Get Mystery Box with random crypto!

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

የቴሌግራም ቻናል አርማ arebgendamesjid — የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች
የቴሌግራም ቻናል አርማ arebgendamesjid — የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች
የሰርጥ አድራሻ: @arebgendamesjid
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.19K
የሰርጥ መግለጫ

بسم الله الرحمن الرحيم
📮እንኳን ወደዚህ ቻናል ተቀላቀሉ‼️
በዚህ ቻናል ቂርአቶችን፣ ሙሐድራዎችን፣ዳዐዋዎችን እና ሌሎችንም ከአረብገንዳ መስጊድ በአሚሩ አማካኝነት በቀጥታ የምታገኙበት ቻናል ነው።
ሃሳብ አስተያዬት ካለ በዚህ ያድርሱን ⤵️
@ye_Arebgenda_mesgid_wetatoch_bot

Ratings & Reviews

1.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-08-28 20:45:38 አቂደቱል ዋሲጥያ
ሸይህ ዑመር አሊ
  ክፍል-13-
http://t.me//@arebgendamesjid
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ
ዘርፍ
201 views17:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 20:42:26    የአቡበክር አስ-ሲዲቅ (ረድየሏሁ ዐንሁ) ታሪክ

  "ከአቡበክር በስተቀር ማንኛውንም ሰው ወደ እስልምና ስጋብዘው ያላመነታና ያላንገራገረ የለም።..." ረሱል ﷺ
   
                    ክፍል ስድስት

    ለዚህ ነበር በወቅቱ ወደ እስልምና ገብተው የነበሩ አዳዲስ ሰዎች ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ያደረጉትን ይህንን ጉዞ አምኖ ለመቀበል የተሳናቸዉ፡፡ የቁረይሽ ሙሽሪኮችና ባላባቶች ይህንኑ ዜና በሰሙ ጊዜ ረሱልን (ሰ.ዐ.ወ) ለማሳጣትና ለማዋረድ የማይገኝ እድል ያገኙ ስለመሰላቸው ጮቤ ረገጡ፡፡ ክፍተትን ለስህተት ለመጠቀም ያላቸው አቋም ይገርማል፡፡

    በነገሩ ለመሳለቅና ለማሾፍም ወደ አቡበከር (ረ.ዐ) ዘንድ ሄዱ፡፡
እንደደረሱም ለአል ሲዲቅ እንዲህ አሏቸው፡- "አቡበክር ሆይ! ጓደኛህ የሚዘላብደውን ሰምተሀልን?” ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) በኢስራእና ሚዕራጅ ስላደረጉት ጉዞ የተናገሩትን ነገሯቸው፡፡ አቡበከርም(ረ.ዐ) "በእርግጥ እንዲህ ብሏል? አሉ፡፡“አዎ! ብሏል፡፡” አሏቸው፡፡ አቡበከርም (ረ.ዐ) "በእዉነት ይህንን ብሎ ከሆነ እውነትን ተናግሯል።” አሉ፡፡

   ቁረይሾቹም "ይህንን አምነህ ትቀበላለህ?” ሲሉ ደግመው
ጠየቋቸው፡፡ “ከዚህ የበለጠ ነገር ቢናገሩም አምናቸዋለሁ፡፡” ሲሉ
መለሱ..." ወደ እርሳቸው እንሂድ አሉ። ወደ ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ዘንድ
እንደደረሱም ስለ ኢስራእና ሚዕራጅ የተከተለውን ሁሉ በዝርዝር
ነገሯቸው፡፡ አቡበከርም እንዲህ አሉ፡- "እውነት ተናግረዋል! እውነት
ተናግረዋል! እርሶ የአላህ መልክተኛ መሆንዎን እመሰክራለው፡፡”
ረሱልም (ሰ.ዐ.ወ) "አቡበከር ሆይ! አንተ እውነተኛ ነህ፡፡” አሏቸው፡፡

       ከማንም የተሻለ ጉርብትና

  የመካ ከሓዲያን በረሱል (ሰ.ዐ.ወ) እና በተከታዮቻቸው ላይ
የሚያደርሱት ስቃይና ግፍ በጣም እየበረታ ሲመጣ! ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ለአቡበከር ወደ ሐበሻ ይሰደዱ ዘንድ ፈቀዱላቸው፡፡ ከቁረይሽ ጎሳዎች ዉስጥ በጣም የተከበረ ሰው የነበረው ኢብኑ ዱግና ይህንን ይሰማና፤ የሚሻለው የርሱ ጎረቤት ሆነው መኖር ከቻሉ ማንም ሊነካቸዉ እንደማይችል ለአቡበክር ይመክራቸዋል፡፡

    ሰይድ አቡበክር በኢብን ዱግና ምክር ይስማማሉ፡፡ አቡበክር (ረ.ዐ) የዚህ ሰውዬ ጎረቤት ሆነው በመኖር ብዙ ጊዜ ቁርኣን እየቀሩ ያለቅሱ ነበር። እንዲህ ሲያደርጉ ሴቶችና ህፃናት ከበዋቸው ያዳምጡ ስለነበር በጣም ይማረኩና ተፅዕኖ ያድርባቸው ነበር፡፡

     ቁረይሾች በዚህ ሁኔታ ብዙም ስላልተደሰቱ፤ ከዚህ ተግባር
እንዲታቀቡ ይነግሯቸው ዘንድ ኢብን ዱግናን ይልኳቸዋል፡፡ ኢብን
ዱግናም በተላኩት መሰረት አቡበክር በቤታቸው ሆነው እንዲቀሩ
ይነግሯቸዋል። አቡበክርም በመንገድ የሚያልፉ ሰዎች እንዲሰሟቸው በሚል በቤታቸው መስኮት አቅጣጫ ሆነው መቅራት ይጀምራሉ፡፡

     የመካ ቁረይሾች ይኸኛው ሁኔታም ቢሆን ስላልተስማማቸው ጎረቤታቸው ወደሆኑት ሰው (ኢብን ዱግና) ስሞታ ያቀርባሉ፡፡ ኢብን ዱዓናም ቁርአኑን መቅራት እንዲያቆሙ ለአቡበክር ይነግሯቸዋል።
አቡበክር ግን ቁርኣን መቅረቱን ማቆሙ በጭራሽ እንደማይችሉ
ይነግሯቸውና እንዲህ ይላሉ፡- "ወላሂ ሰዎች ቁርኣን እንዲሰሙ
ማድረጌን አላቆምም፡፡ ከፈለክ ጉርብትናህ ይቅርብኝ፡፡ ካንተ የተሻለና የበለጠ ጎረቤት አግኝቻለሁ፡፡” (ቁርኣንን ማለታቸው ነው፡፡)

