Get Mystery Box with random crypto!

ሊቀ መዘምራን

የቴሌግራም ቻናል አርማ z_tewodros — ሊቀ መዘምራን
የቴሌግራም ቻናል አርማ z_tewodros — ሊቀ መዘምራን
የሰርጥ አድራሻ: @z_tewodros
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 58
የሰርጥ መግለጫ

✞ በየጊዜው አዳዲስ መንፈሳዊ
➢ ፅሁፎች
➢ መዝሙሮች
➢ ኦርቶዶክሳዊ መልእክቶች
➢ መንፈሳዊ ነገሮችን
ሁሉንም ለማግኘት ከፈለጉ ተቀላቀሉን ✞
ለአስተያየቶ @Channel_admin09 ይጠቀሙ
Youtube:
https://youtube.com/@shamo_guy
➢ ሁሉም እንዲያነበው SHARE ያርጉ ! እናመሰግናለን !

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2023-04-13 13:01:57 "እውነት ስለሆነ"

ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ

ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች
                •➢ ሼር // SHARE

@Z_TEWODROS
@Z_TEWODROS
@Z_TEWODROS

Comment @Channel_admin09
5.6K views◦•●Yaredo●•◦, 10:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 09:20:06 #የሰሙነ_ህማማት_ሐሙስ

#ጸሎተ_ሐሙስ
በቤተ ክርስቲያን የተለያዩ ስያሜዎች ያሏቸው በርካታ ድርጊቶች የተፈጸሙበት ዕለት ነውና ጸሎተ ሐሙስ ይባላል፡፡  የዓለም መድኃኒት ኢየሱስ ክርስቶስ ሥጋን የተዋሐደ አምላክ፣ መሆኑን ለመግለጥና ለአርአያነት ጠላቶቹ መጥተው እስኪይዙት ድረስ ሲጸልይ ያደረበት ነውና ጸሎተ ሐሙስ ተባለ፡፡ (ማቴ. 26፥36-46 ዮሐ.17)

#ሕፅበተ_ሐሙስ_ይባላል፡-
ጌታችን በዚህ ዕለት የደቀመዛሙርቱን እግር በፍጹም ትሕትና ዝቅ ብሎ አጥቧል፡፡ ይህም የሚያሳየው የዓለምን ሁሉ ኃጢአት ለማጠብ የመጣ መሆኑን ነው፡፡ ይህን ለማስታወስ ዛሬም ካህናት በተለይም ሊቃነ ጳጳሳት፣ የደብር አስተዳዳሪዎች፤ «በመካከላችን ተገኝተህ የእኛንና የሕዝብህን ኃጢአት እጠብ እኛም የአንተን አርአያ አንዘነጋም የሌላውን እግር እናጥባለን፤» ሲሉ በቤተ ክርስቲያን የተገኙትን ምእመናንን እግር በወይንና በወይራ ቅጠል ያጥባሉ፡፡

#የምስጢር_ቀን_ይባላል፡-
ከሰባቱ ምስጢራት አንዱ በዚህ ዕለት ተመሥርቷልና፡፡ ይኸውም «ይህ ስለ እናንተ በመስቀል ላይ የሚቆረሰው ሥጋዬ ነው፡፡ እንካችሁ ብሉ» ጽዋውንም አንስቶ አመሰገነ «ይህ ስለ እናንተ ነገ በመስቀል የሚፈስ ደሜ ነው ከእርሱም ጠጡ» በማለት፤ እኛ ከእርሱ ጋር፣ እርሱ ከእኛ ጋር አንድ የምንሆንበትን ምስጢር ከጠላት ዲያብሎስ ሰውሮ፣ ለደቀ መዛሙርቱ የገለጠበት ቀን በመሆኑ የተሰጠ ሥያሜ ነው፡፡ በዚህ ዕለት ክርስቲያን የሆነ ሁሉ በንስሐ ታጥቦ ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ለመቀበል ይዘጋጃል፡፡

