Get Mystery Box with random crypto!

ቢስሚከ ነሕያ✿⁠ ⁠♡

የቴሌግራም ቻናል አርማ daruljennah — ቢስሚከ ነሕያ✿⁠ ⁠♡
የቴሌግራም ቻናል አርማ daruljennah — ቢስሚከ ነሕያ✿⁠ ⁠♡
የሰርጥ አድራሻ: @daruljennah
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 244
የሰርጥ መግለጫ

اعلم ارشدك الله لطاعته🖤

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

3

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-06-28 04:12:26 ጌትዬ የመጨረሻችንን ነገር አደራ ዛሬ ስንታይ ጀነት ላይ vip ፊርደውስን የገባን ያህል ፈታ ብለናል አንተው በዲንህ ላይ አፅናን ።

ኢብነል ጀውዚ እንዳወሰቱ ኢብኑከሲር አልቢዳያ ወኒሃያ ላይ እንዳሰፈሩት አንድ ዐብደቱ ኢብኑ ዐብዱረሂም የተባለ ቃሪእና ሙጃሂድ ከሚባሉት ውስጥ የነበረ ሰው ነበር ከእለታት አንድ ቀን ከሙስሊሞች ጋር ወደ ሩም በዘመተበት ግዜ ላይ ይህ ሙጃሂድ ከአንድ ምሽግ ውስጥ ተቀምጦ ይጠባበቃል በአጋጣሚ ግን አይኑ ወደ አንዲት ቆንጆ የሩም ክርስቲያን ሴት ላይ አረፈ ወድያውኑ ልቡም ሸፈተ ወደዚች ሴት ለመድረስም ደብዳቤ ላከላት እንዲህም አላት " ወደ አንቺ መድረሻው መንገድ ምንድነው?

እርሷም " እኔን የምታገኝበት መንገድ አንድና አንድ ነው እሱም እኔ ያለሁበትን ክርስትና መቀበል ያኔ እኔ ያንተ መሆን እችላለሁ " አለች

እርሱም ለጥያቄዋ አወንታዊ ምላሽን ሰጠ! ለርሷ ተንበረከከ ከፈረ! አላህ ይጠብቀን ።

ከርሱም ጋር የነበሩ ሙስሊሞች ያልጠቁት ክስተት ነበረና እጅጉን አዘኑ በርሱ ሰበብም የሙስሊሞች ጦር ክፍተት ተፈጠረበት። ይህ ክስተት ካለፈ ከረዥ አመታት ቡሃላ ሙስሊሞቹ በሩሞቹ ቀዬ በኩል ሲያልፉ ይህን ቃሪእ ምጃሂድ የነበረ ወንድማቸውን አስታወሱት ፈልገውም አገኙት ።

ሲያገኙት ከዛችው ከሩም የሆነችዋ ከሚስቱ ጋር ነበር ቀጥለውም እንዲህ አሉት " አንተ ዐብደት ሆይ! እንደው እስቲ ንገረን ያ ሁሉ የሸመድድካቸው የአላህ ቃል ቁርአን ምን ላይ አደረሰክ? ያ ዒልምህስ? ያ ሶላትህስ ያ ፆምህስ ? ያ ጂሀድህስ? ...

የእርሱ መልስ ግን እንዲህ ነበር

" እወቁ እኔ አሁን ላይ ሁሉንም የቁርአን አንቀፆች ረስቻቸዋለሁ አይህ አንቀፅ ሲቀር እርሱም ...


