Get Mystery Box with random crypto!

ትምህርተ አበው

የቴሌግራም ቻናል አርማ fgonfa — ትምህርተ አበው
የቴሌግራም ቻናል አርማ fgonfa — ትምህርተ አበው
የሰርጥ አድራሻ: @fgonfa
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 354
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የአባቶቻችንን ትምህርት የምንማማርበት መንፈሳዊ ገጽ ነው።
ለሃሳብ አስተያየቶ @fgonfa

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-05-31 12:22:54
207 viewsፍቅር በ ኢትዮጵያ, 09:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-29 07:21:42
“ታላቅ ምልክትም በሰማይ ታየ ፀሐይን ተጐናጽፋ ጨረቃ ከእግሮችዋ በታች ያላት በራስዋም ላይ የአሥራ ሁለት ከዋክብት አክሊል የሆነላት አንዲት ሴት ነበረች።”
ራእይ 12፥1

ግንቦት 21 ቀን እመቤታችን ንጰጽሕይት ድንግል ማርያም በደብረ ምጥማቅ በስሟ በተሰራች ቤተክርስቲያን ጉልላት ላይ በብርሃን መርከብ ተቀምጣ በግልፅ ለአምስት ቀን መታየቷን እንዘክራለን።

በዚህም ሕዝብም አህዛብም ለአምስት ቀን ያክል ተመልክተዋታል ወደ ቤታቸው ሲሄዱም ትባርካቸው ነበር።

አምላክን የወለደች እመቤታችን ድንግል ማርያም ሁላችንን ትባርከን እናትነቷ አማላጅነት ከሃገራችን ከኢትዮጵያ እና ከሁላችንም ጋር ይሁን።
180 viewsፍቅር በ ኢትዮጵያ, 04:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-08 16:40:58 "የዓለም ሁሉ እመቤት ተወለደች"

እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የልደት በዓል አደረሳችሁ።የድንግል ማርያም ልደት የሁላችን ልደት ነውና እርሷን የሰጠን አምላክ ክብር ምስጋና ይግባው።



(ሊቁ አባ ሕርያቆስ) በድርሰቱ"ድንግል ሆይ በኃጢአት ፍትወት የተፀነስሽ አይደለም በሕግ በሆነ ሩካቤ ከሐና ከኢያቄም ተወለድሽ እንጂ"አ
እየለ የልደቷን ነገር ያደንቃል።

የተባረኩ ቅዱስ ኢያቄም እና ቅድስት ሃና ግንቦት ፩ ቀን ይህችን ብርክት ልጅ ወለዱ ስሟንም ማርያም አሏት።

ማርያም ማለት:- ጸጋ ወሀብት ማለት ነው ለጊዜው ለወላጇቿ ለፍፃሜው ለሁላችን ጸጋና ሀብት ሆና ተሰታለችና።
ማርያም ማለት:- ፍጽምት ማለት ነው መልክ ከደምግባት አሟልታ ይዛለችና በኋላም በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ ጸንታ ኖራለች።
ማርያም ማለት:- መርሕ ለመንግስተ ሰማያት ማለት ነው በምልጃዋ ሁላችንን ከልጇ አማልዳ መርታ መንግስተ ሰማያት ታስገባናለችና።
ማርያም ማለት:- ከሁለት ቃላት የተገኘ ነው እርሷም ሁለቱን መስተፃርራን አስተባብራ ይዛለችና እናትነትን ከድንግልና። ማር:- በምድር ያለ ጣፋጭ ያም:- በገነት ያለ ጣፋጭ ምግብ ነው ማርያም በምድር በደቂቀ አዳም በሰማይ በመላእክት ስሟ ጣፋጭ ነውና።

የከበረች ቅድስት ሃና የብጽአት ልጇን ነሃሴ 7 ቀን ጸንሳ በፈቃደ እግዚኣብሔር ግንቦት ፩ ቀን በሊባኖስ ተራራ
ወልዳታለች።

የመወለድዋ ደስታ ለቤተሰቦቿ ብቻ አይደለምና የዓለም ደስታ ድንግል ማርያም ከቤት ውጭ በተራራ ስር ተወለደች በቤት ወልደዋት ቢሆን ደስታው በእነርሱ በቀር ነበር የልደቷ ደስታ ግን ለሁላችን ነው በተለይ ለኦርቶዶክሳውያን።