                    ለቅሶ
      አቡበክር አስ-ሲዲቅ ቁርኣን በሰሙ ቁጥር እንባቸውን
አይቆጣጠሩም ነበር፡፡ በጣም ስቅስቅ ብለው ያለቅሳሉ፡፡ በተለይ ሱረቱል ዘልዘላን በቀሩ ቁጥር ማልቀስ የዘውትር ልማዳቸው ነበር፡፡

     ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) በመሞቻቸው ዕለት ታመው ነበርና ሶላት
እንዲያሰግዱ አቡበክርን ያዟቸዋል፡፡ ይሄኔ እሜቴ ዓኢሻ (ረ.ዐ) እንዲህ ይላሉ፡- “አንቱ የአላህ መልእክተኛ! አቡበክር እኮ ለስላሳ ስው ነው። ቁርኣን ሲቀራ እምባውን መቆጣጠር ስለማይችል ሰፉዋን ምን እንደሚል መስማት አይችሉም፡፡ ስለዚህ ዑመርን ይዘዟቸው...”

    በአንድ ወቅት ከየመን የመጣ ልዑክ ወደ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ዘንድ
ይመጣና ለእስልምና ቃል ኪዳን (ሙባየዓ) ይገባል፡፡ ልዑኩ ቁርኣን
ኢስማም ያለቅሳል፡፡ ይሄኔ አቡበክር እንዲህ ይላሉ..“ቀልቦቻችን
ሳይደርቁ በፊት እኛም እንዲህ ነበርን፡፡” ወዲያዉም ማልቀስ ይጀምራሉ፡፡

       እስኪ የታላቁን አቡበክር (ረ.ዐ) ሁኔታ ከራሳችን ሁኔታ ጋር
እናነፃፅረው፡፡ ለመሆኑ እኛ አላህን ፈርተን፣ ቁርኣን ሰምተን
ያለቀስነበትን ጊዜ እናስታውሳለን? ለምን ይሆን ቀልባችን እንዲህ
የደረቀው? ለምንስ ይሆን ከዓይናችን እንባ የጠፋው? መጠያየቅ አለብን!

      ስባት ባህሮችን የፈጠረው ኃያሉ አላህ (ሱ.ወ) እርሱን በመፍራት የሚወርድ እንባን ከእኛ መመልከት ይወዳል፡፡ ነገር ግን የእኛ ዐይን ይህን ከማድረግ ሰስቷል፡፡

          በአላህ ቃል ኪዳን ላይ የነበራቸው ፍጹም እምነት

ፋርሶች ሮሞችን በጦርነት ባሸነፉ ጊዜ፤ አላህ(ሱ.ወ)
የሚከተሉትን የቁርኣን አንቀጾች አወረደ....

{ الۤمۤ (1) غُلِبَتِ ٱلرُّومُ (2) فِیۤ أَدۡنَى ٱلۡأَرۡضِ وَهُم مِّنۢ بَعۡدِ غَلَبِهِمۡ سَیَغۡلِبُونَ (3) فِی بِضۡعِ سِنِینَۗ لِلَّهِ ٱلۡأَمۡرُ مِن قَبۡلُ وَمِنۢ بَعۡدُۚ وَیَوۡمَىِٕذࣲ یَفۡرَحُ ٱلۡمُؤۡمِنُونَ (4) بِنَصۡرِ ٱللَّهِۚ یَنصُرُ مَن یَشَاۤءُۖ وَهُوَ ٱلۡعَزِیزُ ٱلرَّحِیمُ (5) }    الروم: ١-٥

አሊፍ ላም፣ ሚም፡፡ ሩም ተሸነፈች። በጣም ቅርብ በኾነችው ምድር፡፡ እነርሱም ከመሸነፋቸው በኋላ በእርግጥ ያሸንፋሉ። በጥቂት ዐመታት ዉስጥ (ያሽንፋሉ) ትእዛዙም በፊትም በኃላም የአላህ ነዉ። በዚያ ቀንም ምእመናን ይደሰታሉ፡፡ በአላህ እርዳታ (ይደሰታሉ) የሚሻውን ሰው ይረዳል እርሱም አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡ (አል-ሩም 1-5)

     እነዚህ አናቅጽ ከወረዱ በኋላ አቡበክር አስ-ሲዲቅ በቁረይሽ
ወደ ሙሽሪኮች መሰብሠቢያ እየሄዱ "ሮሞች እንደሚያሸንፏቸው አርግጠኛ ነኝ፡፡” ማለት ጀመሩ፡፡ አቡበክር እንዲህ እርግጠኛ የሆኑት ከላይ የተገለጸዉን የአላህ (ሱ.ወ) ቃል ኪዳን መሠረት አድርገው ነዉ። ኡመያ ኢብን ኸለፍ ይህንን ሲሰማ “እስኪ እዉነተኛ ከሆንክ እንወራረድ” አላቸው፡፡ አቡበክርም ተስማሙ። ኡመያም “መቼ ነው ድል የሚያደርጉት” ሲል አቡበክርን ጠየቃቸው፡፡ እርሳቸውም “ከሶስት ዓመታት በኋላ” አሉት።

   ▻▻ኢንሻአላህ ይቀጥላል◅◅
http://t.me//@arebgendamesjid

  
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ
2.6K views17:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 21:09:20 አቂደቱል ዋሲጥያ
ሸይህ ዑመር አሊ
  ክፍል-12-
http://t.me//@arebgendamesjid
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ
ዘርፍ
96 views18:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 21:08:49 የአቡበክር አስ-ሲዲቅ (ረድየሏሁ ዐንሁ) ታሪክ

