Get Mystery Box with random crypto!

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

የቴሌግራም ቻናል አርማ arebgendamesjid — የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች
የቴሌግራም ቻናል አርማ arebgendamesjid — የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች
የሰርጥ አድራሻ: @arebgendamesjid
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.19K
የሰርጥ መግለጫ

بسم الله الرحمن الرحيم
📮እንኳን ወደዚህ ቻናል ተቀላቀሉ‼️
በዚህ ቻናል ቂርአቶችን፣ ሙሐድራዎችን፣ዳዐዋዎችን እና ሌሎችንም ከአረብገንዳ መስጊድ በአሚሩ አማካኝነት በቀጥታ የምታገኙበት ቻናል ነው።
ሃሳብ አስተያዬት ካለ በዚህ ያድርሱን ⤵️
@ye_Arebgenda_mesgid_wetatoch_bot

Ratings & Reviews

1.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-09-02 10:04:04 #የጁምአ_ቀን

ነብዩ ሙሐመድ (ሰለላሁ ዐለይሂ .ወሰለም )እንዲህ ብለዋል ፡-
አርብ(ጁመዓ) ቀን፡ ገላውን ታጥቦ መላ ሰውነቱን አፀዳድቶ ፡ቅባትና ሽቶ ከተቀባ በሗላ ጁመአ ለመስገድ ቀደም ብሎ ወደ መስጊድ ፡በመሔድ ሌሎች ሰዎችን ሳይገፋና ሳይረብሺ በፀጥታ ቦታውን ለሚይዝ ፡ከዚያም የቻለውን ያህል (ነፍል) ከሰገደ በሗላ በፀጥታ ኹጥባን(የኢማሙን ንግግር )ለሚያዳምጥ ሰው ከዚያ ጁመዓ ጀምሮ እስከሚቀጥለው ጁመአ ድረስ በመካከል ያለው ሐጢያቱን አላህ ይተውለታል፡፡ ነብዩ{ሰ,ዐ,ወ} ስለ ጁምአ ቀን ታላቅነት ሲናገሩ የጁምአ ቀን የቀኖች ሁሉ ኑጉስ ነው እነዚህ አምስት ነገሮች በጁምአ ቀን ተከስተዋል ብለዋል። እነሱም
1, አላህ አደምን የፈጠረው በጁመአ ቀን ነው፣
2, አደም ከጀነት የወጡት በጁምአ ቀን ነው፣
3, አደም የሞተውም በጁመአ ቀን ነው፣
4, ቂያማ የምትቆመውም በጁመአ ቀን ነው፣
5, በጁምአ ቀን የሆነች ሠአት አለች።አንድ የአላህ ባሪያ የጠየቀውን ነገር ይሠጠዋል፣ያቺን ሠአት ካገኛት ሀራም ነገር እስካልሆነ ድረስ አላህ ይቀበለዋል። በሌላ የሀድስ ዘገባ አንድ ሰው ታጥቦ ያለውን ጥሩ ልብስ ለብሶ ሽቶ ተቀብቶ ወደ መስጂድ ሄዶ ማንንም አዛ ሳያደርግ ኢማሙ ቁጥባ ሲያደርጉ ዝም ብሎ ከሠማ ጁማአውን ከሰገደ አላህ ካለፈው ጁምአ እሥከ አሁኑ ጁምአ ያለውን ወንጀሉን ያብስለታል። በሌላ የሀድስ ዘገባ የጁምአ እለት በመጀመሪያ ሠአት ወደ መስጅድ የገባ ግመል ሰደቃ እንዳደረገ ይፃፍለታል። ከዚህም አርፍዶ የመጣ የቀንድ ከብት ሠደቃ እንዳደረገ ይፃፍለታል። ከዚህም አርፍዶ የመጣ በግ/ፍየል ሰደቃ እንዳደረገ ይፃፍለታል። ከዚህም አርፍዶ የመጣ ዶሮ ሰደቃ እንዳደረገ ይፃፍለታል። ከዚህም አርፍዶ የመጣ እንቁላል ሠደቃ እንዳደረገ ይፃፍለታላ። ኢማሙ ሚንበር ላይ ሲወጡ የሚመዘግቡት መላኢኮች የኢማሙን ኹጥባ ለመስማት መስጂድ ይገባሉ።

የአላህ መላእክተኛ(ሰ,ዐ,ወ) እንድህ ብለዋል፦

የጁምአ ቀን በእኔ ላይ ሠላወትን ማውረድ አብዙ፣ማንኛውም ሠው የጁምአ ቀን በእኔ ላይ ሠላዋት አያወርድም ሠላዋቱ ቢቀርብልኝ እንጅ።

{አልባኒ ሶሂህ ብለውታል} ‌"እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በዐርብ ቀን ለስግደት ጥሪ በተደረገ ጊዜ ወደ አላህ ማውሳት ኺዱ። መሸጥንም ተዉ፡፡ ይህ የምታውቁ ብትኾኑ ለእናንተ በጣም የተሻለ ነወ።" ‌ "ሶለቲቱም በተፈጸመች ጊዜ በምድር ላይ ተበተኑ። ከአላህም ችሮታ ፈልጉ፡፡ አላህንም በብዙ አውሱ፡፡ ልትድኑ ይከጀላልና፡፡" ((62:910)

[የጁመአ ቀን ሱናወች] ~‌
~ገላን መታጠብ
~ ጥሩ ልብስ መልበስ
~ሽቶ መቀባት ለወንዶች
~ ሲዋክ
~ ማልዶ በግዜ ወደ መስጅድ መሄድ
~ ሱረቱል ካፍን መቅራት ዱአ ማብዛት ~ በረሱል (ሰ፣ዐ፣ወ) ላይ ሰለዋት ማውረድ።

  اللَّهُمَّ صَلِّ عَلَى مُحَمَّدٍ، وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ كَمَا صَلَّيْتَ عَلَى إِبْرَاهِيمَ وَعَلَى آلِ إِبْرَاهِيمَ، إِنَّكَ حَمِيدٌ مَجِيدٌ، اللَّهُمَّ بَارِكْ عَلَى مُحَمَّدٍ، وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ، كَمَا بَارَكْتَ عَلَى إِبْرَاهِيمَ، وَعَلَى آلِ إِبْرَاهِيمَ، إِنَّكَ حَمِيدٌ مَجِيد
      
الَّلهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى نَبَيِّنَا مُحَمَّد ٍﷺ 
http://t.me//@arebgendamesjid
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ
18 views07:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 20:36:21 አቂደቱል ዋሲጥያ
ሸይህ ዑመር አሊ
  ክፍል-17-
http://t.me//@arebgendamesjid
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ
ዘርፍ
105 views17:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 20:35:07   ሰይድ አቡበክር ወደ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ሄዱና እንዲህ አሏቸው
«ዑመርን ይቅርታ አድርግልኝ፣ ታረቀኝ ብለው እንቢ አለኝ ከዚያም
ዑመር ትንሽ ቆይተው ወደ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) መስጂድ ሲገቡ አቡበክር አጠገባቸው እንደተቀመጡ ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) በጣም ተቆጥተው ፊታቸው ቀልቶ አዩዋቸው።

   አቡበክርም ይህንኑ የረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ሁኔታ ሲመለከቱ
ያበርዷቸውና ያረጋጓቸው ጀመር፡፡ «ረሱል ሆይ! እባክዎን ይረጋጉ እኔ ነኝ ጥፋተኛ አሉ። ነብዩም (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ አሉ “ምን ሆነህ ነው ዑመር እንዴት ለአቡበክር ፊት ትነሳዋለህ?..»

