Get Mystery Box with random crypto!

"ኡማ ቲቪ " Tv

የሰርጥ አድራሻ: @ethioomahtvchannle
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 44.00K
የሰርጥ መግለጫ

መረጃወችን ለወዳጄ ዘመድ ሼር ያርጉ!
የቴሌግራም ቻናላችን ከስር በሊንኩ ይቀላቀሉ👇
https://t.me/ UAKV32q7U2HKzEMf

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2024-05-16 14:50:17 ሀገራዊ ምክክሩ ሙስሊሙን ያገለለ የተሳታፊ ልየታ እንደተደረገበት ተገለፀl
በኢትዮጲያ በመጪው ለሚካሄደው ሀገራዊ ምክክር የሙስሊሙ ቁጥር አነሳ በመሆኑ የተሳታፊዎች ልየታ  በድጋሚ እንዲካሄድ እና በሙስሊሙ በኩል የቀረቡ አጀንዳዎች በሀገራዊ ምክክሩ እንዲካተቱ  የኢትዮጲያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ጥሪ አቀረበ።

ጠቅላይ ምክር ቤቱ ባቀረበው ጥያቄ የሙስሊሞች ተሳትፎ በሕዝባችን ቁጥር ልክ መሆን ያለበት በመሆኑ የተሳታፊዎችና የአወያዮች ቁጥር በዚሁ መሠረት በኮሚሽኑ "የአካታችነት መርህ መሠረት ጠ/ም/ቤቱ ያቀረበውን የሕዝበ ሙስሊሙ የምክክር እጀንዳዎች ለጉባኤው ለማሰማት፤ ለማብራራት የሚችሉ ተገቢ ቁጥር ያላቸው ሙስሊም ተወካዮች እንዲካተቱ ይቻል ዘንድ የህዝብ ጥያቄዎች ከፍተኛ እየሆነብን በመምጣቱ ሥብጥሩ በፍትሃዊነት እንደገና እንዲቃኝ ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ የበላይ ጠባቂ ለሆኑት  ለፕሮፌሰር መስፍን አርአያ በፃፈው ደብዳቤ ጠይቋል።

በኢትዮጵያ የተለያዩ አገራዊ ጉዳዮች ላይ መግባባት ለመፍጠር ይችላል የተባለው የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአዋጅ ተቋቁሞ የተለያዩ ተግባራትን ሲያከናውን መቆየቱ የሚታወስ ሲሆን  ኮሚሽኑ ከትግራይ ክልል ውጪ እና ግጭት ባለባቸው የአማራ እና የኦሮሚያ ክልልች አንዳንድ አካባቢዎችን ሳያካትት በ10 ክልሎችን እና የከተማ አስተዳደሮች ለምክክሩ የሚሳተፉ አካላትን ልየታ ቢያካሂድም የሙስሊሙ ቁጥር አነስተኛ መሆኑ ተገልጿል፡፡

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ተወካዮች ከሀገራዊ ምክክሩ "3"ኮሚሽነሮች ጋር  ውይይት ማድረጋቸው የተገለፀ ሲሆን በባለሙያ በተሰጠ መግለጫ ላይም  በተሳታፊና በአወያይ ደረጃ የሙስሊሞችን ተሳትፎ እንዲነገረን ብንጠይቅም ከምክክር ኮሚሽኑ ምላሽ እንዳልተሰጠ በሰጠው መግለጫ ላይ አስታውቋል፡፡

ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ውሳኔውን በድጋሚ እንዲያጤነው እና
በኢትዮጲያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት አማካኝነት የቀረቡ የመስሊሙ አጃንዳዋች እንዲካተቱ እና ህዝበ ሙስሊሙም በቁጥሩ ልክ ተሳታፊ እንዲሆን ጥሪ ቀርቧል።መረጃወችን ለወዳጄ ዘመድ ሼር ያርጉ!
የቴሌግራም ቻናላችን ከስር በሊንኩ ይቀላቀሉ
https://t.me/+UAKV32q7U2HKzEMf
5.2K viewsedited  11:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-15 22:05:17 ከፍር*ቴው ሚሽነሪን በተመለከተ ኡስታዝ አብዱረህማን ሱልጧን የጀመረውን ጽሁፍ ተከትሎ በክፍል በክፍል ለምን ተደረገ አጠረ የሚል ወገኖች ቅሬታቸውን እያቀረቡ ነው ። በግሌ ከፌስቡክ ልምዴ በመነሳት ረዘም ያለ ጽሁፍ ሲሆን ለምን የፈለገ አይሆንም ብዙሃኑ ለማንበብ ትእግስት የለውም ።