ቅድስት ሃና ሆይ "እንኳን ልጅሽ ማረችሽ" ለሌሎች ሴቶች በወለዱ ግዜ እንኳን ማርያም ማረችሽ እንላለን አንቺ ግን የምትምርሽን ወልደሻታልና።

(ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ እንዲህ እያለ ያመሰግናል) "የእግዚአብሔር ልጆች እንግዲህ ይህችን ንጽህይት ሙሽራ የወለዱልንን ኢያቄምንና ሐናን እናድንቃቸው፤የማትነቀፍ የእስራኤል ድንግል የተባረከችይቱም ፍሬ የፈራችባት የሩካቤያቸው ንጽህይት ቀን እንደምን ያለች ናት? ከይሁዳ ወገን የምትሆኝ ንጽህይት ርግብ ለመጸነስሽ የእግዚአብሔር ፈቃድ የሆነባት የመገናኘታቸው ቀን እንደ ምን ቅድስት ናት?የንጉሥ አዳራሽ የምትሆን የእርሷ መሠረት የተመሰረተባት ዕለት እንደምን ደስ ያለች ናት? (አርጋኖን ዘሐሙስ)


አደራ በዓሉን ከፍፁም ክርስቲያናዊ ሥርዓት ሳንወጣ በአግባብ እናክብር ቅድስት ሃና እና ዘመዶቿ በዓሉን ለ15 ቀን በውጭ እንዳከበሩት አንድም ድንግል ማርያም ከቤት ውጭ እንደተወለደች አብነት በማድረግ ከቤታችን ውጭ በተለያየ ሥርዓት እንደየአቅማችን እናከብራለን የበዓሉ አከባበር ከጥቂት ጊዜያት ወዲህ ቅርጽ እየቀየረ ወደ ባዕድ አምልኮ እየዞረ መቷል ኦርቶዶክሳውያን በዓሉን ድንግል ማርያም ባለ ልደቷ በምትደሰትበት መልኩ ብቻ ማክበር ይገባናል።