  "ከአቡበክር በስተቀር ማንኛውንም ሰው ወደ እስልምና ስጋብዘው ያላመነታና ያላንገራገረ የለም።..." ረሱል ﷺ
   
                    ክፍል አምስት

   አቡበክርም (ረ.ዐ) “እሺ ስንት ልክፈልህና ነፃ ትለቀዋለህ?” ብለው ይጠይቃሉ፡፡ “በሰባት ወቄት ወርቅ እሸጥልሃለሁ” ይላል። አቡበክርም (ረ.ዐ) “እሺ እከፍላለሁ” በማለት ይስማማሉ።
ከዚህም ኡመያ ሳቅ ይልና እንዲህ ይላቸዋል፡፡ “ታውቃለህ አቡበክር
ስአራት ወቄት ካልሆነ አልወስድም ብትለኝ ኖሮ እንኳ እሽጥለህ ነበር።” አቡበክርም (ረ.ዐ) መልሰው “ወላሂ መቶ ወቄት ብትጠይቀኝ እንኳ ከፍዬህ እወስደው ነበር፡፡” ይላሉ፡፡ ከዚያ ክፍያውን ፈጸሙና ቢላልን በነፃ ለቀቁት። ከቢላል በኋላም ሕፃናትንና ሴቶችን በገንዘባቸው ነፃ አውጥተዋል።

      አባታቸው ከደካማዎች ይልቅ ይመሰገኑ ዘንድ ጠንከር ያሉትን
ነፃ ቢያስወጡት እንደሚሻል ደጋግመው ቢነግሯቸውም አቡበክር (ረ.ዐ) ግን "ይህን የማደርገው የአላህን (ሱ.ወ) ውዴታ ለማግኘት እንጂ ለሌላ ለምንም አይደለም፡፡” ብለው ይመልሱላቸው ነበር፡፡

   መልካም ድርጊታቸውን ጭቃ ሊቀቡ የተነሱ የመካ ሙሽሪኮች
የሐሰት ፕሮፓጋንዳዎችን በአቡበክር (ረ.ዐ) ላይ ይነዙ ጀመር፡፡ “ቢላልን ነፃ እንዲወጣ ያደረገው እርሱ እንደሚለው የአላህን ውዴታ ለማግኘት ሳይሆን ከዚህ በፊት ቢላል የዋለለትን ዉለታ ለመመለስ ብሎ ነዉ።" እያሉ ሥራቸውን በማንኳሰስ አንጓጠጡ፡፡ በዚህ ጊዜ አላህ (ሱ.ወ) የሚከተለውን የቁርኣን አናቅጽ አወረደ

{ وَمَا لِأَحَدٍ عِندَهُۥ مِن نِّعۡمَةࣲ تُجۡزَىٰۤ (19) إِلَّا ٱبۡتِغَاۤءَ وَجۡهِ رَبِّهِ ٱلۡأَعۡلَىٰ (20) وَلَسَوۡفَ یَرۡضَىٰ (21) }

“ለአንድ ሰው እርሱ ዘንድ የምትመለስ ውለታ የለችም፡፡ ግን የታላቅ
ጌታውን ውዴታ ለመፈለግ (ይህን ሠራ)፡፡ ወደፊትም በእርግጥ
ይደሰታል፡፡” (አል-ለይል፡ 19-21)

    ሱረቱል ለይል በውስጧ ያካተተችው መልእክት በአቡበክር (ረ.ዐ) ላይ የተነዛው ሀሰት መሆኑን መግለጫ ነው፡፡ ሃያ አንድ አናቅፅን አካታለች፡፡

              ከሶሐቦች ሁሉ ጀግና
    አቡበክር አስ-ሲዲቅ (ረ.ዐ) ምንም እንኳ ጉልበታቸው ደካማና
ሰውነታቸው ለስለስ ያለ ቢሆንም በሐቅ ጉዳይ ግን መንፈሳቸው ጠንካራ ነበር። በአላህ(ሱ.ወ) ጉዳይ ማንንም አይፈሩም፡፡

   በአንድ ወቅት ስይድ ዓሊይ ቢን አቢጧሊብ "ከሰዎች ሁሉ ጀግና
ማንነው? እርሶ ነዎት አሚረል ሙእሚኒን?” ተብለው ሲጠይቁ
የሚከተለውን ምላሽ ሰጡ" የለም! ከሰው ሁሉ ጀግናው አቡበክር አስ-ሲዲቅ ናቸው። በአንድ ወቅት የቁረይሽ ከሃዲዎች ነብዩን (ሰ.ዐ.ወ) ከበው ሲያንገላቷቸው ተመለከትኩ፡፡ እኛ ራቅ ብለን ሁኔታውን እንመለከት ነበር፡፡ ለብቻቸው ሆነው ከሃዲዎቹን ገፈታተሯቸው፡፡ ከረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ዙሪያ ገለል አደረጉዋቸው፡፡ “አላህ ጌታዬ ነው የሚልን ሰው ልትገድሉ ነው እንዴ?” በማለት ተናገሯቸው፡፡ ከሐዲዎቹም ረሱልን (ሰ.ዐ.ወ) ተወት አደረጉና አቡበክርን ያዟቸው፡፡ ዑቅበት ቢን አቢ ሙዐጥ የሚባል ከሐዲ መጣና የአቡበክርን (ረ.ዐ) ፊት ይመታ ጀመር፡፡ ፊታቸው እስኪያባብጥ ድረስ በጫማው ደበደባቸው፡፡ አፍንጫቸው
እስኪቀላ ድረስ ፊታቸው አበጠ፡፡ ከፊታቸው ላይም ደም ይፈስ ጀመር፡፡ አቡበክር ሲዲቅ ራሳቸውን ሳቱ፡፡

     ትንሽ ቆይቶም የአቡበክር (ረ.ዐ) ጎሳዎች የሆኑ በኒ ተሚሞች
መጡና ወደ ቤታቸው ይዘዋቸው ሄዱ፡፡ ከመጎዳታቸው ብዛት ከሞት እንደማይተርፉ እርግጠኛ ነበሩ፡፡ ለእናታቸውም 'በሕይወት ከቆየ መግቢው፣ አጠጭውም' ብለዋቸው ሄዱ፡፡ ከዚያም ወደ ዑቅበት ተመልሰው ሄዱና አቡበክር (ረ.ዐ) ከሞት ሊበቀሉት እንደሚችሉ ዝተው ተመለሱ፡፡

    አቡበክር (ረ.ዐ) ከጉዳታቸው ትንሽ መለስ በማለት ዓይናቸውን
እንደከፈቱ ወዲያው የጠየቁት ጥያቄ «ረሱል እንዴት ናቸው?” የሚል ነበር፡፡ በወቅቱ ያልሰለመችው እናታቸው አጠገባቸው ነበረችና አሁንም ታስታውሰዋለህ እንዴ! አለቻቸው... እርሳቸውም "ወላሂ ያሉበትን ሁኔታ አውቄ ነፍሴ እስክትረጋጋ ድረስ እህልም ሆነ ውሃ አልቀምስም” ይላሉ፡፡