رُّبَمَا يَوَدُّ الَّذِينَ كَفَرُوا لَوْ كَانُوا مُسْلِمِينَ

እነዚያ የካዱት (በትንሣኤ ቀን) ሙስሊሞች በኾኑ ኖሩ ብለው በብዛት ይመኛሉ፡፡

ذَرْهُمْ يَأْكُلُوا وَيَتَمَتَّعُوا وَيُلْهِهِمُ الْأَمَلُ ۖ فَسَوْفَ يَعْلَمُونَ

ተዋቸው ይብሉ፤ ይጠቀሙም፡፡ ተስፋም ያዘናጋቸው፡፡ በእርግጥም ወደፊት (መጥፎ ፍጻሜያቸውን) ያውቃሉ፡ ( አል ሂጅር 23)

ረሱሉ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ይህን ዱዐእ ያበዙ ነበር

" አንተ ልብን ምታገለባብጥ ጌታ ሆይ በዲንህ ላይ ልቤን አፅና "

አላህ ልቦናችንን ያፅናልን

አንዋር ኺያር
99 views01:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-26 18:35:59 #አስሩ የዙልሂጃ ቀናት!

ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦

ما مِن أيّامٍ العملُ الصّالحُ فيها أحبُّ إلى اللَّهِ من هذِهِ الأيّام يعني أيّامَ العشرِ، قالوا: يا رسولَ اللَّهِ، ولا الجِهادُ في سبيلِ اللَّهِ؟ قالَ: ولا الجِهادُ في سبيلِ اللَّهِ، إلّا رَجلٌ خرجَ بنفسِهِ ومالِهِ، فلم يرجِعْ من ذلِكَ بشيءٍ

“በነዚህ አስር ቀናቶች ውስጥ ከሚፈጸም መልካም ስራዎች በበለጠ መልካም ስራዎች አላህ ዘንድ የተወደዱ የሚሆኑባቸው ቀናት የሉም። ‘በአላህ መንገድ ላይ የሚደረግ ጂሀድም ጭምር?’ ተባሉ። እርሳቸውም ‘ራሱንና ንብረቱን ይዞ ወጥቶ ምንም ያልተመለሰለት ሰው ሲቀር ጂሀድም ከዚህ አይበልጥም’ አሉ።”

ቡኻሪ ዘግበውታል: 969
101 views15:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-24 15:45:45 الهم صلى وسليم وباريك على نبينا محمد ‌ﷺ
120 views12:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-24 03:16:22
የአላህ መልዕክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦

«በጁምዓ ሌሊትና በጁምዓ ቀን ላይ በእኔ ላይ ሰለዋት ማውረድ አብዙ፣ በእኔ ላይ አንድ ሰለዋት ያወረደ አላህ በእርሱ ላይ አስር ሰለዋት ያወርድለታል።»

ኢማሙ አልባኒ ሀዲሱን ፦ " ሐሰን " ብለውታል።

አላሁመ ሰሊ ወሰሊም ወባሪክ ዓላ ነብይና ሙሀመድ ሶለሏሁ ዓለይሂ ወሰለም
127 views00:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-23 21:05:29 ሐዘን አይቀጥልም፣አዲስ ነገርም አይደለም፦
(ነብዩ (ﷺ) አዝነው ነበሩ )ቡኻሪ ―6982

ማንባት ሁልግዜም አይቀጥልም፣ዱንያም ናትና ኣለማልቀስም አይታሰብም፦
(ነብዩ ﷺ አለቀሱ)ቡኻሪ ―1304

ዝምታ ጥሩ ነገር ነው፣በተለይ ስለ ጉዳዩ ምንም ተጨባጭ ግንዛቤ በሌለንበት ጉዳዮች ላይ፦
(ነቢያችን ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰላም ለተወሰነ ጊዜ ዝም ይሉ ነበር) ቡኻሪ 3695

የፈገግታ ግዜ እሩቅ ባይሆንም በትዕግስትና በስሌት ግዜውን እንጠብቅ፣ነገራቶች እያማሩ ሲመጡ የብስራት ብርሃን ፍንጣቂ መምጣቱ አይቀርም፣ፈገግታም ሱና ነው ተብለዋል
(ከዚያም ነቢዩ ﷺ ፈገግ አሉ።)ቡኻሪ- 1021

ከዚያም ዉዱ ነቢያችን በሚያምረው ገፅታቸው ስቀው ነበሩ፣ማለትም ሁልግዜ አንድ አይነት ጨለማ ፊትን ለሁሉም ማሳየት ተወዳጅ አይደለም፦
"ነብዩ ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም ሳቁ) ቡካሪ 1936