እመቤቴ ሆይ እኔን ኋጥኡን ባርያሽን በምልጃሽ አስቢኝ።

የግንቦት ልደታ ዋዜማ/2014
ዲ/ን ፍቃዱ ጎንፋ (ዘፍቁረእግዚእ)
338 viewsፍቅር በ ኢትዮጵያ, 13:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-01 07:42:59 #####ቶማሶች እመኑ #######
እንኳን ለዳግማ ትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ። አደረሰን።
የዳግም ትንሳኤ ነገር እንዴት ነው ቢሉ:- አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሦስት ቀን ሦስት ሊሌት(33 ሰዓት) በከርሰ መቃብር ከቆየ በኋላ መግነዝ ፍቱልኝ መቃብር ክፈቱልኝ ሳይል ሙስና መቃብር(በስጋ መፍረስ መበስበስን) ሳያገኘው ሞትና መቃብርን ድል አድርጎ መግነዝ ፍቱልኝ መቃብር ክፈቱልኝ ሳይል ለትንሣኤያችን በኩር ሆኖ ተነስቷል።
የክርስቶስን መነሳት አስቀድሞ የተገለፀው #ለሴቶች ነበር ሰው የመሆኑ ነገር ቀድሞ ለሴት(#ለድንግል _ማርያም) እንደተነገረ ሁሉ ከሙታን መነሳቱም አስቀድሞ ለሴት(ለመቅደላዊትማርያም)ተገልፆአል(ዮሐ 20፥16)።
እርሷም ለሐዋርያት ሄዳ ነግራቸው ነበር ከዚህ በኋላ ለቅዱስ ጴጥሮስ(ሉቃ 24፥34)፣
ወደ ኤማሁስ ተስፋ ቆርጠው ለተመለሱት አርድእት ከተገለፀ በኋላ(ሉቃ 24፥15)
ለሐዋርያት ሁሉ በተዘጋ ማህፀን አድሮ ሰው የሆነ አምላክ በተዘጋ በር ገብቶ ሰላምን ሰብኮላቸዋል(ሉቃ 24፥36)።
ትንሣኤውን ክርስቶስ ለሐዋርያት ሲገልፅ ከእነርሱ መሃል ቶማስ አልነበረም ነበርና (ዮሐ 20፥24) እንዴት እኔ ትንሣኤውን ሳላይ ቢል ክርስቶስ ደግሞ #በ8ተኛው ቀን ትንሣኤውን ለሐዋርያት ገለፀ ዳግም ትንሣኤ ይህ ነው።
#የቶማስ _አለማመን
ሊቃውንት ቤተ ክርስቲያን የቶማስን አለማመን የእግዚአብሔር መለኮታዊ ሐሳብ ነው ብለው ይፈቱታል። ባይጠራጠር ባላየው አይቶትም እጁን ከቶ ባልዳሰሰው ባይዳስሰው የክርስቶስን አምላክነት ባልመሰከረ በመመስከሩ ደግሞ የሁሉን እምነት ጨምሯል።(ዮሐ 20፥31)ደግሞስ ይላሉ መተርጉማን ሐዋርያት ክርስቶስ ከሞት ተነሳ ብለው ሲያስተምሩ። #ቶማስ መነሳቱን ሐዋርያት ነገሩኝ ቢል ማን ትምህርቱን ይቀበለው ነበር???
የቶማስ አለማመን ለ8 ቀን የቆየ ነው የተወጋ ጎኑን ዳሶ ትንሳኤውን አይቶ "#ጌታዬ _አምላኬም" ብሎ መስክሯል(ዮሐ 20፥28)።
ቶማስ ጌታዬ አምላኬም በማለት የመሰከረው እግዚኣብሔር ፍፁም ሰው ፍፁም አምላክ መሆኑን(ምስጢረ ሥጋዌን) ነው።ቶማስ ክርስቶስን ከዳሰሰ በኋላ ጌታዬ አለ አምላኩን ሥጋን ተዋሕዶ በሰው አካል ዳሶታልና ጌታዬ አለ።የዳሰሰው አካል ሩቅ ብእሲ ያልሆነ መለኮትን የተዋሐደ ነውና አምላኬም አለ።ቶማስ ጌታዬ አምላኬም ብሎ የመሰከረው ሌሎች እንዳሉት ሲዳስ ደንግጦ የደነገጠ የሚለውን እንደማያውቅ ሆኖ አልነበረም በፍፁም አምኖ እንጂ ለዚህም ማስረጃችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተናገረው ቃል ነው
"ኢየሱስም ስለ አየኸኝ አምነሃል፤ ሳያዩ የሚያምኑ ብፁዓን ናቸው አለው" ዮሐ 20፥29
ተመልከቱ ስለ አየኸኝ አምነሃል አለው እንጂ ስለ ደነገጥክ መስክረሃል አላለውም።ቶማስስ አይቶ ዳስሶ አመነ በሐዋርያት ስብከት የምናምን እንደ አባ ህርያቆስ "ከርሱም ጋር በላን ጠጣን..." ስለምንል ስለ እኛም ብፅዕና ተመስክሮልናል።እስከ አሁን የክርስቶስን አምላክነት ያላመኑ ያልመሰከሩ ቶማሶች ግን ብዙ ናቸው(ልብ ይስጥልን) ንዋየ ኅሩይ ቅዱስ ጳውሎስ ለገላትያ ክርስቲያኖች እንዲህ ይላቸዋል:-
"የማታስተውሉ የገላትያ ሰዎች ሆይ፥ በዓይናችሁ ፊት ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ተሰቀለ ሆኖ ተሥሎ ነበር፤ ለእውነት እንዳትታዘዙ አዚም ያደረገባችሁ ማን ነው?" ገላ 3፥1
እኔም እንዲህ እላለሁ የማታስተውሉ መናፍቃን ሆይ የእግዚአብሔር ልጅ እግዚኣብሔር መሆኑን እንዳታስተውሉ ማን አዚም አደረገባችሁ፤የማታስተውሉ መናፍቃን ሆይ ቶማስ አምላክነቱን የመሰከረለትን ክርስቶስን አምላክ ብላችሁ እንዳትቀበሉ አዚም ያደረገባችሁ ማነው???
እኛስ አባቶቻችን በተረዳ ነገር እንዳስተማሩን ወልደ አብ ወልደ ማርያም ክርስቶስ በተዋሕዶ ሰው የሆነ አምላክ ነው ብለን እናምናለን።
መልካም የትንሣኤ በዓል።