    በመቀጠልም "ወደ ኡሙ ጀሚል ፋጢማ ቢንት አል-ኸጣብ
(የሰይድ ዑመር እህት) ዘንድ ሂጅና ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ያሉበትን ሁኔታ
ጠይቂያት፡፡” አሏቸው፡፡ የአቡበክር (ረ.ዐ) እናት ወደ ተባሉበት ቦታ
ይሄዳሉ፡፡ ያኔ ቢንት አል-ኸጣብ መስለሟን ደብቃ ትኖር ነበር፡፡
የአቡበክር (ረ.ዐ) እናት ስለ ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ሁኔታ ይጠይቋታል።
እርሷም እንዲህ ትላለች "ወላሂ! ልጅሽንም ሆነ መሐመድን አላውቅም፡፡ ነገር ግን ደስ ካለሽ ልጅሽን ለመጠየቅ አብሬሽ ልመጣ እችላለሁ፡፡”

     ከዚያም ተከታትለው ወደ አቡበክር (ረ.ዐ) ዘንድ ይሄዳሉ፡፡
አቡበክርም "ፋጢማ ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) እንዴት ናቸው?” ሲሉ
ይጠይቋታል፡፡ እርሷም "እኔ ሙሐመድ ማን እንደሆነ አላውቅም፡፡”
ስትል ትመልሳለች፡፡ አቡበክርም ነገሩ ገብቷቸው "አትፍሪ እርሷ እናቴ ነች።” ይሏታል፡፡ ከዚያም “ደህና ናቸው ምንም አልሆኑ፡፡” ትላለች አቡበክርም "ወላሂ! በዓይኔ እስካላየኋቸው ድረስ እህልም ሆነ ውሃ አልቀምስም” ይላሉ፡፡ እናትየውም "እግርህ እስኪሻልህ ድረስ ትንሽ ጠብቅ” ይሏቸዋል፡፡

    እርሳቸውም እግራቸው መራመድ እያቃተውም ቢሆን ብድግ
ብለው በመነሳት ሁለቱም ሴቶች ደግፈዋቸው የአል-አርቀም ቢን አቢ አል-አርቀም ቤት ይደርሳሉ፡፡ በር ሲያንኳኩ ይከፍትላቸዋል፡፡ ረሱል(ሰ.ዐ.ወ) አቡበክርን ሲያዩዋቸው በጣም ያዝኑላችዋል። እቅፍ ያደርጓቸዋል፡፡ አቡበክር የረሱልን (ሰ.ዐ.ወ) ማዘን ሲመለከቱ «የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ወላሂ ከፊቴ በስተቀር ደህና ነኝ ምንም አልሆንኩም» ይላሉ። ረሱልም (ሰ.ዐ.ወ) በጣም አዝነው ዱዓ ያደርጉላቸዋል፡፡

    አቡበክርም እንዲህ ይሏቸዋል፡፡ "አንቱ የአላህ መልዕክተኛ!
እናቴን አላህ ሙስሊም እንዲያደርጋት ዱዓ አድርጉላት፡፡” ነብዩም
(ሰ.ዐ.ወ) "አላህ ሆይ! የአቡበክርን እናት ወደ ቀጥተኛው ጎዳና ምራት” ብለው ዱዓ ያደረጋሉ። የአቡበክር እናትም እዚያው እንደቆሙ "ከአላህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም፡፡ ሙሐመድም የአላህ መልእክተኛ ናቸው፡፡” በማለት የምስክርነት ቃላቸውን ይሰጣሉ፡፡

       አስ-ሲዲቅ ስለ እስልምና የነበራቸው ድንቅ አቋሞች

   ሰይድ አቡበክር አስ-ሲዲቅ (ረ.ዐ) በእስልምና ዙሪያ የነበራቸውን
አቋሞች ስናይ ለዲን የነበራቸውን ፍቅር ከፍተኛነት መረዳት እንችላለን፡፡ አስ-ሲዲቅ ሁሉ ነገራቸውን ለዲን የበላይነት ሲሉ
ገብረዋል። ነፍሳቸውን፣ ገንዘባቸውን፣ ቤተሰባቸውን ደማቸውን ይህን ሃይማኖት ለማገልገል ሲሉ ሰጥተዋል፡፡ ለእስልምና የበላይነት ሲሉ ሁለመናቸውን ከፍለዋል፡፡

   ስለ አስ-ሲዲቅ አቋሞች ስንነጋገር ዋነኛው ዓላማችን ሁሉም
ሙእሚን በዓርአያነት እንዲከተላቸው ነው፡፡ አቡበክርን (ረ.ዐ) ተምሳሌት አድርገን ከእስልምና ረገድ ያለብንን ኃላፊነቶች ሁሉ በአግባቡ እንድንወጣ ያግዘናል።

            ዕለተ-አል ኢስራእ ወል ሚዕራጅ

   ምንም ዓይነት ፈጣን የትራንስፖርት አገልግሎት ባልነበረበትና
በማይታወቅበት ዘመን አንድ ሰው አንድ ሙሉ ሌሊት ባልሞላ ጊዜ
ዉስጥ ከመካ ተነስቶ ቁድስ ደርሶ ተመለሰ ተብሎ ቢነገር የሚታመን ነገር አልነበረም ::
915 views18:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 21:51:59 የአቡበክር አስ-ሲዲቅ (ረድየሏሁ ዐንሁ) ታሪክ

  "ከአቡበክር በስተቀር ማንኛውንም ሰው ወደ እስልምና ስጋብዘው ያላመነታና ያላንገራገረ የለም።..." ረሱል ﷺ
   
                    ክፍል አራት

              የአስ-ሲዲቅ (ረ.ዐ) ያሰብዕና ቁልፍ
  ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ይላሉ፡፡ "ከሰዎች ሁሉ በእውነተኛ እምነቱ ወደር የማይገኝለት ስው አቡበክር አስ-ሲዲቅ ነው፡፡” እንዲህም ይላሉ... "ከሰዎች ሁሉ በጽኑ እምነቱ አቻ የማይገኝለት ሰው አቡበክር አስ-ሲዲቅ ነው።”

   ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፡- “የኡማው ኢማን በአንድ መዳፍ፤ የአቡበክር ኢማን ደግሞ በሌላ መዳፍ ሆኖ ቢመዘን የአቡበክር ኢማን ባመዘነ ነበር፡፡” ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) "አቡበክር የበለጣችሁ በሶላትና በፆም ብዛት ሳይሆን በቀልቡ ውስጥ ጸዳል በሆነው ኢማኑ ነው፡፡” ሲሉመስክረዋል፡፡

   የአቡበክር አስ-ሲዲቅ (ረ.ዐ) የስብዕናቸው ቁልፍ የሆነው ለእውነት - የነበራቸው ፍጹም ውዴታ ነበር፡፡ ለእውነት መስዋእት
ለመሆን ሲሉ እድሜያቸውንም ሆነ ደማቸውን ከመስጠት ለአፍታም አላንገራገሩም፡፡
    አስ-ሲዲቅ (ረ.ዐ) ሕይወታቸውን ሁሉ ምንም ሳይሰስቱ ለነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) የሰጡት የእውነት ሁሉ መገኛ ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) በመሆናቸው ነበር፡፡
     ነብዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ወደ ዝንተ-ዓለማዊው ሕይወት
በተሸጋገሩበት ቅጽበት ሶሀባዎች ሁሉ ተደናግጠው የሚያደርጉትን ሲያጡ ግልጽና ትክክለኛ አቋም የወሰዱት ብቸኛው ሰው አቡበክር (ረ.ዐ) ነበሩ፡፡ የአቡበክርን (ረ.ዐ) ሕይወት ምንጊዜም ቢሆን ሙሉ በሙሉ የሚቆጣጠረው እውነት ብቻ ነበር፡፡

   ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) መካ ውስጥ የእውነት ተምሳሌት ሆነው ብቅ ሲሉ አቡበክር (ረ.ዐ) በእጃቸው ያለውን ነገር ሁሉ ለነብዩ (ሰ.ዐ.ወ)
በመስዋኣትነት አቀረቡ፡፡ ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ለሕልፈት ሲበቁም አስ-ሲዲቅ (ረ.ዐ) በእውነት መስመር ላይ ጸኑ፡፡

   ዑለማዎች አንድ በጋራ የሚስማሙበት ነገር አለ፡፡ ይኸውም
ከነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) በመቀጠል ለመጀመሪያ ጊዜ ለአላህ (ሱ.ወ) ሱጁድ ያደረጉ(በግንባሩ ተደፍቶ የስገደ) እመቤት ኸዲጃ (ረ.ዐ) ናቸው፡፡ ከወንዶች መጀመሪያ የሰለመው ደግሞ አቡበክር አስ-ሲዲቅ (ረ.ዐ) ናቸው። ከሕፃናት የመጀመሪያው እስልምናን የተቀበለ ደግሞ ዓሊይ ቢን አቢጧሊብ (ረ.ዐ) ሲሆኑ ከአገልጋይ ደግሞ መጀመሪያ እስልምናን የተቀበሉት ዘይድ ቢን ሐሪስ (ረ.ዐ) ናቸው፡፡

   ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ለመጀመሪያ ጊዜ ኣቡበክርን (ረ.ዐ) ወደ እስልምና ሲጋብዟቸው ያለምንም ማመንታት ነበር የተቀበሏቸው፡፡ ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ይህንኑ አስመልክተው እንዲህ ይሉናል "ከአቡበክር በስተቀር ማንኛውንም ሰው ወደ እስልምና ስጋብዘው ያላመነታና ያላንገራገረ የለም፡፡ አቡበክር ግን ስለ እስልምና ስነግረው ወዲያውኑ ያለማመንታትና ያለማንገራገር ተቀበለኝ፡፡ ከአላህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም ሙሐመድም የአላህ መልክተኛ ነው በማለት እዚያው መሰከረ፡፡”

  ሰይድ አቡበክር (ረ.ዐ) ወደ እስልምና ጥሪ ሲደረግላቸው
ወዲያውኑና ያለማመንታት የተቀበሉት እንዲሁ በስሜትና በዘፈቀደ
ኣልነበረም፡፡ ምንም ዓይነት ራዕይ ሳይኖራቸው ቀርቶም አይደለም፡፡
ይልቁንም ሐቅ የተባለን ነገር ወዲያውኑ የመቀበልና የማመን ቋሚ
ባህሪ ስለነበራቸው ነው። የእስልምናን እውነት ከተቀበሉበት ዕለት
አንስቶ የብርሃን ፀዳል ቀልባቸውን ይሞላ ጀመር፡፡
እዚህ ቦታ ላይ ለአፍታ ቆም ብለን በማስተዋል ከእኝህ ታላቅ
ሰው መማር ይኖርብናል። እስልምና እውነት መሆኑን አምነን
እስከተቀበልን ድረስ፤ ሁለመናችንን በእስልምና ጥላ ሥር ማኖር
ይገባናል፡፡ አቡበክርን (ረ.ዐ) ተምሳሌት ማድረግ ይኖርብናል፡፡

   ከላይ እንደተጠቀሰው አቡበክር አስ-ሲዲቅ (ረ.ዐ) እኛን የበለጡን በሶላት ወይም በዖም ብዛት ሳይሆን የእውነትን ብርሃን ሲመለከቱ በዚያ ውስጥ ተጠቅልለው ለመኖር አንዳችም ባለማመንታታቸው ነው። ነፍሳቸውን፣ ሃብታቸውን፣ ጊዜያቸውን ሁሉ ለእውነት ሰውተዋል፡፡ ለእውነት ሲሉ ደማቸውን ሰጥተዋል፣ ገንዘባቸውን ሁሉ አፍስሰዋል። ኃይላቸውን፣ ችሎታቸውን፣ ልጆቻቸውን ለእውነት ሰጥተዋል።

      ከአቡበክር (ረ.ዐ) ልንማር ከሚገባን ቁም ነገር አንዱ አንድን
እውነት ካወቅን ሕይወታችንን በሙሉ ለዚህ እውነት መስጠትን ነው::