ፈገግታው፣ ሳቁ፣ ዝምታው፣ ሀዘኑ እና ለቅሶው ለእኛ ለተከታዮቹ መንገድ በሆነው ነቢይ ላይ ሰላት እና ሰላም በእርሱ ላይ ይሁን።

@ጃዕፈር
111 views18:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-23 14:44:06 #ከዓሪፎቹ_መንደር

‹‹ አንድ ሰው ወደ አላህ እውነትኛ የሆነን ሱጁድ ቢያደርግ ከስጁድ በኋላ በፍጹም ካጎነበሰበት መነሳት አይችልም፡፡›› ሱልጣን አልዓሪፊን ኢብኑ ዐረቢ (ቀደሰላሁ ሲረሁ)

እንግዲህ የዓሪፎቹ ንግግር ከባድና ጥልቅ ነው፡፡ የእነርሱን ንግግሮች ለመረዳት ጥረት ብናደርግና ብንኖርበት ለጊዜያችን ብዙ ምላሾች አሉት፡፡ ንግግሮቻቸው ከቁርአናዊና ሐዲሳዊ ግንዛቤና ከአላህ የተሰጣቸው ድንቅ ችሮታ ነው፡፡ እውነት ነው አንዴ ለአላህ የሰገደች ነፍስ እንዴት ሌላ ይታያታል፡፡ የስጁድ ትርጉሙ ባርነትን ለአላህ ማድረግ መቻል ነው፡፡ ባሪያ ደግሞ ነጻነቱ ጌቶቹን ማስደሰቱ ነው፡፡ እኛ አላህን ማስደስት መቻል ነበር ነጻነታችን እንጂ የነፍሲያን ፍላጎት ማግነን አልነበረም፡፡ አላህን በማምለክ ባርነት ውስጥ ማግኘት የነበረብንን ብዙ ጥቅሞችና የዱንያ ገረዶች ፍጡሩን በማምለክ የፈለግነው ጊዜ ተዋረድን፡፡ ሰዎች የገንዘብ፣ የአስተሳሰብ፣ የፖለቲካና የነፍሳቸው ባሪያ ሲኾኑ ሰው ስለኾኑ ብቻ የተሰጣቸው ታላቅነት ይገፈፋሉ፡፡ ሰዎች ለአላህ በሚያሳዩት ባርነት ልክ ደስታቸውን መሥራት ሲጀምሩ ከመላእክት ሁላ ይበልጣሉ፡፡ ዛሬ ግን ሰዎች ሕይወታቸው ከሚያሳድጉት ውሻ ራሱ አልሻል አለ፡፡ ለውሻቸው ስም የሚያወጡ ሰዎች ረስተውት ራሳቸው እንደውሻ ፍርፋሪ መልቀም ብቻ ሆነ ሥራቸው፡፡ ሰዎች ከፍታቸው በባርነታቸው ሲሆን ይህ ባርነት ለፍጡር ሲሆን ደግሞ በምንም ነገር ቢከብሩ በእምነት እንኳ የላቁ ቢመስላቸው የተዋረዱ ሆነው ይኖራሉ፡፡

#መደድከ_ያ_አላህ!

@ቤስት ከሪም
101 views11:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-22 05:22:51 ኡሙ አማራህ የጀግንነት ተምሳሌቷ እንስት

ክፍል (1¹)