አጽራረ ቤተክርስቲያንን ያስታግስልን።



ዲ/ን ፈቃዱ ጎንፋ (ዘፍቁረእግዚእ)
200 viewsፍቅር በ ኢትዮጵያ, 04:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-24 10:30:17
197 viewsፍቅር በ ኢትዮጵያ, 07:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-23 07:15:22 ሦስት ቀን እና ሦስት ሌሊት በመቃብር

የክርስቶስ በከርሰ መቃብር ሦስት ቀን ሦስት ሌሊት የመቆየቱ ነገር እንዴት ነው ብላችሁ ለጠየቃችሁኝ በሙሉ አቆጣጠሩን ይህን ይመስላል:-

በመጀመሪ ጌታችን ከሦስት ቀን በኋላ እንደሚነሳ የተናገሩ ትንቢቶችን ምሳሌዎችን እና እራሱ በመዋዕለ ስብከቱ ያስተማረውና እንመልከት።

“ዮናስ በዓሣ አንባሪ ሆድ #ሦስት #ቀንና #ሦስት #ሌሊት እንደ ነበረ፥ እንዲሁ የሰው ልጅ በምድር ልብ #ሦስት #ቀንና #ሦስት #ሌሊት ይኖራል።” — ማቴዎስ 12፥40 “

በኋላም ሁለት ቀርበው፦ ይህ ሰው፦ የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ አፍርሼ #በሦስት ቀን ልሠራው እችላለሁ ብሎአል አሉ።”— ማቴዎስ 26፥6

“የሰው ልጅ ብዙ መከራ ሊቀበል፥ ከሽማግሌዎችም ከካህናት አለቆችም ከጻፎችም ሊጣል፥ ሊገደልም #ከሦስት ቀንም በኋላ ሊነሣ እንዲገባው ያስተምራቸው ጀመር፤ ቃሉንም ገልጦ ይናገር ነበር። ማርቆስ 8፥31


ሦስት ቀን እና ሦስት ሌሊት አቆጣጠሩ

ከአርብ 12 ሰዓት በፊት ያለው የመዘጋጃ ቀን ይባላል ይኽም ማለት ስንበት አይደለም ማለት ነው። ጌታ ወደ መቃብር የወረደው አርብ 11ሰዓት ስለሆነ የአርብን ቀንና ሌሊት ጠቅሎሎ ስለሚይዝ እንደ አንድቀን ይቆጠራል። ከአርብ 12 ሰዓት እስከ ቅዳሜ 12 ሰዓት ሁለተኛ ቀን ይሆናል።
ከቅዳሜ 12 ጌታ እስከ ተነሳባት ሊሌት ያለችው እንደ አንድ ሙሉ ቀን ይቆጠራል።

በሌላ አቆጣጠር

አርብ ከጠዋቱ 12 ጀምሮ እስከ 6 ሰዓት ቀን ነበር። አንድ ቀን ከስድስት ሰዓት እስከ ዘጠኝ ሰዓት ቀኑ ጨልሞ ነበር።አንድ ቀን አንድ ሌሊት።

ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት እስከ 12ሰዓት ደግሞ ቀን ሆኖል አንድ ቀን ከምሽቱ 12 ሰዓት እስከ ጠዋተ 12 ደግሞ አንድ ሌሊት ሁለት ቀን ሁለት ሌሊት ሆነ

የቅዳሜ ቀን እና ሌሊት ሦስት ቀን ሶስት ሌሊት በማለት በቤተክርስቲያን ሊቃውንት ይቆጠራል።


ዕለተ ዓርብ ፈጥሮን ዕለት ዓርብ ያዳነን የድንግል ማርያም ልጅ ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም ያድርሰን።