    አቡበክር አስ-ሲዲቅ (ረ.ዐ) እስልምናን ሳያወላዱ የተቀበሉት ብዙ ተነግሯቸው ሳይሆን ከነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ጣፋጭ አንደበት በሰሟት ጥቂት ንግግር ነበር፡፡ የእስልምናን መልዕክት ለማስራጨት ባጭር ታጥቀው የተነሱት ወዲያው እንደሰለሙ ነበር፡፡ ለዳዕዋ በተነሱ በመጀመሪያው ሳምንት ውስጥ ጀነት ከተበሰረላቸው (ዐሸረቱል ሙበሸሪን) አስር ሰዎች ውስጥ ስድስቱ በእርሳቸው እጅ ለመስለም በቅተዋል፡፡ እነዚህም፦1. ሰዐድ ቢን አቢ ወቃስ 2.ዙበይር ቢን አል-ዓዋም 3. ጦልሐ ቢን 4. አቡ ዑበይዳህ ቢን አል-ጀራህ 5. ዐብዱራህማን ቢን ዐውፍ 6. ዑስማን ቢን ዓፋን ናቸው፡፡
    እነዚህ ሁሉ ዕንቁዎች በአቡበክር (ረ.ዐ) አማካኝነት የሰለሙት
በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ ነው፡፡ በዚህ ወቅት አስ-ሲዲቅ ስለ
እስልምና ያውቁ የነበረው ጥቂት ነገር ብቻ ነበር።

   ከዚህ አንፃር እስኪ የእኛን ሁኔታ እንገምግመው፡፡ ስለ እስልምና
ብዙ እናውቃለን፡፡ በእኛና በአቡበክር (ረ.ዐ) መካከል ያለው ልዩነት አንድ ነው፡፡ ይኸውም እርሳቸው እውነትን አወቁ ወዲያውኑ ጥቅልል ብለው ለእውነት ብቻ መኖር ጀመሩ፡፡ እኛ ግን እውነትን በብዙ አቅጣጫ አውቀናል፡፡ ለእውነት ለመኖር ግን ዝግጁዎች አይደለንም፡፡ እውነትን አውቀን ለእውነት ብቻ ለመኖር ካልቻልን በእውነት ስህተተኞች ነን።

   አቡበክር (ረ.ዐ) እውነትን አወቁ፡፡ ስሜታቸው ለእውነት ተማረከ።
ለእውነትም ሌትተቀን ሠሩ፡፡ ከላይ የተጠቀሱት ስድስት ዕንቁዎች
ሙስሊም እንዲሆኑ ምክንያት የሆኑት አቡበክር (ረ.ዐ) ናቸው። እነዚህ ሰዎች የሠሯቸው መልካም ሥራዎች ሁሉ (የነርሱ ምንም ሳይጓደል) ለአቡበክር አስ-ሲዲቅ (ረ.ዐ) ነው የሚመዘገቡት፡፡ ያደረጉት ዒባዳ፣ ጂሐድ፣ ምጽዋት፣ ዳዕዋ... ሁሉ ምንዳው ለአስሲዲቅ (ረ.ዐ) ነው፡፡

    አቡ ዑበይዳ ቢን አል-ጀራህ ሻምን ሰዐድ ቢን አቢ ወቃስ ደግሞ
ኢራቅን የከፈቱና ያቀኑ ናቸው፡፡ የፋርስንም ቅኝ አገዛዝ ያንኮታኮቱ፡
ናቸው፡፡

    በአቡበክር (ረ.ዐ) እጅ የሰለሙት እጅግ በርካታ ሰዎች ናቸው።
ከእነዚህም ውስጥ አል-አርቀም ቢን አቢ አርቀም፣ ዑስማን ቢን መዝዑን ሊጠቀሱ ይችላሉ። ይህ ብቻ አይደለም፡፡ በባሪያ ፍንገላ ሥር የነበሩ ብዙ ሰዎች በአቡበክር (ረ.ዐ) ገንዘብ ነፃ ሊወጡ ችለዋል። መጀመሪያ ነፃ የወጡት ሰባት ሰዎች ናቸው። ከነዚህ ውስጥ ቢላል ቢን ረባህ(ረ.ዐ) የመጀመሪያው ነው፡፡

  የቢላል ገዢ ኡመያ ቢን ኸለፍ ይሰኛል። በመስለሙ ምክንያት
ቢላልን ይቀጣውና ያስቃየው ነበር፡፡ አንድ ቀን ቢላልን እያሰቃየው ሳለ አቡበክር (ረ.ዐ) በአጠገባቸው ሲያልፉ ይህንን ይመለከቱና ለኡመያ እንዲህ ይሉታል። “ይህ ምስኪን አያሳዝንህም?" ኡመያም “አንተ እዘንለት” ሲል ይመልሳል፡፡ አቡበክርም (ረ.ዐ) “እሺ ስንት ልክፈልህና ነፃ ትለቀዋለህ?” ብለው ይጠይቃሉ፡፡ 

----------ኢንሻ አላህ ይቀጥላል--------------

የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ
http://t.me//@arebgendamesjid
2.0K views18:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 20:25:37 አቂደቱል ዋሲጥያ
ሸይህ ዑመር አሊ
  ክፍል-11-
http://t.me//@arebgendamesjid
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ
ዘርፍ
162 views17:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 21:44:13 واعْلَمُوا رحمكم الله أن فِي الصَّلاة على سيدنا مُحَمَّد ﷺ عشر كرامات :

إحْداهُنَّ: صَلاة الملك الجَبّار
والثّانيِة: شَفاعَة النَّبِي المُخْتار
والثّالِثَة: الِاقْتِداء بِالمَلائِكَةِ الأبْرار
والرّابِعَة: مُخالفَة المُنافِقين والكفّار
والخامِسَة: محو الخَطايا والأوزار
والسّادِسَة: قَضاء الحَوائِج والأوطار
والسّابِعَة: تنوير الظَّواهِر والأسرار
والثّامِنَة: النجاة من عَذاب دار البَوار
والتاسعة: دُخُول دار الرّاحَة والقرار
والعاشرة: سَلام الملك الغفار.