ኡሙ አማራህ (ረ ዐ)(መጀመሪያ ኢስላምን ከተቀበሉ አንሷሮች)የመካ ስደተኞችን የተቀበሉ የመዲና ሰዎች መካከል አንዷ ናት።በ<አል-አቀባህ>ለመልዕክተኛው ድጋፍ ከሰጠው ቡድንም አንዷ ነች።<አል-አቀባህ> በዐረብኛ ትርጉሙ በተራራዎች መሀል ያለ ጠባብ መንገድ ማለት ነው።በመጀመሪያዎቹ የኢስላም ቀናት ሙስሊም የሚሆኑ ሰዎች በቁረይሾች በከፍተኛ ደረጃ ስቃይ ይደርስባቸው ነበር።ቁረይሾች የኢስላም አስተምህሮ እንዳይስፋፋ ማድረግ የሚችሉትን እንቅፋቶች ሁሉ ያደርጉ ነበር።በዚህ ምክንያት መልዕክተኛው ﷺተልዕኳቸውን ያካሂዱ የነበሩት በሚስጥር ነበር።ከመዲና ሃጅ ለማድረግ ወደ መካ የሚመጡ ሰዎች ባብዛኛው ኢስላምን የሚቀበሉት ሚና አጠገብ ከሚገኘው በተራራዎች መሀከል በሚገኘው ጠባብ መንገድ ነበር_ቁረይሾች እንዳያዩዋቸው።ኡሙ አማራህ ከስደት በኋላ ከተካሄዱት አብዛኛዎቹ ዘመቻዎች ተካፍላለች።በኡሁድ፣ሁድይቢያ፣በኸይበር፣በኡምረቱል ቀዷ፣ሁነይንና በየማማህ ዘመቻዎች ላይ ታላቅ ሚና ነበራት።

በኡሁድ ጦርነት ዕድሜዋ 43 ነበር።ባለቤቷና ሁለት ልጆቿም በጦርነቱ ተወግተዋል።ከቆዳ በተሰራ ቀረበት ውሃ ይዛ ወደ ኡሁድ ገሰገሰች።ሙስሊሞች በመጀመሪያ እያሸነፉ ነበር።ነገር ግን በሚቀጥለው ቅጽበት ነገሩ የተገላቢጦሽ ይሆንና ጠላት ሊያሸንፍ በቃ።የጠላት ወታደሮች እየተግተለተሉ መልዕክተኛውን ለመምታትና ለመግደል ሲጎርፉ እሳቸው አጠገብ ደረሰች።ማንኛውም ሰው ሲቀርባቸው ለመልዕክተኛው ትከላከል ነበር።በጭኗ በታጠቀችው መቀነት የቁስል ማከሚያ ቋጥራለች።ቁስለኛችን ታክማለች።እሷም እራሷ አንድ በከፍተኛ ሁኔታ የቆሰለችውን ጨምሮ አስራ ሁለት ቦታዎች ቆስላለች።ኡሙ ሰዒድ ይህንን አስመልክታ እንዲህ ብላለች።

<<በአንድ ወቅት ኡሙ አማራህ ትከሻ ላይ በጣም የቆሰለ ቦታ አየሁ መንስኤው ምን እንደሆነ ጠየቅኳት።በኡሁድ ጦርነት ነው ሰዎች በመደናገጥ ሲሮጡ ኢብን ቁሚያህ ወደኛ እየመጣ ሙሐመድ የት አለ? የት እንዳለ አንድ ሰው ይንገረኝ።እሱ ዛሬ የተረፈ እንደሆነ እኔ አለቀልኝ በማለት አምባረቀ።እኔ፣ሙስአብ ኢብኑ ዑመይርና ሌሎች ሆነን ገጠምነው።እሱ ነው እንዲህ ትከሻዬ ላይ በሰይፍ የቆረጠኝ።እኔም መትቼው ነበር ነገር ግን ሁለት የብረት ልብሶች አጥልቆ ስለነበር ምንም ሳይሆን አመለጠ ስትል መልስ ሰጠችኝ።