ለአብነት ያህል ትላንት ከኡስታዛ ያስሙን ሙጃሂድ የስለ ፌስቡክ ፖስት ያደረጉት ጽሁፍ እጅግ በጣም ጠቃሚ፣በዘመናችን ለወድቅንበት በሽታ ትልቅ መድሃኒት የሆነ ጽሁፍ ነው ። በዚህ ዘመን ከትንሽ እስከ ትልቅ የተፈተነበት ነገር ግን ብዙሃኑ አላነበበውም ።

ለማንኛውም ይሄን ሰው እና ተቋሚ የሚሰሩትን የሚሽነሪ ስራ በተመለከተ መፍትሄውስ ምንድን ነው የሚለውን ጨምሮ ከያህያ ኢብን ኑህ እንዲሁም ግለሰቡን ከሚያውቁት ኡስታዝ አብዱረህማን ሱልጧን እና ኡስታዝ አብዱረህማን አህመድ አልሃዲ ጋር ቆይታ በማድረግ በሃሩን ሚዲያ ልዩ ዝግጅት ይዘንላችሁ እንቀርባለን !
6.6K views19:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-15 21:13:43
የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ-ከተማ እስልምና ጉዳዮች ም/ቤት በክፍለ-ከተማው ውስጥ ከሚገኙ ዳኢዎች ጋር የትውውቅ መርሃ-ግብር ማድረጉን ገለፀ!
...
(ሀሩን ሚዲያ፦ግንቦት 07/2016)
...
የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ-ከተማ እስልምና ጉዳዮች ም/ቤት በክፍለ-ከተማው ውስጥ ከሚገኙ ዳኢዎች ጋር ባደረገው የትውውቅ መርሃ-ግብር ላይ ወደፊት አብሮና ተባብሮ ለምስራት ከስምምነት መድረሳቸውንና በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ማድረጋቸውን የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ መጅሊስ ለሀሩን ሚዲያ በላከው መረጃ ገልጿል።
...
ሀሩን ሚዲያ
6.7K viewsedited  18:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-15 20:38:56 ማስታወቂያ/Promotion ማሰራት የምትፈልጉ አናግሩኝ @Faysul
6.2K views17:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-15 19:02:04 የሚሽነሪዉ አካል ሙሀመድ ሱሩር ማን ነዉ ?

(ክፍል 2 )

ቢስሚላህ !

በቁጥር አንድ እንደ ጀመርኩላችሁ የሚሽነሪዉ አካል ሙሀመድ ሱሩር ቤተሰቦቹ የጁ ዉስጥ እንደ ሆኑ ያወራል ( በርግጥ አንዳቸዉም ቤተሰቡ ነኝ ብሎ የመጣ አላዉቅም ) ሰዉየዉ በአንድ ወቅት መርሳ ከተማ ላይ ለትልቅ እስላማዊ ዝግጅት ስንጓዝ ከፊት ወንበር ጋቢና ላይ ተቀምጧል ታላላቅ ዓሊሞችና ጎደኞቼ ከሓላ ተቀምጠን ከካራቲስትነት ከፍ ብሎ በሆነ ጦርነት ( ስሙን ረሳሁት ሀገር ዉስጥ በተደረገ ) ላይ ከሄሊኮብተር ሲወርድ እንደተጎዳ አገግሞ እንደ ዳነ ያወራል ።

ይህ ሰዉ በማበረሰብ ዘንድ ተቀባይነት አገኘ የቁርአን ሂፍዝ ማእከሉ አድራጊ ፈጣሪ ሆነ ሚስትም አገባ ትንሽ ቆይቶ ሀኪም ነኝ የህክምና ት/ት መማር አለባችሁ ብሎ ከመርከዝ ልጆች አምስት ሰዉ መርጦ በጊዜዉ እኔ አብዱራህማን ሱልጧን ዶ/ር አህመድ ኑርየ ኢንጂነር ሙሀመድ ጀዉሀር ( አሏህ ይማረዉ ሁላችሁም ዱዓ አድርጉለት ) ሌሎች ሁለት ወንድሞቼ ረሳሃቸዉ ሁነን ለአንድ ሳምንት መርፌ እንዴት እንሚሰጥ አስተማረን እኔም በሳምንት የመርከዙ ሀኪም ሆኜ እርፍ !።