#የሐዲስ_ኪዳን_ሐሙስ_ይባላል፡-
ምክንያቱም መሥዋዕተ ኦሪት ማለትም በእንስሳት ደም የሚቀርበው መሥዋዕት ማብቃቱን ገልጦ፣ ለድኅነተ ዓለም ራሱን የተወደደ መሥዋዕት አድርጎ ያቀረበበት ዕለት በመሆኑ ነው፡፡ «ይህ ጽዋ ስለ እናንተ በሚፈሰው በደሜ የሚሆን ሐዲስ ኪዳን ነው፡፡ ከእርሱ ጠጡ» በማለቱ ይታወቃል (ሉቃ. 22፥20) ኪዳን ማለት በሁለት ወገን መካከል የሚደረግ ውል፣ ስምምነት፣ መሐላ ማለት ነው፡፡ በዚህ መሠረት ጌታችን ለአዳምና ለልጆቹ ሁሉ ዘለዓለማዊውን ቃል ኪዳን በራሱ ደም የፈጸመበት ዕለት ስለሆነ የሐዲስ ኪዳስ ሐሙስ ተባለ፡፡

#የነጻነት_ሐሙስ_ይባላል፡-
ለኃጢአትና ለዲያብሎስ ባሪያ ሆኖ መኖር ማብቃቱ፣ የሰው ልጅ ያጣውን ክብር መልሶ ማግኘቱ የተረጋገጠበት ቀን ስለሆነ ነው፡፡ ጌታችን ስለ ሰው ልጅ ነጻነት ሲናገር «ከእንግዲህ ወዲህ ባሮች አልላችሁም ባርያ ጌታዉ የሚያደርገውን አያውቅምና ወዳጆች ግን ብያችኋለሁ» በማለት (ዮሐ. 15፥15)፤ ከባርነት የወጣንበት ልጆች የተባልንበትን ቀን የምናስብበት በመሆኑ ሊቃውንቱ የነጻነት ሐሙስ አሉት፡፡ እያንዳንዱ ክርስቲያንም ከኃጢአት ባርነት ርቆ፣ ከእግዚአብሔር ጋር የሚያወዳጀውን መልካም ሥራ በመሥራት ሕይወቱን መምራት ይኖርባታል፡፡ ባሮች አልላችሁም ተብለናልና፡፡

ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች
                •➢ ሼር // SHARE

@Z_TEWODROS
@Z_TEWODROS
@Z_TEWODROS

Comment @Channel_admin09
6.8K views◦•●Yaredo●•◦, 06:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 08:00:16
አስደሳች መልዕክት ከአያት አ.ማ

አያት ሪል ኢስቴት መጪዎቹ የትንሳኤና የኢድ አል ፍጥር በዓላትን ምክንያት በማድረግ ለሽያጭ ባቀረባቸው አፓርትመንቶች ላይ እስከ 30 በመቶ የሚደርስ ቅናሽ ማድረጉን ሲገልፅ በታላቅ ደስታ ነው!
የመሸጫ ዋጋ እና አከፋፈል
1) ለ107 ካሬ ቤት ከ896,319 ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ፣
2) የካሬ ዋጋ ብር 55,845፣
3) አፓርትመንቶቻችን ከብር 5,975,464 ጀምሮ መግዛት ይችላሉ።
እስከ 3 ዓመት በ7 ጊዜ ክፍያ ቀስ ብለው መክፈል ከፈለጉ፦
የመጀመሪያው ክፍያ__15%
2ኛው ክፍያ___16%
3ኛው ክፍያ___23%
4ኛው ክፍያ___23%
5ኛው ክፍያ___13%
6ኛው ክፍያ___5%
7ኛው ክፍያ___5%
ከ5 እስከ 30 አመት በሚደርስ የረጅም ጊዜ የ60/40 የዱቤ ክፍያ በ9.5% ዓመታዊ ወለድ ዘና ብለው የሚከፍሉበት አማራጭም አቅርበናል።
ሲ ኤም ሲ በሚገኘው በ140,000 ካሬ ሜትር ይዞታ ላይ ባረፈው ዘመናዊ መንደር በዉስጡ:-
   ሰፊ የመናፈሻ ቦታ
   አፀደ ህፃናት
   ዘመናዊ የመኪና ማቆሚያ
  የከርሰ ምድር ውሃ with high capacity pump
  የሰውና የዕቃ ዘመናዊ ሊፍቶች with automatic generator
  ዘመናዊ የቆሻሻ ማስወገጃ ያለው፣
  የተለያየ ግብይት የሚከወንበት 4,000 ሱቆችን የያዘ በአገራችን ግዙፉ Mall ያካተተ እንዲሁም
የስምንት ትርፋማ ኩባንያዎች ባለቤት የሚያደርግዎትን የአያት አክስዮን ማህበር አክስዮኖችን በመግዛት በየዓመቱ እስከ 50% ትርፍ ያግኙ

