቀድመው የሚጓዙ ሰወች ተመለከትኩ። ዘይድ ኢብን ሐሪስን፤ ዓሊይ ኢብን አቡ ጧሊብን እና አቡበክር ሲዲቅን (ረዲየሏሁ ዐንሁም አጅማኢን) አየኋቸው መቸ ነው እዚህ ቦታ የደረሳችሁት አልኳቸው? በቅርብ አሉኝ። በማግስቱ ሙሐመድ ﷺ የሚስጥር ዳእዋ እንደጀመሩ ሰማሁ።

•••✿❒ ❒✿•••

አላህ ለኔ በጎ ነገር እንደሻልኝ አወቅኩ ። በርሳቸው አማካኝነትም ከጨለማ ወደ ብርሃን ሊያወጣኝ መሆኑን ተረዳሁ። በፍጥነት ወደ እርሳቸው ሄድኩ። በአንድ የመካ ሸለቆ ስር ባለ ቤት ውስጥ አገኘኋቸው። ሶላት ሰግደው ጨርሰዋል። ኢስላምን ተቀበልኩ። በህልሜ ካየኋቸው ግለሰቦች ውጭ የቀደመኝ አልነበረም። ሰዕድ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) ኢስላምን ከተቀበለ በኋላ የገጠመውን ፈተናም እንዲህ በማለት ይገልፀዋል። "እናቴ መስለሜን ስትሰማ እጅግ በጣም ተበሳጨች። እናቴን ታዛዥና አፍቃሪ ወጣት ነበርኩ። ወደኔ በመምጣትም፦ 'ሰዕድ ሆይ! ...

የአባትህና የእናትህን ሃይማኖት በመተው ያቀፍከው ዲን (ሃይማኖት) ምንድን ነው? በፈጣሪ ስም እምላለሁ አዲሱን ሃይማኖትህን መተው አለብህ። አሊያ ግን እስከምሞት ድረስ አልበላም፥ አልጠጣም። ልብህም በእኔ ሀዘን እንደተቆራመተ ይኖራል። በሰራኸው ተግባር ፀፀት ይወርስሀል። ሰወችም ዝንተ ዓለም በአድራጎትህ ሲያነውሩህ ይኖራሉ። አለችው። "እሱም እናቴ ሆይ!፥ ይህንን ነገር አትፈፅሚ። እኔ ሃይማኖቴን ለምንም ነገር ስል አልለውጥም" አልኳት። እርሷ ግን በዛቻ ብቻ አልተወሰነችም። መብላትና መጠጣቷን አቆመች። ለተወሰኑ ቀናትም በዚሁ ሁኔታ ቀጠለች። አካሏ ተዳከመ። አጥንቷ ተዝለፈለፈ፥ ኃይሏ ሟሸሸ።

•••✿❒ ❒✿•••

በተደጋጋሚ በመመላለስ ጥቂት ህይወቷን ሊያቆይ የሚችል ምግብና መጠጥ እንድትወስድ አቀረብኩላት። እምቢታዋ ግን ከፍተኛ ነበር። እኔ ሃይማኖቴን እስካልተውኩ ድረስም እስትንፋሷ እስኪቋረጥ ድረስ እንደማትበላና እንደማትጠጣ በመሀላዋ አረጋገጠችልኝ። በዚህ ወቅት እንዲህ አልኳት፦ "እናቴ ሆይ! እኔ በጣም እወድሻለሁ። ነገር ግን ላንች ያለኝ ውዴታ ለአላህና ለመልእክተኛው ﷺ ካለኝ ፍቅር የሚበልጥ አይደለም። በአላህ ስም እምላለሁ! ለአንች አንድ ሺህ ነፍስ ቢኖሩሽና አንዱ ነፍስ ወጥቶ ሌላው እየተተካ ቢትቆይ እንኳን ይህንን ሃይማኖት አልተውም።"