ابن الجوزي | بستان الواعظين
1.8K views18:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 20:15:43 አቂደቱል ዋሲጥያ
ሸይህ ዑመር አሊ
  ክፍል-10-
http://t.me//@arebgendamesjid
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ
ዘርፍ
211 views17:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 19:30:42 የአቡበክር አስ-ሲዲቅ (ረድየሏሁ ዐንሁ) ታሪክ

  "የኡማው ኢማን በአንድ መዳፍ፤ የአቡበክር ኢማን ደግሞ በሌላ መዳፍ ሆኖ ቢመዘን የአቡበክር ኢማን ባመዘነ ነበር፡፡” ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ)
   
               ክፍል ሦስት
   
     የአስ-ሲዲቅ አራተኛ ሚስት የአል-ኸዝረጅ ጎሳ አባል የሆኑት
እመቤት ሐቢባ ቢንት ዘይድ አል-ኸዝረጂይ ናቸው፡፡ አቡበክር (ረ.ዐ) በሞት የተለዩዋቸው ቅሪት ሆነው ነበር፡፡ ከአስ-ሲዲቅ (ረ.ዐ) ሕልፈት በኋላ ኡሙ ኩልሱም ቢንት አቡበክርን ወልደዋል፡፡ በጥቅሉ ከሰይድ አቡበክር (ረ.ዐ) አብራክ የተገኙ ስድስት ልጆች ነበሩ። ሶስት ወንዶችና ሶስትሴቶች።

          ያአስ-ሲዲቅ ሰውነት ገፅታ

   ሰይድ አቡበክር አስ-ሲዲቅ (ረ.ዐ) መካከለኛ ሰው ነበሩ። እግሮቻቸው ቀጠን ይላሉ፡፡ ታፋቸው ብዙም ወፍራም አልነበረም፡፡ ዓይኖቻቸው ጎድጎድ ያሉ ሆነው ባለ ግርማ ሞገስ ነበሩ፡፡ አጭርም ረዥምም አይባሉም፡፡ መካከለኛ ሰው ነበሩ። አንገታቸውን ትንሽ ደፋ ያደርጉ ነበር፡፡ በጣም ነጭ ሲሆኑ፡፡ ፂማቸው ለዓይን ማራኪ ነው፡፡ በሂናም ያቀልሙት ነበር፡፡ ግንባራቸው ያበራ ነበር፡፡ አቡበክር (ረ.ዐ) ቀጥ ያለና ሰልካካ አፍንጫ ነበራቸው፡፡

           ዋና ዋና ባህሪዎቻቸው

    በሕይወታቸው ጣዖት አምልከው አለማወቃቸው

  ሰይድ አቡበክር አስ-ሲዲቅ (ረ.ዐ) ከመስለማቸው በፊትም ቢሆን
የነበራቸው እውቅ ባህሪ አንዲትም ቀን እንኳ ለጣኦት ሰግደውና
አጎብድደው አለማወቃቸው ነበር፡፡

በአንድ ወቅት አባታቸው ለመካ ጣዖታት ክብር እንዲሰጡና
እንዲያጎበድዱ አቡበክር ሲዲቅን (ረ.ዐ) ያዙዋቸዋል፡፡ ይገፋቸዋል፣
አቡበክርም (ረ.ዐ) የዋዛ አልነበሩምና አባታቸውን ተወት በማድረግ ወደ ጣዖታቱ ዘወር ይሉና እንዲህ ይላሉ፡፡ እስቲ አቅሙና ችሎታው ካላችሁ “አብሉኝ... አጠጡኝ... አልብሱኝ” የግዑዛኑ ምላሽም ዝምታ ይሆናል:: አቡበክር አስ-ሲዲቅም (ረዐ) ወዲያው ድንጋይ አንስተው ወደ ግዑዛኑ በመወርወር እንክትክቱን ያወጡታል፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ወደነዚህ ጣኦታት ዞር ብለው አያውቁም፡፡

    ከዕለታት አንድ ቀን የመካ ጣዖታዊያን ኣስ-ሲዲቅን (ረ.ዐ)
“አቡበክር ሆይ! ለነላትና ዑዛ አትሰግድም?” ይሏቸዋል፡፡ አቡበክርም (ረ.ዐ) “ለመሆኑ ላትና ዑዛ ምንድን ናቸው?” ሲሉ መልሰው ይጠይቃሉ... “የአላህ ሴት ልጆች ናቸው በማለት ጣዖታዊያኑ ይመልሳሉ...” “አስ-ሲዲቅም እናታቸውስ ማን ትባል ይሆን!” በማለት ተሳለቁባቸው።

        አስካሪ መጠጥ (ኸምር)
           የሚባል ነገር ቀምሰው አለማወቃቸው

  አቡበክር አስ-ሲዲቅ (ረ.ዐ) ሙስሊም ከመሆናቸው በፊት ለሰላሳ
ስምንት ዓመታት ያህል ቢኖሩም የአስካሪ መጠጥ ጣዕም ምን ምን እንደሚል እንኳ አያውቁም ነበር። ስለዚህ ጉዳይ ተጠይቀው “ሳየው እራሱ ይከረፋኛል” ብለዋል፡፡

   በአንድ ወቅት አንድ ሰው በመጠጥ ናላው ዞሮ ከመሬት ላይ
ቆሻሻ እያነሳ ሲመገብ ይመለከቱና በጣም ስለዘገነናቸው ራሳቸውን
በእንዲህ ዓይነቱ ወራዳ ነገር እንደማያስገቡ መማል መገዘታቸው ተነግሯል፡፡ አስካሪ መጠጥ የሚጠጣ ሰው ካለ የእኚህን ታላቅ ሶሐቢ አርአያነት በመከተል እርግፍ አድርጎ ሊተወው ይገባል፡፡

       ከቁረይሽ ጋር የነበራቸው ጥብቅ ቁርኝት
ሰይድ አቡበክር አስ-ሲዲቅ (ረ.ዐ) ከእስልምና በፊት በጣም
በሚያስገርም አኳኋን ሰውን ሁሉ ይወዱ ነበር፡፡ አቡበክር አስ-ሲዲቅ (ረ.ዐ) ስለ ቁረይሽ ጎሳ የጠለቀ እውቀት ነበራቸው፡፡ ይህ እውቀታቸው ወደ አላህ (ሱ.ወ) ይደረግ ለነበረው ዳዕዋ ብዙ ወሳኝ አስተዋጽኦዎችን አበርክቷል፡፡ ከረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ጋር ሆነው ወደ አንዳንድ ጎሳዎች ዘንድ ይሄዱ በነበረበት ጊዜ ሰለ ጎሳዎቹ ዝርዝር ሁኔታ ለነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ያብራሩላቸው ነበር፡፡ እንዲህ ባይሆን ኖሮ ለእነዚህ ስዎች በሚገባቸው መልኩ ዳዕዋ ማድረጉ ለረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ቀላል አይሆንም ነበር፡፡