" ገብረ ሰላም በመስቀሉ ትንሣኤሁ አግሃደ "


ዲ/ን ፍቃዱ ጎንፋ (ዘፍቁረእግዚእ)
ለቀዳም ሥዑር/2014
189 viewsፍቅር በ ኢትዮጵያ, 04:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-22 09:45:11
“አውቀውስ ቢሆኑ የክብርን ጌታ ባልሰቀሉትም ነበር፤”1ኛቆሮ 2፥8

ዕለተ ዓርብ።
ዕለተ ይቅርታ ።
ዕለተ ስቅለት ።
ዕለተ ፍቅር።
ዕለተ መከራ።

እንኳን አደረሳችሁ።


ሠዓሊ ገብረክርስቶስ ደስታ እንደሳለው።
161 viewsፍቅር በ ኢትዮጵያ, 06:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-20 22:35:27 "ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት አለ"
ሉቃ 22፥19

በስመ አብ ወወልድ መንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን።
የተከበራችሁ የክርስቶስ ቤተሰቦች እንደምን ከርማችኋል እንኳን ለጸሎተ ሐሙስ አደረሳችሁ።
በዚህች ቀን ከተፈፀሙ ምስጢራት መካከል አንዱ ምስጢረ ቁርባን ነውና ስለ ቅዱስ ቁርባን ጥቂት እንነጋገር።ከላይ መግቢያ ያደረግነውን ጥቅስ በመያዝ ከእኛ እምነት በአፋ ያሉ ሰዋች(መናፍቃን) ለመታሰብያ አድርጉ ብሏቸዋልና መታሰብያ ነው እንጂ አማናዊ አይደለም ብለው ይሞግቱናል የእኛ ቤተክርስቲያን ሊቃውንት ምን ይላሉ:-

++++++++እውን መታሰብያ ነውን++++++

መናፍቃኑ መታሰብያ ለማለት የሚጠቅሱት ጥቅስ ይህ ነው" ስለ እናንተ የሚሰጠው ሥጋዬ ይህ ነው ይህን ለመታሰብያዬ አድርጉት" ሉቃ22፥19 ነገር ግን ኢየሱስ ክርስቶስ ይህንን ቃል የተናገረው እነርሱ መስሏቸው በተረዱበት "በተረጎሙበት" አግባብ አይደለም ይልቁኑ ይህ ቃል እንዴት ይታያል ካላችሁ ተከተሉኝ:-

ይህንን ቃል ከሉቃስ ወንጌል በተጨማሪ በማቴዋስ ወንጌልም እናገኘዋለን "ሲበሉም ኢየሱስ እንጀራን አንሥቶ ባረከ ቈርሶም ለደቀ መዛሙርቱ ሰጠና። እንካችሁ፥ ብሉ ይህ ሥጋዬ ነው አለ። ሲበሉም ኢየሱስ እንጀራን አንሥቶ ባረከ ቈርሶም ለደቀ መዛሙርቱ ሰጠና። እንካችሁ፥ ብሉ ይህ ሥጋዬ ነው አለ። ስለ ብዙዎች ለኃጢአት ይቅርታ የሚፈስ የአዲስ ኪዳን ደሜ ይህ ነው" ማቴ 26፥26-28 በዚህ ቃል አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ህብስቱ አማናዊ ሥጋው ወይኑ አማናዊ ደሙ እንደሆነ ገለጠ እንጂ መታሰብያ አድርጉት አላለም።

የጌታ ሥጋና ደም መታሰብያ ሳይሆን አማናዊ ነው ይህንንም ንዋየ ህሩይ ቅዱስ ጳውሎስ እንዲህ ይገልጸዋል "ስለዚህ ሳይገባው ይህን እንጀራ የበላ ወይም የጌታን ጽዋ የጠጣ ሁሉ የጌታ ሥጋና ደም ዕዳ አለበት" 1ቆሮ 11፥27 አስተውሉ መታሰብያውን ሳያስብ ቢቀር አላለም ይልቁኑ ሳይገባው የተቀበለ አለ እንጂ ስለዚህ የተገባቸው ብቻ ከርሱ ሊቀበሉት የሚገባ አማናዊ እንጂ መታሰብያ አይደለም ይህንንም እራሱ ባለቤቱ ኢየሱስ ክርስቶስ እንዲህ ብሎ በትእዛዝ አስቀመጠው "ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው፥ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ" ዮሐ 6፥54 ተመልከቱ ሥጋዬንና ደሜን የሚቀበል አለ እንጂ መታሰብያ የሚያደርገው አላለም ስለዚህ አማናዊ እንጂ መታሰብያ አይደለም።