በጊዜዉ ለህክምና ብዙ ትልልቅ ሰዎች ይመጡ ነበር ቪ B2 ወግቶ በጊዜዉ የማይታመን ብር ነበር የሚጠይቀዉ ለምን የሚለዉም አልነበረም ።

ሚስት የሓላ ሓላ ስቃዪ በዛ ከአንድ የዲን መምህር ነኝ ከሚል ሰዉ የማይጠበቁ ነገሮችን ስታይ ለማን ትናገር ማንስ ያምናታል ።

የመርከዝ ልጆችም ለሁለት መከፈል ጀመሩ የተለያዩ ወንጀሎችን ሲፈፅም ያዮትንና የጠረጠሩትን ልጆች የኢማን ድክመት አለባቸዉ ፡ ጅሀድ ይጠላሉ የተለያዮ ስም እየለጠፈ የመርከዙ ልጆችን ከፋፈላቸዉ በመሀባ እንባ ይራጩ የነበሩ ወንድማማቾች ተኮራረፉ ።

ባጭሩ የወልዲያ ሰዉ ዳዒ አለመሆኑን እየተረዳ ይመስላል ስለዚህ ክትትል ጀምሯል ።

የሚገርሙ ታሪኮች ይቀጥላሉ ወልዲያ የጀመዓዉና የሚስቱ ታሪክ ከቆቦ እስከ ኮምቦልቻ …..።
Abdurahman Sultan
6.9K viewsedited  16:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-15 15:18:12
የሚሽነሪዉ አካል ሙሀመድ ሱሩር ማን ነዉ ?!!
ቢስሚላህ !
ከ 25 አመት በሗላ የጠፋኝን ሰዉ ወንድሜ የህያ ኢብኑ ኑህ ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ለጥፎት ባይ ገረመኝ !!

የዛን ዘመን አፍላ የቁርአንና የዳዕዋ ንቅናቄን ከየት እንደመጣ ሳናዉቅ ነበር የተቀላቀለን ።

ፂሙ ያደገ የፓኪስታን ልብስ የለበሰ በቀኝ እጁ ሲዋክ በግራ እጁ ሙስበሃ ይዞ የፈጅርን ሰላት ለመስገድ የሂፍዝ ተማሪዎች ዉዱእ ማድረጊያ ላይ በዛ ብርድ ወቅት እንጣደፋለን ። ከመሀላችን ሞቅ ባለ ከፍ ባለ ድምፅ “ እናንተ ወጣቶች በናንተ ጊዜ ዲን ሲደፈር ነብያችን ሰ.ዐ.ወ ክብራቸዉ ሲነካ እናንተ እያላችሁ እንዴት ይሆን ለጅሀድ ተነስ እኔ አሰለጥንሀለሁ !” የሚል የወጣቱን ስሜት በሚቀሰቅስ መልኩ በቁጣ ንግግር አደረገ ። ብዙዎቻችን ሙሀመድ ሱሩር በሚል የቀረበንን ሰዉ ያኔ ተዋወቅነዉ ከፈጅር ሰላት በሓላ የቁርአን ሀለቃ ላይ አብሮን ተቀመጠ ። መስጅድ ላይ በተበላሸ ምላስ የቁርአን አያቶችን እየሰባበረ ዳዕዋ ማድረግ ጀመረ የዋሁ ማህበረሰባችን እና ወጣቱ ተከተለዉ ። በጣም የሚገርሙ ሊታመኑ የማይችሉ ለሀገር ሲል ከኤርትራ ጋር በተደረገ ጦርነት መሳተፉንና ለኢስላም ሲል አፍጋኒስታን ድረስ ዘልቆ የተዋጋበትን ባዶ ታሪክ ለወጣቱ ይግተዉ ጀመር አንዳንዱ በየት ብለን ጅሀድ በወጣን እስኪል ድረስ
የማልረሳዉ ሁሌ ግን ጥያቄ የሚሆንብኝ የነበረዉ ጠዋት ከሀለቃ በሗላ ከቁርስ በፊት ወደ ዉጭ እንዳንወጣ እንከለከል ነበር ። ለምን አትሉም ?
ሙሀመድ ሱሩር ካራቴ እየሰራ ጩሀቱን እንጅ ስራዉን ማየት እንዳንችል ምክኒያቱም በጩሀቱ ብቻ ካራቲስት እንደሆነ እንድንመሰክር ።

ማህበረሰባችን በዚህ ብቻ አልቆመም በዲኗ ጠንካራ የሆነች ልጅ ተፈልጋ ተዳረ ። ከዛን ጊዜ ጀምሮ የሙሀመድ ሱሩር ማንነት ይጋለጥ ጀመረ ።
ይቀጥላል !!

