2022-09-02 07:37:26
መረጃ
በደባርቅ ከተማ 16 ሰርጎ ገቦች ተያዙ።
የደባርቅ ከተማ አሥተዳደር በምሽት የኬላ ጥበቃ 16 የአሸባሪውና ተስፋፊው ትህነግ ወራሪ ቡድን አባላት የኾኑ ሰርጎ ገቦችን በቁጥጥር ስር አውሏል።
የአሸባሪውና ተስፋፊው ትህነግ ወራሪ ቡድንን እኩይ ዓላማ ለማስፈፀም በተለያየ ምክንያት ወደ ከተማዋ ገብተው እየተንቀሳቀሱ የመረጃ ማቀበል ሥራ የሚሠሩ 16 ተጠርጣሪ ሰርጎ ገቦች እና ሶስት ህገ-ወጥ መሳሪያ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የደባርቅ ከተማ ከንቲባ ብርሃን ፀጋየ ገልፀዋል።የአሸባሪውና ተስፋፊው ትህነግ ወራሪ ቡድንን ዳግም ወረራ ለመከላከል በሚደረግ ዘመቻ የመጀመሪያው ተግባር የከተማችን ከሰርጎ_ገብ መጠበቅ እና የደጀንነት ሚና መወጣት ዋነኛና ቁልፍ ተግባር መሆኑ ታውቆ በአደረጃጀት ስምሪት ተሰጥቶ ወደ እየተሠራ መኾኑን ከንቲባው ተናግረዋል።
@dailyNews_et @dailyNews_et
402 views04:37