ሊቁ አባ ሕርያቆስ እንዲህ ይላል"በበግ በጊደር በላህም ደም እንደነበረው እንደ ቀደሙት አባቶች መስዋዕት አይደለም እሳት ነው እንጂ፤ ፈቃዱን ለሚፈፅሙ ልብናቸውን ላቀኑ ሰዋች የሚያድን እሳት ነው ስሙን ለሚክዱ ለአመፀኞች ሰዎች የሚባላ እሳት ነው፤ እሳታውያን የሚሆኑ ሱራፌልና ኪሩቤል ሊነኩት የማይቻላቸው በእውነት እሳት ነው"(ቅዳሴ ማርያም)

ስለዚህ እንደሚሉን መታሰብያ ሳይሆን ሊቁ እንዳስተማረን በንፅህና ብንቀበለው ሕይወት የሚሰጠን አማናዊ ነው።

++ታድያ ለምን ለመታሰብያዬ አድርጉት አለ++

ይህንን ቅዱስ ጳውሎስ እንዲህ ብሎ ያስረዳናል
" እንደዚሁም ከእራት በኋላ ጽዋውን ደግሞ አንሥቶ። ይህ ጽዋ በደሜ የሚሆን አዲስ ኪዳን ነው፤ በጠጣችሁት ጊዜ ሁሉ ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት አለ። ይህን እንጀራ በበላችሁ ጊዜ ሁሉ፥ ይህንም ጽዋ በጠጣችሁ ጊዜ ሁሉ ጌታ እስኪመጣ ድረስ ሞቱን ትናገራላችሁና" 1ቆሮ 11፥25
ስለዚህ ቅዱስ ጳውሎስ እንዳስተማረን አማናዊ የክርስቶስን ሥጋ እና ደም ስንቀበል ሞቱን ማሰብ ህማማተ መስቀልን መዘከር ይገባል ለዚህ ነው በቅዳሴያችን "ንዜኑ ሞተከ..." እያልን ሊቁ አፈ በረከት ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ በቅዳሴው "የምትወዱት አልቅሱለት" እንዳለ የምንወደው ዋጋ የተከፈለልን እኛ አማናዊውን የክርስቶስን ሥጋ እና ደም ስንቀበል ሞቱን ሕማሙን ለእኛ ሲል የተቀበለውን መከራ ሁሉ መታሰብያ (ምሳሌ) አድርገን ልንቀበል ይገባል እንጂ ሥጋ ወደሙ አማናዊ ነው። ሲሰጠንም እንዲህ ብሎናል "ይህ ህብስት ሥጋዬ ነው ይህ ወይን ደሜ ነው" ማር 14፥22 መታሰብያ ሳይሆን ዘላለማዊ ሕይወት የምናገኝበት አማናዊ ነው።ንሰሐ ገብተን ሥጋውን በልተን ደሙን ጠጥተን የስሙ ቀዳሽ የክብሩ ወራሽ ያደርገን ዘንድ የድንግል ማርያም ምልጃ የቅዱሳን ጥባቆት አይለየን።
አሜን።

እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ጻማ ወድካም ዓመ ከመ ዮም ያብጽሐነ ያብጽሕክሙ እግዚአብሔር በፍስሐ ወበሰላም።

ዲ/ን ፍቃዱ ጎንፋ (ዘፍቁረእግዚእ)
ጸሎተ ሐሙስ(2014)
156 viewsፍቅር በ ኢትዮጵያ, 19:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-20 22:33:37
130 viewsፍቅር በ ኢትዮጵያ, 19:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