WhatsApp, Viber, Telegram & Linked In via +251911141372
Email:  tesema12015@gmail.com

https://t.me/Tese_Apartment
5.7K views◦•●Yaredo●•◦, 05:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-12 17:14:06 አልፋና ኦሜጋ

ሊቀ መዘምራን ኪነጥበብ ወ/ ቂርቆስ
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች
                •➢ ሼር // SHARE

@Z_TEWODROS
@Z_TEWODROS
@Z_TEWODROS

Comment @Channel_admin09
2.3K views◦•●Yaredo●•◦, 14:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-12 08:01:21 #የሰሙነ_ሕማማት_ረቡዕ

#ምክረ_አይሁድ_ይባላል
ምክንያቱም የአይሁድ ሊቃነ ካህናትና ጸሐፍት ጌታን እንዴት መያዝ እንደሚገባቸው ምክር ያጠናቀቁበት ቀን ነውና፡፡ በዚህ ምክራቸው ላይ በጣም ትልቅ ጭንቀት ነበር፡፡ ምክንያቱም ወቅቱ የፋሲካ በዓላቸውን የሚያከብሩበት ቀን የተቃረበ በመሆኑ ብዙው ሕዝብም በጌታችን ትምህርት የተማረኩ ተአምራቱንም የሚያደንቁ ስለ ነበር ሁከት እንዳይፈጠር ነው፡፡ በዚህ ጭንቀት ሳሉ ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ የአስቆሮቱ ይሁዳ በመካከላቸው በመገኘት የምክራቸው ተባባሪ ሆኖ ጭንቀታቸውን አስወግዶላቸዋል፡፡ (ማቴ. 26÷1-14፣ ማር. 14÷1-2፣ ሉቃ. 22÷1-6) የሐዲስ ኪዳን ካህናትና ምእመናን በዚሁ ዕለት በቤተ ክርስቲያን ተሰብስበው መላ ሰውነታቸውን ለእግዚአብሔር አስገዝተው የሞት ፍርዱን በማሰብና በማልቀስ ሐዋርያት ከጌታችን መያዝ በኋላ በኀዘን በፍርሐት እንደነበሩ እያሰቡ መጻሕፍትን በማንበብ በጾም በጸሎትና በስግደት ተወስነው ይቆዩና ከአሥራ ሁለት ሰዓት በኋላ ወደ ቤታቸው ይሄዳሉ፡፡

#የመልካም_መዓዛ_ቀንም_ይባላል
ምክንያቱም ጌታችን በዚህ ዕለት በቤተ ስምዖን ዘለምጽ ተቀምጦ ሳለ መላ ሕይወቷን ለዝሙት አስገዝታ ትኖር የነበረችው ማርያም እንተ እፍረት (ባለሽቱዋ ማርያም) "ከእንግዲህ ወዲህ በኃጢአት ተበላሽቶ ይኖር የነበረውን ሕይወቴን እንደዚህ መልካም ሽቱ የሚያጣፍጥ ኃጢአትን ይቅር የሚል አምላክ መጣ" ስትል ዋጋው እጅግ በጣም ውድ የሆነ ከሦስት መቶ ዲናር በላይ የሚያወጣ በአልባስጥሮስ ብልቃጥ የተሞላ ሽቱ ይዛ በመሔድ በጠጉሩ (በራሱ) ላይ በማርከፍከፍ ስለቀባችው ረቡዕ የመዓዛ ቀን ይባላል፡፡

#የእንባ_ቀንም_ይባላል
ማርያም እንተ እፍረት በጌታችን እግር ላይ ተደፍታ መላ ኃጢአቷን ይቅር እንዲላት በእንባዋ እግሩን አጥባዋለችና በጠጉሯም በእንባዋ ያጠበችውን እግሩን አብሳዋለችና። (ማቴ. 26÷6-13፣ ማር. 14÷9፣ ዮሐ. 12÷8) ኃጢአትን በማሰብ ማልቀስና ራስን የተወደደ መሥዋዕት አድርጎ ለእግዚአብሔር ማቅረብን ከምታስተምረን ማርያም እንተ እፍረት እንባን ለንስሐ ሕይወት ልንጠቀምበት ይገባል፡፡


ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች
                •➢ ሼር // SHARE

@Z_TEWODROS
@Z_TEWODROS
@Z_TEWODROS

Comment @Channel_admin09
5.0K views◦•●Yaredo●•◦, 05:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-12 07:15:04 ማስታወቂያ

አስደሳች   ዜና   ማየት ማመን ነው

መፍትሔ ስራይ ወአይነጥላ
   መሪጌታ ጥበቡ
የባህል ህክምና መስጫ ማእከል
የባህል መድሀኒት ከአባቶቻችን ባገኘነው ትምህርትና ጥበቡ እንዲሁም ከተለያዩ የአፍሪካ እና የአረብ ሀገራት በምናመጣቸው መድለኒቾች ፍቱን ህክምናወችን
እንሰጣለን ።
ለኪንታሮት በሽታ ታማሚው ባለበት ከቤቱ ወስዶ በመቀባት ሌላ ገላ ሳይነካ ሳያቆስል ስራ ሳያስቆም ዘላቂ ፈውስ ይሰጣል
በሌሊት ለሚሸና
ለነገረ በትን
ለደም ግፊት
ለስኳር ህመም መቀነሻ
ለሁሉም ቁርጥማት
ለዲስክ መንሸራተት ዘላቂ ፈውስ
ለፊት ማድያት
ለሳል በሽታ
ለግርማሞገስ ለህዝብ መስተፋቅር
ለማህጸን እንፌክሽን
ለአእምሮ ጭንቀት
ለወገብ ህመም
ለነርብ
ጋኔን አጋንንት የሰውጅ ለያዘው
የሚጥል በሽታ
ገንዘብ ለሚበተንበት
ስራ አልሳካለት ላለ
ገብያ ለሚገረግረው ለገብያ
ለመፍትሔ ስራይ
ለአስም (ለሳይነስ)

ለአይነጥላ ለሰው እጅ ለገርጋሪ

       እንዲሁም የተለያዩ የጤና ችግሮች መቶ ተመርምሮ የለብወትን ችግር አውቆ መታከም ይችላሉ

እኛ ጋር ለሚአገኙት ማንኛውም አይነት
አገልግሎቶቻችን  ውጤት እንዳዩ ክፍያ ይፈጽማሉ።
እነዚህን እና ሌሎች አገልግሎቶችን እንሰጣለን
    መድሀኒቱን ባሉበት መላላክ ይቻላል

ለበለጠ መረጃ አድራሻ ባህርዳር ቀበሌ 11ዲያስፖራ በኮብሉ መጨረሻ ንግድ ባንኩ ላይ።

    ቅርንጫፍ አዲስ አበባ ሳሪስ አደይ አበባ

እኒህን እና ሌሎች አገልልግሎቶችን ለማግኔት
                   ይደውሉ
0917040506
          0912718883

    ጓድኞቻችሁን ወደዚህ ጉርብ

ለምትቀላቅሉ ለምታስገቡ   አ  5 ሽብር ያሸልማል
                 

https://t.me/mergatah
4.6K views◦•●Yaredo●•◦, 04:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 20:00:31 ጌታዬ ሆነ ደም ግባት አልባ

➮ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ

በሕማማት ወቅት ስለሚጸለዩ እና ስለማይጸለዩ የጸሎት አይነቶች ከላይ ማንበብ ትችላላችሁ።

ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች
                •➢ ሼር // SHARE

@Z_TEWODROS
@Z_TEWODROS
@Z_TEWODROS

Comment @Channel_admin09
2.5K views◦•●Yaredo●•◦, 17:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 14:43:16 በሕማማት የሚጸለዩ ፀሎቶች ምን ምን ናቸው?
በሕማማት ወቅት የሚሰሙ የምንላቸው ከሌላ ቋንቋ የተወሰዱ ቃላት ትርጉም
የ41 ስግደት ምን እየተባለ ነው የሚሰገድ?

የሕማማት ጸሎት

በሕማማት የሚጸለየው በአብዛኛው ውዳሴ ማርያም እና መዝሙረ ዳዊት፤ የነቢያት ጸሎት ሲሆን የጌታን መከራ መስቀል የሚያነሱ መጻሕፍት ይጸለያሉ፡ ሕማማተ መስቀል፣ ድርሳነ ማሕየዊ የመሳሰሉ። መልክአ መልኮች፣ ድርሳናትና ገድላት የማይጸለዩት ዋናውን ጸሎት በጌታ ሕማማና መከራ መስቀል ለመስጠት ስለሆነ ነው። በአጠቃላይ በቤተክርስቲያን የሚነበበው ንባብ (ግብረ ሕማም) ዋናው የጸሎት ክፍል በመሆኑ ያንንም መሳተፍ ትልቁ ጸሎት ነው።

ጥብጠባ

በሰሙነ ሕማማት እለተ ዓርብ ስቅለቱ መታሰቢያ ነው፡ ምእመናኑ በሰሙነ ሕማማት የሰሩትን ይናዘዛሉ ካህናቱን በወይራ ቅጠል ትከሻቸውን እየጠበጠቡ ስግደት ያዟቸዋል፡፡ ጥብጠባው የተግሳፅ ምሳሌ ነው፡፡

ይህ በስቅለተ ቀን የሚፈጸም ስነ ስርዓት ሲሆን ጥብጣቤ ማለት ቸብ ማድረግ ማለት ነው፡፡ ይህም የጌታን ግርፋት ያሳያል።፡ሕዝብ ክርስቲያኑ በእለተ ስቅለት ሲሰግድ ሲጸልይ ሲያነብ ከዋለ በኋላ ሰርሆተ ሕዝብ ይሆናል። አርብ ከ 11 ሰአት በኋላ ስግደት እንደሌለ ግብረ ሕማሙ "አልቦ ስግደት "ይላል።

በሕማማት ወቅት የሚሰሙ የምንላቸው ከሌላ ቋንቋ የተወሰዱ ቃላት ትርጉም

በግብረ ሕማማት ውስጥ ወደ ግእዝም ሆነ በኋላ ወደ አማርኛ ሳይተረጎሙ የተቀመጡ የዕብራይስጥ፣ የቅብጥ እና የግሪክ ቃላት ይገኛሉ፡፡ የእነዚህ ቃላት ትርጉም የሚከተለው ነው፡፡

"ኪርያላይሶን"

ቃሉ የግሪክ ሲሆን አጠራሩ “ኪርዬ ኤሌይሶን” ነው፡፡ “ኪርያ” ማለት “እግዝእትነ” ማለት ሲሆን “ኪርዬ” ማለት ደግሞ “እግዚኦ”ማለት ነው፡፡ ሲጠራም “ኪርዬ ኤሌይሶን” መባል አለበት፡፡ ትርጉሙም “አቤቱ ማረን” ማለት ነው፡፡ “ኪርያላይሶን” የምንለው በተለምዶ ነው፡፡ ይኼውም ኪርዬ ከሚለው “ዬ”ኤላይሶን ከሚለው ደግሞ “ኤ” በመሳሳባቸው በአማርኛ "ያ"ን ፈጥረው ነው፡፡

"ናይናን"

የቅብጥ(ጥንታዊው የግብጻውያን ) ቃል ሲሆን ትርጉሙ “መሐረነ፣ ማረን” ማለት ነው፡፡

"እብኖዲ"

የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ “አምላክ” ማለት ነው፡፡ “እብኖዲ ናይናን” ሲልም “አምላክ ሆይ ማረን” ማለቱ ነው

"ታኦስ"

የግሪክ ቃል ሲሆን ትርጉሙ “ጌታ፣ አምላክማለት ነው፡፡ “ታኦስ ናይናንማለትም “ጌታ ሆይ ማረን” ማለት ነው፡፡

"ማስያስ"

የዕብራይስጥ ቃል ሲሆነ ትርጉሙ “መሲሕ” ማለት ነው፡፡ “ማስያስ ናይናን” ሲልም “መሲሕ ሆይ ማረን” ማለት ነው

"ትስቡጣ"

ደግ (ቸር) ገዥ ማለት ሲሆን "ትስቡጣ ናይናን" ማለት ቸር ገዥ ማረን ማለት ነው።

"አምንስቲቲ ሙኪርያቱ አንቲ ፋሲልያሱ"

የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙም “ተዘከረነ እግዚኦ በውስተ መንግሥትከ- አቤቱ በመንግሥትህ አስበኝ” ማለት ነው፡፡

"አምንስቲቲ መዓግያ አንቲ ፋሲልያሱ"

የቅብጥ ቃል ሲሆን “ተዘከረነ ኦ ቅዱስ በውስተ መንግሥትከ ቅዱስ ሆይ በመንግሥትህ አስበን” ማለት ነው

"አምንስቲቲ ሙዳሱጣ አንቲ ፋሲልያሱ"

የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙም “ተዘከረነ እግዚአ ኩሉ በውስተ መንግሥትከ፤የሁሉ የበላይ የሆንክ ወይ በመንግሥትህ አስበን” ማለት ነው፡፡

የ41 ስግደት ምን እየተባለ ነው የሚሰገድ?

አንድ ክርስቲያን በፆም ጊዜ ከፀሎት በኋላ የጌታን መከራና ለእኛ ያሳየውን ፍቅር እያሰበ ከሐጢያቱ ብዛት ከአምላኩ ይቅርታ ያገኝ ዘንድ 41 ጊዜ እንዲህ እያለ ይስገድ

12 ጊዜ ---- #እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ
12 ጊዜ ---- #በእንተ እግዝዕትነ ማርያም መሐረነ
ክርስቶስ
12 ጊዜ ---- #ኪራላይሶን (አቤቱ ማረን)
5 ጊዜ ---- #ሳዶር፣ አላዶር፣ ዳናት፣ አዴራ፣ ሮዳስ (አምስቱ የጌታ ችንካሮች)

✞ እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ጻማ ወድካም
✞ አመ ከመ ዮም ያብጽሐነ ያብጽሕክሙ
✞ ለብርሃነ ትንሳኤሁ እግዚአብሔር
✞ በፍስሐ ወበሰላም::


ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች
•➢ ሼር // SHARE
✧┈┈•◦●◈◎❖◎◈●◦•┈┈✧
•✥• @Z_TEWODROS •✥•
@Z_TEWODROS
•✥• @Z_TEWODROS •✥•
✧━━━━━━━━━━━━━━━━━✧
4.7K viewsዲያቆን አቤንዔዘር ሙሉ, 11:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 08:20:05 #የሰሙነ_ሕማማት_ማክሰኞ

#የጥያቄ_ቀን_ይባላል፦

ሰኞ ባደረገው አንጽሖተ ቤተመቅደስ ምክንያት፣ ሹመትን ወይም ሥልጣንን ለሰው ልጅ የሰጠ ጌታችን፣ ስለ ሥልጣኑ በጸሐፍት ፈሪሳውያን ተጠይቋልና፤ የጥያቄ ቀን ይባላል፡፡

ጥያቄውም ከምድራውያን ነገሥታት፣ ከሌዋውያን ካህናት ያይደለህ ትምህርት ማስተማር፣ ተዓምራት ማድረግ፣ ገበያ መፍታትን፣ በማን ሥልጣን ታደርጋለህ? ይህንንስ ሥልጣን ማን ሰጠህ? የሚል ነበር፡፡ /ማቴ. 21፥23-27፣ ማር. 11፥ 7-35፣ ሉቃ.21፥23-27፣ ማር.11፥27-33፣ ሉቃ. 20፥1-8/፤ እርሱም ሲመልስ፤ «እኔም አንድ ነገር እጠይቃችኋለሁ፣ እናንተም ብትነግሩኝ በማን ሥልጣን እነዚህን እዳደርግ እነግራችኋለሁ፡፡ የዮሐንስ ጥምቀት ከወዴት ነበረ፣ ከሰማይ ነውን? ወይስ ከሰዉ? በእግዚአብሔር ፈቃድ፣ ወይስ በሰው ፈቃድ?» አላቸው፡፡ እነርሱም ከሰማይ ብንል ለምን አልተቀበላችሁትም ይለናል፤ ከሰው ብንል ሕዝቡ ሁሉ ዮሐንስን እንደ አባት ያከብሩታል፣ እንደ መምህርነቱ ይፈሩታልና ሕዝቡን እንፈራለን፤ ተባብለው ከወዴት እንደሆነ አናውቅም ብለው መለሱለት፡፡ እርሱም እኔም በማን ሥልጣን እነዚህን እንደማደርግ አልነግራችሁም አላቸው» ይህንንም መጠየቃቸው እርሱ የሚያደርጋቸውን ሁሉ በራሱ ሥልጣን እንዲያደርግ አጥተዉት አልነበረም፣ ልቡናቸው በክፋትና በጥርጥር ስለተሞላ እንጂ፡፡

#የትምህርት_ቀንም_ይባላል፡-

በማቴ. 21፥28፣ ማቴ. 25፥46፣ ማር.12፥2፣ ማር.13፥37፣ ሉቃ. 20፥9፣ ሉቃ. 21፥38 የሚገኙት ትምህርቶች ሁሉም የማክሰኞ ትምህርት ይባላሉ፡፡ በዚህ ዕለት በቤተ መቅደስ ረጅም ትምህርት ስላስተማረ፣ የትምህርት ቀን ይባላል፡፡ ክርስቲያን የሆነ ሁሉ ከሥጋዊ ነገር ርቆ በዚህ ሰሞን የሃይማኖት ትምህርት ሲማር ሲጠይቅ መሰንበቱም መጽሐፋዊ ሥርዓት ነው፡፡

         "እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ጻማ ወድካም
             አመ ከመ ዮም ያብጽሐነ ያብጽሕክሙ
   እግዚአብሔር ለብርሃነ ትንሣኤሁ በፍስሓ ወበሰላም!"

ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች
                •➢ ሼር // SHARE

@Z_TEWODROS
@Z_TEWODROS
@Z_TEWODROS

Comment @Channel_admin09
5.7K views◦•●Yaredo●•◦, 05:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 08:01:40
አስደሳች መልዕክት ከአያት አ.ማ

አያት ሪል ኢስቴት መጪዎቹ የትንሳኤና የኢድ አል ፍጥር በዓላትን ምክንያት በማድረግ ለሽያጭ ባቀረባቸው አፓርትመንቶች ላይ እስከ 30 በመቶ የሚደርስ ቅናሽ ማድረጉን ሲገልፅ በታላቅ ደስታ ነው!
የመሸጫ ዋጋ እና አከፋፈል
1) ለ107 ካሬ ቤት ከ896,319 ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ፣
2) የካሬ ዋጋ ብር 55,845፣
3) አፓርትመንቶቻችን ከብር 5,975,464 ጀምሮ መግዛት ይችላሉ።
እስከ 3 ዓመት በ7 ጊዜ ክፍያ ቀስ ብለው መክፈል ከፈለጉ፦
የመጀመሪያው ክፍያ__15%
2ኛው ክፍያ___16%
3ኛው ክፍያ___23%
4ኛው ክፍያ___23%
5ኛው ክፍያ___13%
6ኛው ክፍያ___5%
7ኛው ክፍያ___5%
ከ5 እስከ 30 አመት በሚደርስ የረጅም ጊዜ የ60/40 የዱቤ ክፍያ በ9.5% ዓመታዊ ወለድ ዘና ብለው የሚከፍሉበት አማራጭም አቅርበናል።
ሲ ኤም ሲ በሚገኘው በ140,000 ካሬ ሜትር ይዞታ ላይ ባረፈው ዘመናዊ መንደር በዉስጡ:-
   ሰፊ የመናፈሻ ቦታ
   አፀደ ህፃናት
   ዘመናዊ የመኪና ማቆሚያ
  የከርሰ ምድር ውሃ with high capacity pump
  የሰውና የዕቃ ዘመናዊ ሊፍቶች with automatic generator
  ዘመናዊ የቆሻሻ ማስወገጃ ያለው፣
  የተለያየ ግብይት የሚከወንበት 4,000 ሱቆችን የያዘ በአገራችን ግዙፉ Mall ያካተተ እንዲሁም
የስምንት ትርፋማ ኩባንያዎች ባለቤት የሚያደርግዎትን የአያት አክስዮን ማህበር አክስዮኖችን በመግዛት በየዓመቱ እስከ 50% ትርፍ ያግኙ

WhatsApp, Viber, Telegram & Linked In via +251911141372
Email:  tesema12015@gmail.com

https://t.me/Tese_Apartment
4.8K views◦•●Yaredo●•◦, 05:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