ይቀጥላል

ምንጭ #ሐያቱ_ሶሐባ 240
https://t.me/daruljennah
98 viewsedited  02:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-20 20:46:39 « ላ ኢላሃ ኢለላህ ሙሐመድ ረሱሊላህ» ማለት ምን ማለት ነው?
ከአላህ ውጭ ጌታ ከሙሐመድ ውጭ መልእክተኛ የለም ማለት ነው። ይህ ማለት ምንድነው? የነገራት ሁሉ አስገኚና ፈጣሪ ሊመለክ የሚገባውና መመሪያው ክቡር የሆነው አላህ ነው ማለት ነው። ታላቁ የአላህ ነብይ ሙሐመድ (ሰዐወ) በምድር ላይ ካሉ ፍጡራን ሁሉ ምርጡና ከነፍሳችን በላይ የምንወዳቸው የሰው ልጆች ሁሉ ዓይነታ ናቸው ማለት ነው። ይህ መንገድ ብቻ ነው ቅዱስ ሌላው ሁሉ ከዚህ የተረፈና ውድቅ ነው ማለት ስንችል ነው ኢማን ማለት። እኛ በዚህ መንገድ ስንኖር የምናገኘው ክብር እንጂ በተቃራኒው በመንገዱ እኛ የራሳችንን ፍላጎት ያጎላን ጊዜ በምድር ላይ የተዋረድን ሆነን እንኖራለን። በእምነት ውስጥ "ፍላጎትን" ትተን መንፈሳዊ ከፍታ አገኘን ወይስ በእምነቱ "ፍላጎትን" አከማቸን?! ሰይድና ዑመር(ረዐ) እንዲህ ይላሉ « እኛ በእስልምና ክብርና ልቅና ያገኘን ሕዝቦች ነን ይህን ክብር በሌላ መንገድ የፈለግን ጊዜ ውርደትን ያከናንበናል።»
ሰይድና ዑመር በምድር ላይ ፍትሕን ያሰፈኑ በርካታ ሐገራትን በአንድ አድርገው የመሩ ታላቅ ሰው ነበሩ። ግለሰባዊ ባሕሪያቸው ግን የተለየ ነበር። ሰይጣን ሳይቀር የሚፈራቸው ታላቁ ዑመር በለሊት ራሳቸውን ለመተሳሰብ አለንጋ አዘጋጅተው ራሳቸውን ይገርፉ ነበር። በዙህድናቸው የታወቁ ፍላጎታቸውን ገትተው በድህነት የገፉ ነበሩ። ከራሳቸው በላይ ለሌላው ይጨነቁና ትውልድን ለመስራት ይታትሩ ነበር። ያለፉት ሰለፎች ፍላጎታቸውን በመርታት ከእኔ ይልቅ ሌላው በማለት ትውልድን ቀረጹ ትውልዱ እንዲቀየር መድረክ ላይ መተወን ሳይኾን የሚያስፈልገው ከመድረኩ ወርዶ ከሕዝብ ጋር ተቀላቅሎ መኖርን ኢስላም ያለማምዳል። ዐዲስ ነገር መስማት ብቻ ሳይኾን የሚታወቁና የምንሰማቸውን ቀላል የሚባሉ ነገሮችንም ደጋግሞ ማለትና ማሰብ የሚፈለገውን ኢማን ያስገኛል።

አላህ ይሁነና ያስረዳንም!

@ቤስት ከሪም
100 views17:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-20 00:23:32 ኡሙ ሰለማህ(ረዲየአሏሁ ዐንሀ)ስለ ሶሀቢያት
አቋም እንዲህ ትላለች......
(الاحزاب59)
#ይህች !አንቀጽ ስትወርድ የአንሷር ሴቶች ከቤታቸው ሲወጡ !ከእርጋታቸውና
ጥቁር ከመልበሳቸው የተነሳም #አናታቸው ላይ ቁራ ያለ ይመስል ነበር!!
በማለት እነዚያ ቀዳም ምዕመናን ሴቶች የቁርዐን አንቀጹን እንዴት ሙሉ በሙሉ በመሸፋፈን
እንደተረዱትና እንደተገበሩት አስገንዝበዋል !!!
ዛሬ ላይ ግን አላህ ያዘነላቸው ሲቀሩ ተቃራኒ ሆኗል
አላህ ይዘንልን!!
https://t.me/daruljennah
104 viewsedited  21:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-17 23:32:43 ربما ذنباً :
أفقدك نعمه في دنياك - فاستغفر -
حتى يعيدها الله لك !
فالمعاصي تزيل النعم
والإستغفار يجلبها ، والشكر يحفظها
111 views20:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