   "ሰዎች ሆይ! ይህን ዲን ዤ ስመጣ ሰው ሁሉ ፊት ሲነሳኝ
የተቀበለኝ አቡበክር ነው፡፡ እውነተኛ ነህ ያለኝ አቡበክር ነው፡፡ ገንዘቡን፣ ነፍሱንና ቤተሰቡን አሳልፎ የሰጠኝ አቡበክር ነው፡፡ እባካችሁ ጓደኛዬን እንዳትነኩት፡፡" ከዚህ ጊዜ ጀምሮ አቡበክርን(ረ.ዐ) ቀና ብሎ ያያቸው ኣልነበረም፡፡

           የመዋደድ ውበት

  በነብዩ (ሰ.ዐ.ወ)ና በአቡበክር(ረ.ዐ) መካከል የነበረው መዋደድ መለኪያ አልነበረውም። አንድ ቀን በነብዩና (ሰ.ዐ.ወ) በእሜቴ ዓኢሻ መካከል የፍቅር ጭቅጭቅ ይጀመራል፡፡ ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ አሉ «በመካከላችን ማን እንዲፈርድ ትፈልጊያለሽ፡፡ አቡ ኡበይዳ ይፍረድ?›› ዓኢሻም “አቡኡበይዳ መልካም ሰው ቢሆንም ከመጣ እርሶን ነው የሚደግፈው” ይላሉ ‹‹እሺ አባትሽ ይሁን?› እሜቴ ዓኢሻ ይስማማሉ፡፡

  ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) አስ-ሲዲቅን አስጠሯቸው። አቡበክር እንደመጡ እሜቴ እንዲህ ይላሉ «አንቱ የአላህ መልዕክተኛ እውነቱን ብቻ
ይንገሩት›› አቡበክርም ተቆጥተው ‹‹እርሳቸው ያለእውነት መች ይናገራሉ” ብለው ዓኢሻን ሊመቷት ተጠጉ፡፡ ረሱልም (ስ.ዐ.ወ)
በመሃላቸው ይገቡና ‹‹አቡበክር ይህን እንድታደርግ አላስጠራንህም፡፡ በቃ ተወው›› ይሏቸዋል፡፡

  አቡበክር ከወጡ በኋላ ለእሜት ዓኢሻ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ
ይሏቸዋል «በእርሱና በአንቺ መካከል እንዴት ገላጋይ እንደሆነኩ አየሽ አይደል» አቡበክር(ረ.ዐ) ቆየት ብለው ተመልሰው ሲገቡ ሁለቱም ሲሳሳቁ አገኙዋቸውና ‹‹ስትፋለሙ እንደጠራችሁኝ በተስማማችሁ ጊዜም አሳትፉኝ» በማለት ቀለዷቸው፡፡ ነብዩም (ሰ.ዐ.ወ) «አቡበክር ና ተሳተፍ› አሏቸው፡፡

  ነብዩን (ሰ.ዐ.ወ) መውደድ ከአላህ (ሱ.ወ) የሚገኝ በረከትና ጸጋ
ነው፡፡ አላህ (ሱ.ወ) ባሪያውን ሲወድ ይህን በረከትና ጸጋ ያጎናጽፈዋል፡፡ ነብዩን (ሰ.ዐ.ወ) ወደድክ ማለት የአላህን (ሱ.ወ) ሪዝቅና ችሮታ አገኘህ ማለት ነው፡፡ ነብዩን (ሰ.ዐ.ወ) ወዳጆች ከሆኑ ሙስሊሞች ጎን መሰለፍም ይጠበቅብናል፡፡

ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) በሌሊት ጉዞ ባደረጉበትና ወደሰማይ በመጠቁበት ወቅት የአፍታ ማረፊያ የነበራቸው ቁዱስን ከጥቃት ካልተከላከልን
እንዴት ነብዩን (ሰ.ዐ.ወ) እንወዳለን እንላለን፡፡ ታላቁ አቡበክር ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ከእንቅልፋቸው እንዳይነቁ ብለው እባብን የሚያክል ነገር
ሲነድፋቸው ድምጻቸውን ዋጥ ማድረጋቸዉን አይተናል፡፡ እኛ ግን የተቀደሰ የመሰሊም ግዛቶች በጠላት እጅ ሲቆሽሹ ዐይተን እንዳላየ
መስለን እናንቀላፋልን፡፡

  አንድ ቀን አቡበክር(ረ.ዐ) ለረቢዓ ቢን ካዕብ ትንሽ የሚያስከፋ ንግግር ይናገሩትና በመካከላቸው አለመግባባት ይፈጠራል፡፡ አቡበክርም(ረ.ዐ) በሁኔታው ያዝኑና «ረቢዓ ግድ የለም የተናገርኩህን መልሰህ ተናገረኝ” ይሉታል፡፡ ‹‹ረቢዓም መልስማ አልሰጦትም» ይላል፡፡ አቡበክርም «ረቢዓ በዚህ ንግግሬ አላህ ፊት እንድከሰስ ትፈልጋለህ?›› ይሉታል፡፡ ሳይናገር ዝም ይላቸዋል፡፡ አቡበክርም ቆጣ ብለው «ከዚህ ቃሌ ጋር አላህ ፊት እንድቀርብ ትወዳለህ ማለት ነው ወላሂ ለረሱል ሄጄ እነግራቸዋለሁ» ይላሉ፡፡

  የረቢዓ(ረ.ዐ) ወገኖችም ተገርመው «ራሱ የሚያስከፋ ንግግር ተናግሮህ ሲያበቃ እንደገና ለረሱል(ሰ.ዐ.ወ) እናገራለሁ ይላል እንዴ?›› ይላሉ። ሪቢዓም «ለመሆኑ የሰውየውን ማንነት አውቃችኋል? ዝም በሉ አስ-ሲዲቅ እኮ ነው! አሁን ለኔ ወግናችሁ እንዲህ ስትናገሩ እንዳይሰማንና እንዳይቆጣን ደግሞ! ከተቆጣ ለረሱል ሄዶ ይናገራላ ረሱልም እርሱን በማስቆጣታችን ይቆጡናል እርሳቸው ከተቆጡ ደግሞ ለእርሳቸው እና ለአቡበክር ቁጣ ሲል አላህም ስለሚቆጣ ረቢዓን ታስጠፋላችሁ፡፡ አሁን ዝም በሉ፡፡››ይላቸዋል ረቢዓ(ረ.ዐ) በስጋት ከአስ-ሲዲቅ(ረ.ዐ) ኋላ እየተከተለ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ዘንድ ሲደርሱ ነብዩ(ሰ.ዐ.ወ) ፈገግ ብለው "አል ሲዲቅና አንተ ምን ሆናችሁ?" ይላሉ አንድ የሚያስከፋኝን ቃል ተናገሩኝና እርሱን መልሰህ ተናገረኝ ሲሉኝ እኔ ደግሞ አይሆንም አልኳቸው›› አለ ረቢዓ፡፡ ነብዩም (ሰ.ዐ.ወ) «ረቢዓ አዎን ልክ ነህ፡፡ ከአቡበክር ጋር መመላለስ የለብህም ይልቁንም አቡበክር ሆይ! አላህ ይማርህ» ብለው» አሉት፡፡

              በስንብቱ ዋዜማ

   ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ስልሣ ሶስተኛ ዓመታቸው ላይ ደርሰዋል፡፡
ሠውነታቸው ላይ የድካም ሁኔታ ይተይባቸው ጀምሯል። አንዲት ሴት ወደ ርሳቸው ዘንድ መጥታ የሆነ ነገር እንዲሰጥዋት ጠይቃቸዋለች፡፡ ከዓመት በኋላ እንድትጠይቃቸው ይነግሯታል፡፡ እርሷም «እኔ ስመለስ ባላገኞትስ?›› ትላለች፡፡ ከመድከማቸው የተነሳ እስከ ቀጣዩ ዓመት ሊቆዩ እንደማይችሉ ገምታለች። «እኔን ካላገኘሽኝ አቡበክር ጋር ሄደሽ ትጠይቂዋለሽ ይሏታል። ይህ የመልዕክተኛው (ሰ.ዐ.ወ) አባባል ከርሳቸው በኋላ አቡበክር እንደሚተካቸው (ሊተኳቸው እንደሚገባ) አመላካች ነው፡፡

  ከዚህ ክስተት በኋላ ነበር ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) የመሰናበቻውን ሐጅ
ያደረጉትና ተከታዩ የቁርዓን አንቀጽ የወረደው

الْيَوْمَ أَكْمَلْتُ لَكُمْ دِينَكُمْ وَأَتْمَمْتُ عَلَيْكُمْ نِعْمَتِي وَرَضِيتُ لَكُمُ الْإِسْلَامَ دِينًا ۚ

"ዛሬ ሃይማኖታችሁን ለናንተ ሞላሁላችሁ፡፡ ጸጋዬንም በናንተ ላይ ፈጸምኩ፡፡ ለእናንተም ኢስላምን ከሃይማኖት በኩል ወደድኩ፡፡"  (ሱረቱል ማኢዳህ- 3)