Abdurahman Sultan
7.0K views12:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-15 11:50:44
ከ ሐጅ ቪዛ ውጪ ሐጅ ማድረግ እንደማይፈ ቀድ የሳውዲ የሐጅ ሚኒቴር አስጠነቀቀ።

የሳውዲ አረቢያ የሐጅና ዑምራ ሚኒስቴር ፣ ከሐጅ ቪዛ ዉጪ በማንኛውም የቪዛ አይነቶች ሐጅ ማድረግ እንደ ማይፈቀድ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ገለፀ።

የጉብኝት ፣ የቱሪስት ፣ የትራንዚት : የስራና መሰል በሳውዲ አረቢያ የሚሰጡ ቪዛዎችን በመጠቀም ሐጅ ለማድረግ የሚሞክሩ ከዚህ ተግባራቸው እንዲቆጠቡ ከወዲሁ የሚኒስተር መስሪያ ቤቱ አስጠንቅቋል።

ሐጅ ለማድረግ ሳዑዲ አረቢያ ከመገባቱ በፊት የሐጅ ቪዛ ማግኘት የግድ አስፈላጊ መኾኑን የጠቀሰው ሚኒስቴሩ፣ በጉብኝት ቪዛ፣ በሥራ ቪዛ፣ በቱሪስት ቪዛ፣ በትራንዚት እና በመሳሰሉት ቪዛዎች ሳዑዲ አረቢያ በመግባት ሐጅ ማድረግ እንደማይቻል አሳስቧል።

ሚኒስቴሩ አክሎም፣ ሐጅ ማድረግ የሚቻለው ጉዳዩ የሚመለከተው የሳዑዲ አረቢያ ሚኒስቴር በየሀገራቱ የሐጅና ዑምራ ጉዳይ ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር በመተባበር በሚሰጠው የሐጅ ቪዛ እና፣ እነዚህ ተቋማት በሌሉባቸው ሀገራት ደግሞ "ኑሱክ ሐጅ" በሚሰኘው ፕላትፎርም አማካይነት ብቻ መኾኑን መረዳት ያስፈልጋል ብሏል።

ሐጅ ለማድረግ፣ ሳዑዲ አረቢያ ከመገባቱ በፊት ራሱን የቻለ የሐጅ ቪዛ ማግኘት የግድ አስፈላጊ እንደኾነ የጠቀሰው የሚኒስቴሩ መግለጫ፣ ከሳዑዲ የሐጅና ዑምራ ሚኒስቴር ጋር ግንኙነት ካላቸው የየሀገራቱ የሐጅና ዑምራ ተቋማት ውጪ የሐጅ ቪዛን ማግኘት እንደማይቻል በመግለጽ ምዕመናን ከመታለል እንዲጠነቀቁ አሳስቧል።

"ሐጅ እናስደርጋለን" በሚሉ አጭበርባሪ ኩባንያዎች መታለል ከሚያስከትለው የገንዘብ ኪሳራ በተጨማሪ፣ የጓጉለትን ሐጅ ለማድረግ አለመቻልን በማስከተል ከባድ ሐዘን ላይ ሊጥል እንደሚችል ሚኒስቴሩ አሳስቧል።

የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት።
7.2K viewsedited  08:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-14 19:41:47
ከአሳሳ እስከ ሮቤ፣ ከኮኮሳ እስከ አዳማ ፣ ከአርሲ እስከ ባሌ፣ እስከ ሸገርና ጎንደር ድረስ ጭምር ታሪክ አለን ከዚህ ሰው ጋር፡፡
በተለያዩ ከተሞች እየተዘዋወረ በጎዳና ላይ ደዕዋ ሲያደርግ ታውቁታላታችሁ፡፡ ምንም ማንንም የማይፈራ ሙጃሂድ ነው። ስፒከሩ በተዳጋጋሚ ታስሮበት በየፖሊስ ጣቢያው ሲንከራተትም አጋጥሞኛል፡፡