•••✿❒ ❒✿•••

ፅናቴን ስትመለከት በከፍተኛ ጥላቻ መብላትና መጠጣት ጀመረች። በዚህ ሳቢያ ነበር አላህ ሱብሐነሁ ወተዓላ ይህን አንቀፅ ያወረደው፦

وَإِن جَٰهَدَاكَ عَلَىٰٓ أَن تُشْرِكَ بِى مَا لَيْسَ لَكَ بِهِۦ عِلْمٌۭ فَلَا تُطِعْهُمَا ۖ وَصَاحِبْهُمَا فِى ٱلدُّنْيَا مَعْرُوفًۭا ۖ
ለአንተ በእርሱ ዕውቀት የሌለህን ነገር በእኔ እንድታጋራ ቢታገሉህም አትታዘዛቸው፡፡ በቅርቢቱም ዓለም፤ በመልካም ሥራ ተወዳጃቸው፡፡ [ሉቅማን፥15]


የተለያዩ ጣፋጭ አስተማሪና ኢስላማዊ
ታሪኮች የሚቀርቡበት ምርጥ ቻናል ነው።

•════••• •••════•
ሼር JoiN & Share
https://t.me/AAASELEFYA
https://t.me/AAASELEFYA
94 views03:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-20 12:34:59 የ ሀጅ ና ኡምራ ት/ት ክፍል 3
https://t.me/ustazAbdalmajid
83 views09:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-19 09:00:17 ስለ አምላካችን አላህ ያስተማሩት ከፊል ነቢያት።

"ኑሕ"
11:25-26 ኑሕንም ወደ ሕዝቦቹ በእርግጥ ላክን፤ አላቸውም ፦ እኔ ለናንተ ግልጽ አስፈራሪ ነኝ። አላህን እንጂ ሌላን አትገዙ፤ እኔ በናንተ ላይ የአሳማሚን ቀን ቅጣት እፈራላችኋለሁና።

"ሁድ"
11:50 ወደ ዓድም ወንድማቸውን ሁድን ላክን አላቸው ፦ ወገኖቼ ሆይ አላህን ተገዙ ከእርሱ ሌላ ምንም አምላክ የላችሁም፤ እናንተም ቀጣፊዎች እንጂ ሌላ አይደላችሁም።

"ሷሊህ"
11:61 ወደ ሠሙዶችም ወንድማቸውን ሷሊህን ላክን፤ ፦ሕዝቦቼ ሆይ አላህን ተገዙ፤ ከርሱ ሌላ ለናንተ አምላክ፣ የላችሁም፤ .. አላቸው።

"ኢብራሒም"
19:48 እናንተንም ከአላህ ሌላ የምትግዙትንም እርቃለሁ፤ ጌታየንም እግዛለሁ፤ ጌታየን በመገዛት የማፍር አለመኾኔን እከጅላለሁ።

ሹዐይብ"
11:84 ወደ መድየንም ወንድማችውን ሹዐይብን፣ ላክን፤ አላቸው ሕዝቦቼ ሆይ! አላህን ተገዙ፤ ከርሱ ሌላ ለናንተ አምላክ የላችሁም፤ ስፍርንና ሚዛንንም አታጉድሉ፤ እኔ በጸጋ ላይ ሆናችሁ አያችኋለሁ፤ እኔም በናንተ ላይ የከባቢን ቀን ቅጣት እፈራለሁ።

"ሙሳ"
7:104-105 ሙሳም አለ፦ፈርኦን ሆይ! እኔ ከዓለማት ጌታ የተላክሁ መልክተኛ ነኝ፤ በአላህ ላይ ከእውነት በቀር አለመናገር ተገቢዬ ነው፤ ከጌታችሁ በታምር በእርግጥ መጣኋችሁ፤ የእስራኤልንም ልጆች ከኔ ጋር ልቀቅ።

ኢሳ"
3:51 አላህ ጌታየና ጌታችሁ ነዉ፤ ስለዚህ ተገዙት፤ ይህ ቀጥተኛ መንገድ ነዉ አላቸዉ።
89 views06:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