  ይህ አንቀጽ ሲወርድ ሶሃቦች ሁሉ በደስታ ሲስቁ አስ-ሲዲቅ ብቻ በአንቀጹ ስለ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) መሰናበት የሚጠቁም ነገር እንዳለ ስለገባቸው ስቅስቅ ብለው አለቀሱ፡፡

  በነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ላይ ሕመም ይጠናባቸው ጀመር፡፡ ዓኢሻ ቤት ሆነው ታስታምማቸው ዘንድ እንዲፈቅዱላቸው ሚስቶቻቸውን ሁሉ
አስፈቀዱ፡፡ ፈቀዱላቸው፡፡ የመጨረሻዎቹ ሰዓታት ሲደርሱ ሶሃቦች ሁሉ በነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) መስጂድ ተሰባስበው ከፍ ባለ ድምፅ ያዝመትሙ ጀመር። ረሱል (ስ.ዐ.ወ) ድምጻቸውን ሰምተው ምን እንደሆኑ ሲጠይቁ በርሳቸውስጋት ገብቷቸው እንደሆነ ተነገራቸው!! ረሱልም (ሰ.ዐ.ወ) "ያሉበት ተሽክማችሁ ውሰዱኝ» አሉ፡፡

  እንደደረሱም ሶሃቦችን እንዲህ አሏቸው «እናንተ ሰዎች ሆይ! የኔ ሁኔታ አስፈርቷችኋልን?» ሶሃቦችም "አዎን አንቱ የአላህ መል
ዕክተኛ» በማለት መለሱላቸው እርሳቸውም እንሚከተለው አሏቸው... «እናንተ ሰዎች ሆይ! የእኔና የእናንተ የቀጠሮ ቦታ ዱኒያ
አይደለችም፡፡ ቀጠሮዋችን ሐውድ ዘንድ ነው፡፡ ከዚሁ ሆኜ እያየሁት ይመስለኛል...

----------ኢንሻአላህ ይቀጥላል-----
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ

http://t.me//@arebgendamesjid
1.4K views17:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 20:34:55 የአቡበክር አስ-ሲዲቅ (ረድየሏሁ ዐንሁ) ታሪክ

                     ክፍል አሥር

  ሰይድ አቡበክር ወደ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ሄዱና እንዲህ አሏቸው
«ዑመርን ይቅርታ አድርግልኝ፣ ታረቀኝ ብለው እንቢ አለኝ ከዚያም
ዑመር ትንሽ ቆይተው ወደ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) መስጂድ ሲገቡ አቡበክር አጠገባቸው እንደተቀመጡ ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) በጣም ተቆጥተው ፊታቸው ቀልቶ አዩዋቸው።

   አቡበክርም ይህንኑ የረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ሁኔታ ሲመለከቱ
ያበርዷቸውና ያረጋጓቸው ጀመር፡፡ «ረሱል ሆይ! እባክዎን ይረጋጉ እኔ ነኝ ጥፋተኛ አሉ። ነብዩም (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ አሉ “ምን ሆነህ ነው ዑመር እንዴት ለአቡበክር ፊት ትነሳዋለህ?..»

   "ሰዎች ሆይ! ይህን ዲን ዤ ስመጣ ሰው ሁሉ ፊት ሲነሳኝ
የተቀበለኝ አቡበክር ነው፡፡ እውነተኛ ነህ ያለኝ አቡበክር ነው፡፡ ገንዘቡን፣ ነፍሱንና ቤተሰቡን አሳልፎ የሰጠኝ አቡበክር ነው፡፡ እባካችሁ ጓደኛዬን እንዳትነኩት፡፡" ከዚህ ጊዜ ጀምሮ አቡበክርን(ረ.ዐ) ቀና ብሎ ያያቸው ኣልነበረም፡፡

           የመዋደድ ውበት

  በነብዩ (ሰ.ዐ.ወ)ና በአቡበክር(ረ.ዐ) መካከል የነበረው መዋደድ መለኪያ አልነበረውም። አንድ ቀን በነብዩና (ሰ.ዐ.ወ) በእሜቴ ዓኢሻ መካከል የፍቅር ጭቅጭቅ ይጀመራል፡፡ ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ አሉ «በመካከላችን ማን እንዲፈርድ ትፈልጊያለሽ፡፡ አቡ ኡበይዳ ይፍረድ?›› ዓኢሻም “አቡኡበይዳ መልካም ሰው ቢሆንም ከመጣ እርሶን ነው የሚደግፈው” ይላሉ ‹‹እሺ አባትሽ ይሁን?› እሜቴ ዓኢሻ ይስማማሉ፡፡

  ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) አስ-ሲዲቅን አስጠሯቸው። አቡበክር እንደመጡ እሜቴ እንዲህ ይላሉ «አንቱ የአላህ መልዕክተኛ እውነቱን ብቻ
ይንገሩት›› አቡበክርም ተቆጥተው ‹‹እርሳቸው ያለእውነት መች ይናገራሉ” ብለው ዓኢሻን ሊመቷት ተጠጉ፡፡ ረሱልም (ስ.ዐ.ወ)
በመሃላቸው ይገቡና ‹‹አቡበክር ይህን እንድታደርግ አላስጠራንህም፡፡ በቃ ተወው›› ይሏቸዋል፡፡

  አቡበክር ከወጡ በኋላ ለእሜት ዓኢሻ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ
ይሏቸዋል «በእርሱና በአንቺ መካከል እንዴት ገላጋይ እንደሆነኩ አየሽ አይደል» አቡበክር(ረ.ዐ) ቆየት ብለው ተመልሰው ሲገቡ ሁለቱም ሲሳሳቁ አገኙዋቸውና ‹‹ስትፋለሙ እንደጠራችሁኝ በተስማማችሁ ጊዜም አሳትፉኝ» በማለት ቀለዷቸው፡፡ ነብዩም (ሰ.ዐ.ወ) «አቡበክር ና ተሳተፍ› አሏቸው፡፡

  ነብዩን (ሰ.ዐ.ወ) መውደድ ከአላህ (ሱ.ወ) የሚገኝ በረከትና ጸጋ
ነው፡፡ አላህ (ሱ.ወ) ባሪያውን ሲወድ ይህን በረከትና ጸጋ ያጎናጽፈዋል፡፡ ነብዩን (ሰ.ዐ.ወ) ወደድክ ማለት የአላህን (ሱ.ወ) ሪዝቅና ችሮታ አገኘህ ማለት ነው፡፡ ነብዩን (ሰ.ዐ.ወ) ወዳጆች ከሆኑ ሙስሊሞች ጎን መሰለፍም ይጠበቅብናል፡፡

ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) በሌሊት ጉዞ ባደረጉበትና ወደሰማይ በመጠቁበት ወቅት የአፍታ ማረፊያ የነበራቸው ቁዱስን ከጥቃት ካልተከላከልን
እንዴት ነብዩን (ሰ.ዐ.ወ) እንወዳለን እንላለን፡፡ ታላቁ አቡበክር ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ከእንቅልፋቸው እንዳይነቁ ብለው እባብን የሚያክል ነገር
ሲነድፋቸው ድምጻቸውን ዋጥ ማድረጋቸዉን አይተናል፡፡ እኛ ግን የተቀደሰ የመሰሊም ግዛቶች በጠላት እጅ ሲቆሽሹ ዐይተን እንዳላየ
መስለን እናንቀላፋልን፡፡

  አንድ ቀን አቡበክር(ረ.ዐ) ለረቢዓ ቢን ካዕብ ትንሽ የሚያስከፋ ንግግር ይናገሩትና በመካከላቸው አለመግባባት ይፈጠራል፡፡ አቡበክርም(ረ.ዐ) በሁኔታው ያዝኑና «ረቢዓ ግድ የለም የተናገርኩህን መልሰህ ተናገረኝ” ይሉታል፡፡ ‹‹ረቢዓም መልስማ አልሰጦትም» ይላል፡፡ አቡበክርም «ረቢዓ በዚህ ንግግሬ አላህ ፊት እንድከሰስ ትፈልጋለህ?›› ይሉታል፡፡ ሳይናገር ዝም ይላቸዋል፡፡ አቡበክርም ቆጣ ብለው «ከዚህ ቃሌ ጋር አላህ ፊት እንድቀርብ ትወዳለህ ማለት ነው ወላሂ ለረሱል ሄጄ እነግራቸዋለሁ» ይላሉ፡፡