ከልጅነት እስከ ወጣትነትና ጎልማሳነት ምናልባት እስካዛሬዋ እስከመጨረሻዋ የዱንያ ላይ ቀን ድረስ ሐያቱን በሙሉ በደዕዋ አሳልፏል፡፡ አላረፈም። ኢስላምን ለማድረስ ሁሌ እንደተጓዘ ስለማየው ቤት ይገባ ይሆን ብዬ እጠይቃለሁ ብዙ ጊዜ፡፡ ዛሬ ሻሻመኔ ላይ ድንገት ማረፉን ሰማሁ፡፡

ፈቂ ገለቶ አላህ ይዘንልህ፡፡

ሰው በኖረበት ነገር ላይ ይሞታል፤
በሞተበት ነገር ላይም ይቀሰቀሳል፡፡

ደጋግ ባሮችህ ወዳንተ እየመጡ ነው።
አላህ ሆይ!
ዐለይከ ረበና ቢሑስኒልኺታሚ እንላለን ።መረጃወችን ለወዳጄ ዘመድ ሼር ያርጉ!
የቴሌግራም ቻናላችን ከስር በሊንኩ ይቀላቀሉ
https://t.me/+UAKV32q7U2HKzEMf
8.0K viewsedited  16:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-14 19:40:57
በስልጤ ዞን ዝናብ ባስከተለው ጎርፍ ከ130 በላይ አባዎራዎች ሲፈናቀሉ 150 ቤቶች በውሃ ተይዘዋል ተባለ!
...

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በስልጤ ዞን በስልጢ ወረዳ ከመበደኛው የዝናብ መጠን በላይ እየጣለ በሚገኘው የበልግ ዝናብ ምክንያት በጎፍለላ ቀበሌ ከ130 በላይ አባወራዎች ከቤት ንብረታቸው መፈናቀላቸውን ተሰምቷል።
...
በዚሁ ጎርፍ 132 አባዎራዎች ከቤት ንብረታቸው ሲፈናቁ ፣ 150 ቤቶች እና 235 ሄክታር ለበልግና ለመኸር የተዘጋጀ ማሳ ደግሞ በጎርፍ ውሃ መያዙን የዞኑ የአደጋ ሥጋት ስራ አመራር ጽህፈት ቤት ሃላፊ ወ/ሮ ወሲላ አሰፋ ተናግረዋል።
...
በበጀት ዓመቱ ገና ከጅምሩ የዝናብ መብዛቱን ተከትሎ በጎፍለላ ቀበሌ የተከሰተው ጎርፍ  እጅግ አሳሳቢ መሆኑንና ችግሩን ለመከላከል ርብርብ ማድረግ እንደሚያስፈልግም ተመላክቷል ።በተጨማሪም የጎርፍ  አደጋው በሰው ህይወትና በንብረት ላይ የከፋ ጉዳት እንዳያስከትል ጥረት መደረጉን አመላክተዋል።
...
አሁን ላይ ከቤት ንብረታቸው የተፈናቀሉ አባወራዎች በጊዚያዊ መጠለያ እንዲጠለሉ መደረጉንም ገልፀዋል። በሌላ በኩል በጎርፉ ምክንያት የኮሌራና ሌሎች መሰል በሽታዎች እንዳይከሱት ከወዲሁ የጤና ተቋማትን ያቀፈ ግብር ሃይል በማቋቋም ርብርብ ይደረጋል ብለዋል።
...
7.3K views16:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-24 08:30:14
የውዱ ወንድማችን ኡስታዝ ያሲን ኑሩ ወላጅ አባት ታመው ለህክምና በዱባይ በሚገኝ ሆስፒታል ህክምናቸውን እየተከታተሉ ይገኛሉ::

አባታችን አላህ ሙሉ አፊያቸውን እንዲመልስላቸው እና በሙሉ ጤንነት ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ሁላችንም በዱዓ እንድናግዛቸው ጥሪዬን አስተላልፋለው::

በዚህ ወቅት በህመም እና በጭንቀት ላይ ያሉትን ሁሉ አላህ ይፈርጃቸው

አሚን
4.9K views05:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