   ከዕለታት አንድ ቀን ዳዕዋ ለማድረግ ከነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ጋር
በመሆን ወደ አንድ ጎሳ ይሄዳሉ፡፡ የዚህ ጎሳ አባል የሆነና ስሙ ዘሒር የሚባል አንድ ገጣሚና ባለቅኔ ነበር፡፡ አቡበክር አስ-ሲዲቅ የዚህን ሰው ማንነትና የሚገኝበትን ቦታ ለረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ይነግራቸዋል፡፡ ቦታው ላይ ሲደርሱ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) የጎሳው አባላት ለሆኑ የጎሳ አለቆች አንድ በአንድ ሠላምታ ያቀርባሉ፡፡ አቡበክር አስ-ሲዲቅም በፊናቸው ነብዩን (ስ.ዐ.ወ) ያስተዋውቃሉ፡፡ እንዲህ እንዲህ እያሉ ዘሒር ዘንድ ሲደርሱ አስ-ሲዲቅ “ይህ ሰው ዘሒር ነው፡፡” ብለው ይነግሯቸዋል። ረሱልም (ሰ.ዐ.ወ) “ባለቅኔው!” ብለው ሰላም ይሉታል።

   ባለቅኔው ዘሒር እንዲህ ይላል... “ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) እኔን
በማወቃቸው የተደሰትኩትን ያህል መቼም ቢሆን ተደስቼ አላውቅም፡፡”

      ዓረብ ፔንሱሳን (ጀዝረተል ዓረቢያ)ያዳረሱ ነጋዴ

      ሰይድ አቡበክር አስ-ሲዲቅ ዓረብ ፔንሱላን ያካለሉ ነጋዴ መሆናቸው በጣም ወሳኝ ነገር ነበር፡፡ እጅግ በጣም በርካታ ከሆነ ሰዎች ጋር አስተውቋቸዋል፡፡ ነብዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ነብይ ሆነው በተነሱ ጊዜ የአስ-ሲዲቅ(ረ.ዐ) ኃብት አርባ ሺህ ዲርሃም ይገመት ነበር፡፡ ወደ መዲና ሲሰደዱ ደግሞ አምስት ሺህ ዲርሃም ነበራቸው። ለኸሊፋነት ሲታጩ ግን ሰባራ ሳንቲም አልነበራቸውም፡፡
ሰይድ አቡበክር (ረ.ዐ) ኃብታቸውን በሙሉ ለዳዕዋው ማካሄጃ
አውለዋል፡፡ በዚህም ምክንያት ከዚህ አለም በሞት ሲለዩ ስድስት ሺህ ዲርሃም እዳ ነበረባቸው፡፡

           የነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ባልንጀራ
   አስ-ሲዲቅ (ረ.ዐ) የነብዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ውድ ጓደኛ ነበሩ፡፡
በሁለቱ መካከል ጥልቅ የሆነ ውዴታና ፍቅር ነበር፡፡ ረሱል(ሰ.ዐ.ወ) ከአጎታቸው አቢጧሊብ ጋር ለንግድ ወደ ሻም ተጉዘው በነበረበት ወቅትና ከባህታዊው ቡሐይራ ጋር በተገናኙ ጊዜ አቡበክር (ረ.ዐ) አብረዋቸው እንደነበሩ ይነገራል፡፡

   ------- ኢንሻ አላህ ይቀጥላል------

http://t.me//@arebgendamesjid
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ
218 views16:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 09:12:43 #በወንጀል #ምክንያት የሚመጣን ቅጣት ሊያስቀሩ የሚችሉ ነገሮች

የአላህን ምህረት ማግኘት ትልቅ ዕድል ነው፣ወንጀላችንን ያለሱ ማንም
ሊምረንና ይቅር ሊለን አይችልምና!

ሙእሚን ወንጀሉ ያሳስበዋል
ሙናፊቅ ግን ከምንም አይቆጥረውም
ቁርኣንና ሐዲሥ የወንጀል መዘዙ ሰዎች/ሰሪዎቹ ላይ እንዳይደርስ
የሚያደርጉ 10- ነገሮች እንዳሉ አመላክተዋል እነሱም፥

➊ ተውበት (ተጸጽቶ ወደ አላህ መመለስ)

➋ኢስቲጝፋር ማድረግ

➌ መልካም ስራዎችን ማብዛት

➍ ስንሞት ሙእሚኖች የሚያደርጉልን ዱዓና ኢስቲጝፋር ለምሳሌ ሰላተል-ጀናዛ
ላይ

➎ ለሞተ ሰው የሚደረጉ መልካም ነገሮች ለምሳሌ ሰደቃ...

➏ የነቢዩ ﺻﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻠﻴﻪ ﻭﺳﻠﻢ ምልጃ

➐ ሙእሚንን ዱኒያ ላይ የሚገጥሙ የተለያዩ ችግርና መከራዎች

➑ የቀብር ጭንቀትና ፈተና/ድንጋጤ

➒ የቂያማ ቀን መከራና ስቃይ

➓ ከወንጀለኛው ወይም ከሰው ልጆች በኩል ምንም ሳይደረግ በአላህ
እዝነትና ይቅር ባይነት
በወንጀላችን ምክንያት ኣኺራ ላይ ይጠብቀን የነበረ ቅጣት ሊቀር ይችላል::
(ከሸይኹል-ኢስላም ንግግር የተወሰደ)

ወንጀልን መጀመሪያውኑ ከበሽታ በላይ እንጠንቀቅ ከተፈተንን ግን ተስፋ
አንቁረጥ የአላህ ረሕመቱ ሰፊ ነው!
ከላይ ከተጠቀሱ ነገሮች በአንዱ ምክንያት ምህረትን እንደምናገኝ ተስፋ
እናድርግ

ዛሬ ነገ ሳንልና ሞት ሳይቀድመን ተጸጽተን እንመለስ!
መስፈርቱን ያሟላ ተውበት የማይሰርዘው ወንጀል የለም!
አብሺሩ ያ ዒባደላህ
( ﻟَﺎ ﺗَﻘْﻨَﻄُﻮﺍ ﻣِﻦْ ﺭَﺣْﻤَﺔِ ﺍﻟﻠﻪ )

SHARE SHARE
http://t.me//@arebgendamesjid
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ
2.9K views06:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