  የረቢዓ(ረ.ዐ) ወገኖችም ተገርመው «ራሱ የሚያስከፋ ንግግር ተናግሮህ ሲያበቃ እንደገና ለረሱል(ሰ.ዐ.ወ) እናገራለሁ ይላል እንዴ?›› ይላሉ። ሪቢዓም «ለመሆኑ የሰውየውን ማንነት አውቃችኋል? ዝም በሉ አስ-ሲዲቅ እኮ ነው! አሁን ለኔ ወግናችሁ እንዲህ ስትናገሩ እንዳይሰማንና እንዳይቆጣን ደግሞ! ከተቆጣ ለረሱል ሄዶ ይናገራላ ረሱልም እርሱን በማስቆጣታችን ይቆጡናል እርሳቸው ከተቆጡ ደግሞ ለእርሳቸው እና ለአቡበክር ቁጣ ሲል አላህም ስለሚቆጣ ረቢዓን ታስጠፋላችሁ፡፡ አሁን ዝም በሉ፡፡››ይላቸዋል ረቢዓ(ረ.ዐ) በስጋት ከአስ-ሲዲቅ(ረ.ዐ) ኋላ እየተከተለ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ዘንድ ሲደርሱ ነብዩ(ሰ.ዐ.ወ) ፈገግ ብለው "አል ሲዲቅና አንተ ምን ሆናችሁ?" ይላሉ አንድ የሚያስከፋኝን ቃል ተናገሩኝና እርሱን መልሰህ ተናገረኝ ሲሉኝ እኔ ደግሞ አይሆንም አልኳቸው›› አለ ረቢዓ፡፡ ነብዩም (ሰ.ዐ.ወ) «ረቢዓ አዎን ልክ ነህ፡፡ ከአቡበክር ጋር መመላለስ የለብህም ይልቁንም አቡበክር ሆይ! አላህ ይማርህ» ብለው» አሉት፡፡

              በስንብቱ ዋዜማ

   ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ስልሣ ሶስተኛ ዓመታቸው ላይ ደርሰዋል፡፡
ሠውነታቸው ላይ የድካም ሁኔታ ይተይባቸው ጀምሯል። አንዲት ሴት ወደ ርሳቸው ዘንድ መጥታ የሆነ ነገር እንዲሰጥዋት ጠይቃቸዋለች፡፡ ከዓመት በኋላ እንድትጠይቃቸው ይነግሯታል፡፡ እርሷም «እኔ ስመለስ ባላገኞትስ?›› ትላለች፡፡ ከመድከማቸው የተነሳ እስከ ቀጣዩ ዓመት ሊቆዩ እንደማይችሉ ገምታለች። «እኔን ካላገኘሽኝ አቡበክር ጋር ሄደሽ ትጠይቂዋለሽ ይሏታል። ይህ የመልዕክተኛው (ሰ.ዐ.ወ) አባባል ከርሳቸው በኋላ አቡበክር እንደሚተካቸው (ሊተኳቸው እንደሚገባ) አመላካች ነው፡፡

  ከዚህ ክስተት በኋላ ነበር ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) የመሰናበቻውን ሐጅ
ያደረጉትና ተከታዩ የቁርዓን አንቀጽ የወረደው

الْيَوْمَ أَكْمَلْتُ لَكُمْ دِينَكُمْ وَأَتْمَمْتُ عَلَيْكُمْ نِعْمَتِي وَرَضِيتُ لَكُمُ الْإِسْلَامَ دِينًا ۚ

"ዛሬ ሃይማኖታችሁን ለናንተ ሞላሁላችሁ፡፡ ጸጋዬንም በናንተ ላይ ፈጸምኩ፡፡ ለእናንተም ኢስላምን ከሃይማኖት በኩል ወደድኩ፡፡"  (ሱረቱል ማኢዳህ- 3)

  ይህ አንቀጽ ሲወርድ ሶሃቦች ሁሉ በደስታ ሲስቁ አስ-ሲዲቅ ብቻ በአንቀጹ ስለ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) መሰናበት የሚጠቁም ነገር እንዳለ ስለገባቸው ስቅስቅ ብለው አለቀሱ፡፡

  በነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ላይ ሕመም ይጠናባቸው ጀመር፡፡ ዓኢሻ ቤት ሆነው ታስታምማቸው ዘንድ እንዲፈቅዱላቸው ሚስቶቻቸውን ሁሉ
አስፈቀዱ፡፡ ፈቀዱላቸው፡፡ የመጨረሻዎቹ ሰዓታት ሲደርሱ ሶሃቦች ሁሉ በነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) መስጂድ ተሰባስበው ከፍ ባለ ድምፅ ያዝመትሙ ጀመር። ረሱል (ስ.ዐ.ወ) ድምጻቸውን ሰምተው ምን እንደሆኑ ሲጠይቁ በርሳቸውስጋት ገብቷቸው እንደሆነ ተነገራቸው!! ረሱልም (ሰ.ዐ.ወ) "ያሉበት ተሽክማችሁ ውሰዱኝ» አሉ፡፡

  እንደደረሱም ሶሃቦችን እንዲህ አሏቸው «እናንተ ሰዎች ሆይ! የኔ ሁኔታ አስፈርቷችኋልን?» ሶሃቦችም "አዎን አንቱ የአላህ መል
ዕክተኛ» በማለት መለሱላቸው እርሳቸውም እንሚከተለው አሏቸው... «እናንተ ሰዎች ሆይ! የእኔና የእናንተ የቀጠሮ ቦታ ዱኒያ
አይደለችም፡፡ ቀጠሮዋችን ሐውድ ዘንድ ነው፡፡ ከዚሁ ሆኜ እያየሁት ይመስለኛል...
የአቡበክር አስ-ሲዲቅ (ረድየሏሁ ዐንሁ) ታሪክ

                     ክፍል አሥር
103 views17:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 19:56:01 አቂደቱል ዋሲጥያ
ሸይህ ዑመር አሊ
  ክፍል-16-
http://t.me//@arebgendamesjid
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ
ዘርፍ
176 views16:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 19:53:53 የአቡበክር አስ-ሲዲቅ (ረድየሏሁ ዐንሁ) ታሪክ

                     ክፍል ዘጠኝ
 
  «አንቱ የአላህ መልዕክተኛ እኛ በቀጥታ የመጣነው ፈጅር ለመስገድ ነው በዚህ ሰዓት እንዴት የታመመን ልንጠይቅ እንችላለን፡፡» በማለት ዕይድ ዑመር መለሱ፡፡ አቡበክርም(ረ.ዐ) «አንቱ የአላህ መልዕክተኛ እኔ ወደ መስጅድ ለመሄድ ከቤቴ ስወጣ ትላንት ወንድሜ አብዱራህማን ቢን ዐውፍ መታመሙን አስታወስኩ፡፡ የርሱ ቤትና የእኔ ቤት በመስጅዱ መካክል ይገኝ ነበር፡፡ ለሪጅር ሶላት መንቃቱን ስላወቅኩ  አንድ አፍታ ገብቼ ጠየቅሁትና ወደዚህ ለሶላት መጣሁ» አሏቸው፡፡

    ረሱል (ሰዐ,ወ) ቀጠል አደረጉና «ዛሬ ምሽት ከናንተ ውስጥ ሶደቃ የሰጠው ማነው?» ብለው ጠየቁ፡፡ ዑመርም “በዚህ ምሽት ሶደቃ የሰጠነው ማንም ደሃ የለም” ብለው መለሱ፡፡ «አንቱ፡ የአላህ መልዕክተኛ ቢን ዓውፍን ከጠየቅሁ በኋላ ወደ መስጂድ ስገባ ድሃ አገኘሁና በእጄ የተጋገረ ዳቦ ይዤ ስለነበር ለርሱ ሰጠሁት» በማለት አቡበክር ተናገሩ፡፡

   ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ አሉ “አንተ አቡበክር ዛሬ አንተን በጀነት
አብስሬሃለሁ ይህን ሁሉ ሥራ የሠራ ሰው ጀነት ሊበሰር ይገባዋል፡፡”
ዑመርም ደንገጥ አሉና “አቡበክር ሆይ! በምንም ነገር አንተን ቀድሜህ አላውቅም" አሏቸው።

                   ከባዱ ዘመቻ

   ሰይድ ዑመር(ረ.ዐ) እንዲህ ይላሉ፡- «በተቡክ ዘመቻ ጊዜ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ወደኛ መጡና ለዘመቻው ግልጋሎት ይውል ዘንድ እንድንወድቅ (እንድንመጸውት) ቅስቀሳ እደረጉልን። ይህ ሀሳብ በጣም ተስማማኝ፡፡ የተወሰነ ገንዘብ ስለነበረኝ ዛሬ እበበክርን በመብለጥ አለብኝ ብዬ ወሰንኩ፡፡ ወደ ቤቴ ሄድኩና ካለኝ ገንዘብ ውስጥ ግማሹን ይዤ ተመለስኩና ረሱል(ሰ.ዐ.ወ) ፊት ዘረጋሁት፡፡ እሳቸውም «ለቤተሰቦችህ ምን ያህል
እስቀረህላቸው ብለው ጠየቁኝ። እኔም "ከገንዘቤ ግማሹን ትቼላቸዋለሁ::" አልኳቸው። አቡበክርም(ረ.ዐ) ምንም እንኳ ከዑመር ያነሰ ቢሆንም ቤታቸው ሄደው ገንዘባቸውን ሁሉ አንዲትም ሳያስቀሩ ጠራርገው በማምጣት ነብዩ(ሲ.ዐ.ወ) ፊት ዘረገፉት ነብዩም (ሰዐ,ወ) ለቤተሰቦችህ ምን ያህል አስቀረህላቸው አቡበክር? በማለት ጠየቋቸው:: አበበክርም «ለቤተሰቦቼ ከአላህና ከርሶ በስተቀር ምንም የተውኩላቸው ነገር የለም፡፡"  በማለት መልስ ሰጡ። እኔም እንዲህ አልኩኝ "አቡበክር ሆይ! ወላሂ
ከአሁን በኋላ ካንተ ገር ለመፎካከር አልሞክርም።"  ሃብት ንብረታቸውን በመሉ ለአላህ (ሱ.ወ) ዲን ሲሉ ለሶስት ጊዜያት ያህል የሰጡት ብቸኛ ጀግና አቡበክር አስ-ሲዲቅ ናቸው፡፡

   እስቲ ጥቂት ቆም ብለን ራሳችንን እንጠይቅ! ማነው እስቲ ከኛ
ውስጥ ለአላህ (ሱ.ወ) ብሎ የተቸገሩ ወገኖቹን ለመርዳት ገንዘቡን ሁሉ የሚሰጥ ሰዎች አሁንም ሞልተዋል፡፡ እኔ ራሴ በዐይኔ አንድ በጣም ደካማ ሰው የቦስኒያ ሙስሉሞችን ለመርዳት ራሱ የሚጠቀምበትን ዊልቸር ሲቸር ተመልክቻለሁ፡፡ አንዲት ሴትም ምንም ነገር ስላልነበራት ሙስሊሞችን ለመርዳት የራሷን ጌጣ ጌጦች ስትሰጥ አይቻለሁ፡፡ በዚህ ኡማ ውስጥ የአቡበክርን ዓርአያነት የሚከተል ሰው ሞልቶናል፡፡ ይህ ዓይነቱ ድንቅ ዓርአያነት ተጠናክሮ እንዲቀጥል እንመኛለን፡፡

  አቡበክር ገንዘባቸውን ሁሉ ለአላህ (ሱ.ወ) ሲሉ ሶስት ጊዜያት
ያህል መጽውተዋል ብለናል፡፡ እነርሱም፡-
-አንዲት ሚስኪን ሴት ከባርነት ነጻ ሲያወጡ፣
- ከነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ጋር ወደ መዲና ሲሰደዱና
- አሁን እንዳልነው በተቡክ ዘመቻ ወቅት ናቸው፡፡

          ለአላህህ (ሱ.ወ) የነበራቸው ፍራቻና ክብር

    ከዕለታት አንድ ቀን የአስ-ሲዲቅ አገልጋይ ለአቡበክር ምግብ
ያቀርብላቸዋል፡፡ አቡበክርም ትንሽ ቀመስ ያደርጉለታል፡፡ አንድ ምግብ ሲቀርብላቸው የምግቡ አመጣጥ ከየት እንደሆነ የመጠየቅ ልምድ ነበራቸው፡፡ በዚህም መሠረት አገልጋያቸውን የምግቡን ምንጭ ይጠይቁታል፡፡ ‹‹ሙስሊም ከመሆኔ በፊት ለስዎች እጠነቁል ነበር፡፡›› በወቅቱ አንድ የጠነቆልኩለት ሰው የነበረበትን ዕዳ ኣሁን ስለከፈለኝ በዚሁ ገንዘብ ነው ይህን ምግብ የገዛሁት ይላቸዋል፡፡

   አቡበክርም በጣም ተደናግጠው «አጥፍተኸኝ ነበር›› ይሉና
ጣታቸውን ወደ ጉሮሮዋቸው ሰድደው የገባውን ለማውጣት ከራሳቸው ጋር መታገል ይጀምራሉ፡፡ ይህን የተመለከቱ ሰዎች በላዩ ላይ በብዛት ውሃ ጠጥተው ካልሆነ ሊወጣሳቸው እንደማይችል ይነግሯቸዋል። ውሃ አምጣልኝ ብለው ያዛሉ፡፡ የመጣላቸውን ውሃ በደንብ ከጠጡ በኋላ እንዲያስታውካቸው በማድረግ የቀመሱትን ጥቂት ጉርሻ ነቅለው ያወጡታል፡፡ ሁኔታውን የሚመለከቱት ሰዎች ‹‹አላህ ይዘንሎት! ትንሽ ነበርች›› ይሏቸዋል፡፡ እርሳቸውም «ወላሂ  ነፍስህ ካልወጣች በስተቀር አትወጣም ነበር ብባል እንኳ ጎልገዬ አወጣት ነበር” ይላሉ፡፡

              አስገራሚ ትህትናቸው

በመዲና ከተማ ውስጥ ባጋደለ ደሳሳ ጎጆ ውስጥ የምትኖር
አንዲት ድሃ አሮጊት ሴትዮ ነበረች፡፡ አቡበክር አስ-ሲዲቅ(ረ.ዐ) በየሳምንቱ ወደ ቤቷ እየሄዱ ቤቱን አጽድተውላት ይመለሱ ነበር፡፡

     ከዕለታት አንድ ቀን ሰይድ ዑመር (ረ.ዐ) የባልቴቷን ደካማነት ይሰሙና ሊጠይቁዋት ቢሄዱ ቤቷ ጥርት ባለ ንጽህና መያዙን ያዩና እንዲህ አድርጎ የሚያጸዳላት ማን እንደሆነ ይጠይቋቸዋል፡፡ ሴትየዋም ማንነቱን የማያውቁት አንድ ሰው በየሳምንቱ እየመጣ እንደሚያጸዳላቸው ይነግሯቸዋል፡፡

    ሰይድ ዑመርም የዚህን ደግ ሰው ማንነት ማወቅ ይኖርብኛል
በማለት በሳምንቱ ተደብቀው መጠባበቅ ይጀምራሉ፡፡ ዑመር(ረ.ዐ) ሁኔታውን እንዲህ ይተርካሉ፡፡ «አቡበክር(ረ.ዐ) መጥተው ቤቱን አንኳኩ፡፡ በሩ እንደተከፈተላቸው አሮጊቷን ወደ ውጪ ደግፈው አወጧቸውና ቤቱን ካጸዱ በኋላ ሴትየዋን ወደ ነበሩበት መልስው ወዲያው በመውጣት ወደ መጡበት አቅጣጫ ይሄዳሉ፡፡››

  ኧረ ለመሆኑ ! እስኪ ማነው ከእኛ ውስጥ ሃቃቸው የማያልቀውን
እናት አባቱን እንኳ እንዲህ አድርጎ የሚያገለግለውና የሚያግዘው?
ራሳችንን መጠየቅ አለብን፡፡

       ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ስስል ሲዲቅ የነበራቸው ውዴታ

  አንድ ቀን ሶሀባዎች በተሰበሰቡበት ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ወደ መስጂድ ገቡና ‹‹አቡበክርስ የታለ?›› ሲሉ ጠየቁ፡፡ አቡበክር ቆም አሉ "ና አጠገቤ ሁን” አሏቸው፡፡ “ዑመርስ የት አለ” ሲሉ አስከተሉ፡፡ እርሳቸውም ቆም ሲሉ ‹‹ና አጠገቤ ሁን›› አሉና የሁለቱንም ሶሀቦች እጅ ይዘው ከፍ
በማድረግ እንዲህ አሉ “በዕለተ ትንሳኤ ልክ እንደዚህ ነው
የምንቀሰቀሰው፡፡”

   ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ከሰው ሁሉ ማንን ይበልጥ እንደሚወዱ ሲጠየቁ ‹‹ዓኢሻን› አሉ፡፡ ከወንዶችስ ሲባሉ ‹‹አባቷን አቡበክርን›› አሉና እንዲህአሉ «አቡበክር ሆይ! በዋሻው ውስጥ ጓደኛዬ እንደነበርከው ሁሉ የጀነትን መጠጥ (ሐውድ) ሳከፋፍልም የቅርብ ጓደኛዬ ትሆናለህ፡፡»

  ከዕለታት አንድ ቀን ሰይድ ዑመር በአንዲት ንግግር አቡበክርን ያኮርፏቸውና ጥለዋቸው ይሄዳሉ፡፡ አቡበክርም(ረ.ዐ) ከኋላ እየተከተሉ "ዑመር እባክህ አትቆጣ ይቅር በለኝ” ቢሏቸው ዑመር(ረ.ዐ) ዝም ብለዋቸው ሄዱ፡፡

  ሰይድ አቡበክር(ረ.ዐ) ወደ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ሄዱና እንዲህ አሏቸው «ዑመርን ይቅርታ አድርግልኝ፣ ታረቀኝ ብለው እንቢ አለኝ ከዚያም ዑመር ትንሽ ቆይተው...
http://t.me//@arebgendamesjid
--------ኢንሻአላህ ይቀጥላል.......

የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ
2.2K views16:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 21:04:53 አቂደቱል ዋሲጥያ
ሸይህ ዑመር አሊ
  ክፍል-15-
http://t.me//@arebgendamesjid
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ
ዘርፍ
131 views18:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 21:03:36 የአቡበክር አስ-ሲዲቅ (ረድየሏሁ ዐንሁ) ታሪክ

                ክፍል ስምንት

   ከርሱ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የሌለ በሆነው አላህ
ምዬ መናገር እችላለሁ፡፡ በዚህ ዓለም ውስጥ ከነቢያት በስተቀር እንደ አቡበክር ያለ ታላቅ ሰው እስከ አሁን ድረስ አልተፈጠረም።

    ብዙ ሙስሊም ወጣቶች ታላላቅ አድርገን የምንቆጥራቸው
ምን አይነት ሰዎችን ነው? እስኪ የአቡበክርን ታሪክ ለመመርመር ጥረት እናድርግ፡፡ ከተራራ የገዘፈ ታላቅነት ጎልቶ ይታየናል። የአስ-ሲዲቅን ሕይወት እንመርምር፡፡

           እስክጠግብ ድረስ እርሳቸው ጠጡ!

      አቡበክር አስ-ሲዲቅ ከነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ጋር ረዘም ላለ ጊዜ በዋሻው ተሸሽገው ቆዩ፡፡ ሁለቱንም ረሃብና ጥማት ያሰቃያቸው ጀመር፡፡ አንድ እረኛ ከዋሻው ወዲያ ማዶ ሲያልፍ ተመለከቱ፡፡ ጥቂት ወተት ካለው ይሰጣቸው ዘንድ ለመጠየቅ አቡበክር ወጣ አሉ፡፡ መጠነኛ ወተት ከእረኛው አገኙ፡፡ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲጠጡ አደረጉ፡፡ አቡበክር ይህን ሁኔታ በተመስጦ ሲተርኩ እንዲህ ይላሉ፦

  “ወተቱን እኔ እስክረካና እስክጠግብ ድረስ እርሳቸው ጠጡ፡፡” እንዴት ያለው ፍቅር ነው! የነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) እርካታ የርሳቸው እርካታ ሆነ፡፡ የነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) መጥገብ ለርሳቸውም ጥጋብ ሆነ፡፡ እንዲህ ያለ ፍቅር ታይቶም አይታወቅም! ከዚህ በኋላ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ)ና ወዳጃቸው ጉዙዋቸውን ወደ መዲና አቀኑ፡፡ አቡበክር በአካባቢው ታዋቂ ነጋዴ ስለነበሩ በየመንገዱ ያገኙዋቸው ሰዎች ሰላምታ
ያቀርቡላቸዋል።

    ስለ ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ማንነትም ይጠይቋቸው ነበር። አንዱን ሰላም ሲሉት ይህ ሰው ማነው አቡበክር በማለት ይጠይቃቸዋል ይህ መንገድ የሚመራኝ ሰው ነው በማለት ይመልሳሉ። ጠያቂው ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ለአቡበክር መንገድ የሚመሩት ሰው እንደሆነ እንዲገምት አድርገዋል። በእርግጥ አቡበክርን የሐቅ የእውነትና የጀነት መንገድ ይመሯቸው የነበሩት ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ናቸው። ዑመር ቢን አል-ኸጣብ የአቡበክር መዓዛ እንደሚስክ ሽቶ ያውዳል ይሉ ነበር፡፡

                     እኔ ተራ ሰው ነኝ
           እርሶ ግን የዚህ ዲን ዓርማ ነዎት!

አቡበክር ከረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ጋር ወደ መዲና አብረው በመጓዝ ላይ
እያሉ አንዴ ወደፊት አንዴ ደግሞ ወደኋላ ቆይተው ደግሞ ከግራና
ከቀኝ እየሆኑ ያጅቧቸዋል፡፡ በዚህ ጊዜ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) “ምን ሆነህ ነውአቡበክር” ይሏቸዋል። አቡበክርም “መጠበቅ እንዳለብኝ ሳስታውስ ከፊት እሆናለሁ። ከዛም የሚያሳድዱዎትን ሳስታውስ ከኋላ እሆናለሁ ከዚያም በግራዎ በኩል አንድ ነገር እንዳይጎዳዎ እልና በግራዎ እሆናልሁ፡፡" በቀኝ በኩልም ምንም ነገር እንዳያገኝዎ እሰጋና በስተቀኝ እሆናሉ፡፡ ‹‹አቡበክር ይህን ያህል ትወደኛለህ እንዴ?›› ይላሉ፡፡ ‹‹እጀግ በጣም ነው እንጂ ረሱልም (ሰ.ዐ.ወ) ‹‹በእኔ ቦታ ሆነህ ለመሞት ትፈልጋለህ ማለት ነው?›› ብለው ይጠይቃሉ ‹‹አዎና እኔ ብሞት እኮ ተራ ሰው ነኝ፡፡ እርሶ ግን የማይገኙ የዚህ ዲን አርማ ነዎት፡፡››

            አምሳያ የሌለው ሥነ-ምግባር

   አቡበክር አስ-ሲዲቅ ከላይ በተጠቀሰው መልኩ እያደረጉ መዲና
እስኪገቡ ድረስ አብረዋቸው ተጓዙ፡፡ ወደ መዲና ሲቃረቡ የመዲና ሰዎች (አንሷሮች) እየጠበቋቸው ነበር፡፡ ረሱልን (ሰ.ዐ.ወ) በመልክ ለይተው አያውቋቸውም። አቡበክር ለጥበቃ ከፊት ከፊት ይጓዙ ስለ ነበር አንሷሮች ሁሉ እርሳቸው መስለዋቸው ነበርና የተጫነበትን ግመል ይዘውላቸው ወደፊት ይመሩ ጀመር፡፡ ይሄን ጊዜ አቡበክር ሁኔታው ይገባቸውና ኩታቸውን ያወልቁና ጥላ ይሆናቸው ዘንድ ረሱልን (ሰ.ዐ.ወ) ይከልሉበታል፡፡ አንሳሮችም ወዲያው ነገሩ ይገባቸውና የረሱልን (ሰ.ዐ.ወ) ግመል መሳብ ይጀምራሉ።

              የውመል ፉርቃን

       ጊዜው ሄዶ ሙስሊሞች መዲና ላይ መሠብሰብ ጀመሩ። ታላቁ የበድር ጦርነት ተከሰተ፡፡ የአስ-ሲዲቅ ልጅ ዐብዱረህማን በወቅቱ ገና አልሰለመም ነበር፡፡ በውጊያው ዕለት ሰይፉን ከአፎቱ መዘዘና "ማነውየሚገጥመኝ?›› ብሎ ፎከረ፡፡ አቡበክር(ረ.ዐ) ተነሱና ««የአላህ መልዕክተኛ ሆይ እኔ እገጥመዋለሁ›› አሉ፡፡ ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) "ተወው እኔ እበቃዋለሁ" ብለው ተነሱ፡፡ ዐብዱረህማን ቢን አቡበክር ከሰለሙ በኋላ ለአባታቸው እንዲህ አሏቸው “ያኔ ካንተ ጋር ላለመግጠም ብዬ እየተደበቅሁ ነበር፡፡
አቡበክርም(ረ.ዐ) ‹‹ወላሂ ያኔ ባገኝህ ኖሮ አልምርህም ነበር›› አሉት፡፡

    አቡበክር ሰውነታቸው ለስላሳና ክብደታቸው ቀላል ቢሆንም
የቀልባቸው ጥንካሬ ግን ድንቅ ነበር፡፡ የአላህ (ሱ.ወ) ውሳኔ እርሳቸውን የመሰሉ ሰዎች በዓርአያነት ይከተሏቸው ዘንድ ገርና ለስላሳ ሆነው ተፈጠሩ፡፡ ህይወታቸውና ገንዘባቸው የአላህ (ሱ.ወ) ዲን የበላይ ይሆንዘንድ የማያወላውሉ ሰዎች አስ-ሲዲቅን በዓርአያነት መከተል ይኖርባቸዋል፡፡ እርሳቸውን ሞዴል ማድርግ አለባቸው፡፡

    የበድርን ውጊያ አቡበክር ጀብድ በተሞላበት ሁኔታ ነው ያሳለፉት፡፡ በወቅቱ ሶሃባዎች ከከህዲያኖች ይከላከልላቸው ዘንድ ለነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ዙፋን ሠርተውላቸው ነበር፡፡ ይህን ሠርተው ካበቁ በኋላ ከረሱል (ስ.ዐ.ወ) ጎን ሆኖ የሚከላከል ሰው ይመርጡ ጀመር፡፡ በወቅቱ የነበረውን ሁኔታ ዓልይ ቢን አቡጣሊብ(ረ.ዐ) ሲተርኩ እንዲህ ይላሉ ‹‹ይህንኑ ኃላፊነት ለመውጣት ሁላችንም አፈግፍገን ነበር፡፡ አቡበክር ሰይፋቸውን መዘው መጡና ‹‹የረሱልን ዙፋን እኔ እየጠበቅኩ እከላከላለሁ አሉ፡፡ እስከመጨረሻው የውጊያ ሰዓት ድረስም ከረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ሳይለዩ በተከላካይነት ቆዩ፡፡››

   አቡበክር የነበራቸው ወኔ እጅግ ከፍተኛና እንግዳ ነበር፡፡ ለጀነት
በተለይ ደግሞ ለከፍተኛው የፊርደውስ ጀነት የነበራቸው ጉጉት
አስገራሚ ነው፡፡ ይህንን ክስተት እስኪ እናስተውል።

   አንድ ቀን ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ሶሃቦቻቸውን (የዕምነት ጓዶቻቸውን)
ሰብስበው ስለጀነት ሰዎች ሁኔታ ይነግሯቸው ነበር፡፡ ‹‹ጀነት ውስጥ የተለያዩ የማዕረግ በሮች አሉ፡፡ እንደየሥራው በየበሩ የሚጠራ ሰው አለ፡፡ የሰላት ሰው በሰላት በር፤ የጾመ ሰው ረያን በሚባል በር፤ ሙጃሂድ ሆነ የሞተ ሰው የጂሀድ በር በሚባለው በኩል፤ የሶደቃ ሰው የነበረ በሶደቃ በር፣ በሚባለው በኩል እንደየሥራው እየተጠራ ይገባል›› ብለው ነገሯቸው፡፡

የጀነት ጉጉታቸው ወደር ያልነበረው አቡበክር እንዲህ በማለት ጠየቁ... ‹‹አንቱ የአላህ መልዕክተኛ በሁሉም በር እየተጠሩ መግባት የሚቻልበት ሁኔታ አለን?›› ነብዩም (ሰ.ዐ.ወ) «እንዴታ አቡበክር አንተ ከእንዲህ ዓይነት ሰዎች እንድትሆን እመኛለሁ፡፡» አሏቸው።

                  ሁለገብ ማንነት

  በአንድ ወቅት ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ሙስሊሞችን የፈጅር ሶላት ካሰገዷቸው በኋላ ወደ እነርሱ ተቀጣጭተው ተቀመጡና እንደሚከተለው ጥያቂያዎችን አቅረቡ፡፡ «ከናንተ ውስጥ ማነው ለዛሬ ጾምን ነይቶ ያደረው፡፡ ሁሉም ዝም ሲሉ ሰይድ ዑመር(ረ.ዐ) «አንቱ የአላህ መልእክተኛ! እኔ ለመጾም ነይቼ አላደርኩም›› አቡበክር(ረ.ዐ) ቀበል አደረጉና «እኔ ጾምን ነይቼ ነው ያደርኩት» አሉ፡፡ ረሱልም (ሰ.ዐ.ወ) ጥያቄዎችን እያከታተሉጠየቁ «ከእናንተ ውስጥ ታማሚን የጠየቀ ማነው?» «አንቱ የአላህ መልዕክተኛ እኛ በቀጥታ የመጣነው ፈጅር ለመስገድ ነው በዚህ ሰዓት እንዴት የታመመን ልንጠይቅ እንችላለን፡፡» በማለት ሰይድ ዑመር....
http://t.me//@arebgendamesjid
1.6K views18:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 21:30:25 አቂደቱል ዋሲጥያ
ሸይህ ዑመር አሊ
  ክፍል-14-
http://t.me//@arebgendamesjid
የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ
ዘርፍ
193 views18:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 21:22:24 የአቡበክር አስ-ሲዲቅ (ረድየሏሁ ዐንሁ) ታሪክ


                    ክፍል ሰባት

      ከዚያም አቡበክር(ረ.ዐ) ወደ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ዘንድ ሄዱና ይህንኑ ነገሯቸው፡፡ ነብዩም (ሰዐ.ወ) "ጊዜው ሊሆን የሚችለው ከሶስት እስከ ዘጠኝ ዐመት ነው፡፡” በማለት ነገራቸው፡፡ አቡበክርም ወደ ኡመያ ዘንድ ተመለሱ፡፡ ኡመያም እንዲህ አለ “ምነው ተጸጸትክ እንዴ?” አቡበክርም “የለም እኔ የመጣሁት ተጸጽቼ ሳይሆን የተናገርኩትን የጊዜ ገደብ ከፍ ለማድረግ ነው።” አሉት፡፡
ዓመታቶች እየተከታተሉ አለፉ፡፡ ልክ በዘጠነኛው ዓመት እንቅጩ
ላይ ሮሞች ፋርሶችን አሸነፉ፡፡ አቡበክርም ዉርርዳቸውን አሸነፉ፡፡
ከዉርርድ ያገኙትን ገንዘብ ሶደቃ እንዲያወጡት ረሱል (ሰ.ዐ.ወ)
ነገሯቸዉ፡፡

     ከዚህ ታሪክ ሁሉም ሙስሊም ሊማር የሚገባው ነገር አለ፡፡
በተለይ ሴትና ወንድ ወጣቶች ከዚህ መማር ያለባቸው ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ከማፈርና ወደ ኃላ ከማለት ይልቅ በሙሉ ልብ ሃይማኖታቸውን ማንጸባረቅ አለባቸው፡፡ እውነትን ከመግለጽ ማፈር የለባቸውም፡፡ መጥፎን ነገር በአግባቡ ከመቃወም ማፈግፈግ አይኖርባቸውም፡፡ አንዳንድ ወጣቶች የአቡበከርን (ረ.ዐ) ሙሉነት ተምሳሌት አድርገው በየኮሌጃቸው ቁርኣን ይዘዉ ከመግባት፤ ሒጃቦቻቸውን ዘውትር ከመልበስ መታቀብ የለባቸውም፡፡

              ስደት ወደ መዲና

     ጊዜው ሙስሊሞች ከመካ ወደ መዲና የሚሰደዱበት ወቅት ነው። አስ-ሲዲቅ ወደ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ዘንድ ሔዱና እንዲህ አሏቸው...“አንቱ የአላህ መልዕክተኛ! እንድሰደድ ይፍቀዱልኝ፡፡” ረሱልም (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ሲሉ መለሱ፡- “አቡበክር ሆይ! ትንሽ ታገስ፡፡ አላህ አብሮህ የሚሰደድ ጓደኛ ይሰጥሀል፡፡”

  አቡበክርም (ረ.ዐ) በስደት ወቅት የነብዩ ጓደኛ መሆንን አጥብቀዉ ተመኙ፡፡ ሁለት ለመጓጓዣ የሚሆኑ ፈረሶችን ገዙና የመሰደጃቸዉ ቀን እስኪደርስ እየተንከባከቧቸው ጠበቁ። አንድ ቀን ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ወደ አቡበከር ቤት መጡ፡፡ “አቡበክር! አላህ እንድሰደድ ፈቅዶልኛል አሏቸው።”

  አቡበክርም «የአላህ መልዕክተኛ እባክዎን ከርሶ ጋር ሆኜ ልሰደድ» አሏቸው፡፡ ነብዩም (ሰ.ዐ.ወ) ፍቃደኛ መሆናቸውን ነገሯቸዉ፡፡ ነብዩም (ሰ.ዐ.ወ) ፍቃደኝነታቸውን ከገለጹላቸው በኋላ አቡበክር (ረ.ዐ) የነበሩበትን ሁኔታ እሜቴ አዒሻ (ረ.ዐ) ሲያብራሩ እንዲህ ይላሉ...“አቡበክርም ያለቀሱትን ያህል ማንም ሰው ደስታ ሲያስለቅሰው አይቼ አላዉቅም፡፡ ጉዞው በጣም አስቸጋሪና የሞት ጉዞ ነዉ፡፡ እንደዚያም ሆኖ የሚጓዙት ከረሱል ጋር መሆኑን ስላወቁ በደስታ ሲቃ ስቅስቅ ብለው ሲያለቅሱ ዋሉ።” አቡበክር ለነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) የነበራቸው ፍቅር በእጅጉ የሚያስገርም ነበር፡፡

     ሰይድ አቡበክር (ረ.ዐ) ገንዘባቸዉን ሁሉ ለዚህ ጉዞ አዋሉት፡፡
ለቤተሰባቸው ከአላህና ከረሱሉ (ሰ.ዐ.ወ) በስተቀር የተዉላቸው አንዳችም ነገር አልነበረም፡፡ ይህ እንግዲህ ለዲን የሚከፈል ጣሪያ የነካ መስዋዕትነት ነበር፡፡ የአቡበክር መስዋትነት ይህን ያህል ነበር፡፡
     በእርግጥ እንዲህ ዓይነቱን መስዋትነት በአሁኑ ሰዓት በፍልስጤም ምድር እያየነዉ ነዉ፡፡ ወጣቶች በሰልፍ ለክብራቸው መስዋዕትነትን እየከፈሉ ይገኛሉ፡፡ ተስፋ መቁረጥ የሚባል ነገር አያዉቁም፡፡ ፍልስጤማዉያን መስዋትነትን የሚከፍሉት እጅግ ደስተኛ ሆነው ነዉ፡፡ እንዲያውም ሰማዕት የሌለበት ቤት ከተገኘ ቤተሠቦቹ በሁኔታዉ እስከማፈር ይደርሳሉ፡፡

    አስ-ሲዲቅና ነብዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ወደ ስደት ወጥተዋል፡፡
“ጋሩ ሠዉር” (የሠዉር ዋሻ) ደርሰዋል፡፡ እንደሚታቀዉ ስደቱ
የሚካሄደዉ በድብቅ ነዉ፡፡ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ወደ ዋሻዉ ለመግባት ሲፈልጉ አቡበክር አስ-ሲዲቅ በቅድሚያ የዋሻዉን ደህንነት ማጣራት ይኖርብኛል ብለዉ ቀድመዉ ገቡና ሁሉንም ነገር አጣሩ፡፡ ነብዩን (ሰ.ዐ.ወ) ሊጎዳ የሚችል ምንም ነገር እንደሌለ ካጣሩ በኃላ ተመልሰዉ ከመዉጣታቸው በፊት በላያቸዉ ላይ ጣል ያደረጉትን ኩታ እየቀደዱ የዋሻዉን ሽንቁሮች ሸፈኑበት፡፡ ከዚህ በኋላ ነዉ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ወደ ዋሻው ዘልቀዉ የገቡት፡፡ የአቡበክር ኩታ መቀደድን ሲመለከቱ ለምን እንዲህ እንዳደረጉ ጠየቋቸው፡፡ አስ-ሲዲቅም “እርሶን አንዳች ነገር እንዳይጎዳብኝ ፈርቼ ነው፡፡” አሏቸው፡፡ ትንሽ እንደቆዩ ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) በአቡበክር እግር ላይ ጋደም ብለው እንቅልፍ ይዟቸው ሄደ፡፡ አቡበክር ትንሽ ሽንቁር ተመለከቱና ረሱልን (ሰ.ዐ.ወ) የሚጎዳ ነገር ከዚያ ውስጥ እንዳይወጣ ፈርተው በእግርቸው መዳፍ ሸፈነት፡፡ ሽንቁሩ ውስጥ ጊንጥ ነበርና
እግራቸው ተነደፈ፡፡

    አቡበክር እግራቸውን የቱንም ያህል ቢያሳርራቸውም ረሱልን
(ሰ.ዐ.ወ) ላለመቀስቀስ ሲሉ ስቃያቸውን ዋጥ አድርገው ዝም አሉ:: ምንም ድድምፅ ላለማሠማት ጥረት አደረጉ እንባቸው ብቻ ፀጥ ብሎ ቁልቁል ይፈስ ጀምር፡፡ ይሄኔ ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ከእንቅልፋቸው ተነሱና የነገሩን ምንነት ጠየቁ፡፡ አቡበክር እንዲህ አሏቸው፡፡ እናትና አባቴ መስዋእት ይሁንልዎ! ጊንጥ ነደፈኝ፡፡ ረሱልም (ሰ.ዐ.ወ) ፈጠን ብለው ሲዳብሷዋቸው ወዲያው በአላህ (ሱ.ወ) ፍቃድ ተፈወሱ፡፡

             የሁለቱ ሁለተኛ

    ብዙዎቻችን የቻልነውን ያህል አቡበክርን (ረ.ዐ) እናወድሳለን፡፡
አላህ (ሱ.ወ) በሱረቱ ተውባ በአንቀጽ 40 ላይ ያወደሳቸውን ያህል ግን ማንም አላወደሳቸውም፡፡

  አቡበክር እንዴት ታድለዋል! አላህ “የሁለት ሁለተኛ” ሲል
አሞግሷቸዋል። አስ-ሲዲቅ በጣም የታደሉ ሰው ነዎት! ኃያሉ ጌታችን በዚያች ቀውጢ ጊዜ የረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ጓደኛ ሆነው በመጓዝዎ አወድሶዎታል፡፡ በጣም ታድለዋል! አላህ (ሱ.ወ) መረጋጋትን ለርሶ በማድረጉ እንዴት የታደሉ ነዎት!

  ሰይድ ዑመር ቢን አል-ኸጣብ(ረ.ዐ) ይህን አስመልክተው እንዲህ ይላሉ፡-

  "አቡበክር የተሰደዱባት ያቺ ሌሊት ምድር ከሞላችው በረከት ሁሉ
የበለጠች ናት።” እንዲህም ብለዋል፡- “ምነው ያኔ አቡበክር ደረት ላይ ከነበሩት ፀጉሮች አንዲቷን አድርጎኝ በነበረና አብሬያቸው በሆንኩ!”

   የተከበራችሁ ሙስሊሞች! ዓለምን በዲን ቀጥ ያደረጓት እነዚህን
ዕንቁዎች ለመገናኘት በእጅጉ አንጓጓምን? የአቡበክር አስ-ሲዲቅ(ረ.ዐ) ታላቅነት እኮ በዲን ብቻ የሚገታ አይደለም፡፡ ታላቅነታቸው ሰብአዊ የሆነ ታላቅነትም ጭምር ነው።
http://t.me//@arebgendamesjid
        ▻▻ኢንሻአላህ ይቀጥላል◅◅

የአረብገንዳ መስጂድ ወጣቶች የመረጃ ዘርፍ
188 views18:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