Get Mystery Box with random crypto!

☦የዘላለም ✞ ሕይወት¤ETERNAL LIFE

የቴሌግራም ቻናል አርማ yezelalemhiywet — ☦የዘላለም ✞ ሕይወት¤ETERNAL LIFE
የቴሌግራም ቻናል አርማ yezelalemhiywet — ☦የዘላለም ✞ ሕይወት¤ETERNAL LIFE
የሰርጥ አድራሻ: @yezelalemhiywet
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.11K
የሰርጥ መግለጫ

🔊ሕይወትም ተገለጠ አይተንማል
እንመሰክርማለን፥ ከአብ ዘንድ የነበረውንም ለእኛም የተገለጠውን የዘላለምን ሕይወት እናወራላችኋለን፤|1ኛ ዮሐ 1፥2
🔊ሕይወት ከሞት በኃላ ከጌታ ጋር ይቀጥላል፡፡ቻናሉ የተከፈተው ሰዎች በክርስቶስ በማመን የሚገኘውን ሕይወት እንዲካፈሉና የቃሉን እውነት ተምረው አርነት እንዲወጡ ነው፡፡You can contact me📲 @YesZoelife

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2022-07-30 09:50:30 የቀጠለ; ከድሉም በኃላ በራእይ መጽሐፍ ላይ የተነገረው ትንቢት አካል መልበስ ይጀምራል።የሺህ አመት መንግስት።ሃሌ ሉያ! ኢየሱስ በዚህኛው ምጽአቱ ላይ በዋናነት የመጣበት ሁለት ምክንያቶች ናቸው።አንድኛው እስራኤልን የወጉትን ሁሉ ድል ሊነሳና ለእያንዳንዱም ነገስታትና ለአውሬው ፍርድን ሊሰጥ ሲሆን፤ በሁለተኛነት አስደናቂ የሆነውን የሺህ አመት መንግስት ለመመስረትና አሁን በምናያት አለም ላይ ለአንድ ሺህ አመት መንግስት ሁኖ አሕዛብን ሊገዛ ነው።መጽሐፍ ሲናገር አሕዛብን ይገዛ ዘንድ የብረት ብትር ተጠሰው ይላል።ልክ ሰባኛው ሱባኤ በአርማጌዶ ጦርነት በኢየሱስ ድል አድራጊነት ከተጠናቀቀ በኃላ አዲስ አመት ማለትም ለአንድ ሺህ አመት የሚቆይ ዘመን መቆጠር ይጀምራል።ራእይ ምዕራፍ አስራ ዘጠኝን ሙሉ አንብቡት ልክ ጦርነቱ በልጁ ድል አድራጊነት ከተጠናቀቀ በኃላ ምዕራፍ ሃያ ላይ ቅደም ተከሉን ጠብቆ ስለሺህ አመት መንግስት መመስረት ይናገራል።

ይሄ የሺህ አመት የንግስ ሂደት የሚመሰረተው በኢየሩሳሌም በእስራኤል ምድር ነው።ልክ በአዲስ አበባ የጠቅላይ ሚኒስተሩ ቤተ-መንግስት በአራት ኪሎ እንዳለ ሁሉ፥ የእግዚአብሔር መንግስት በእየሩሳሌም ምድር በአካል ይመሰረታል።ከሙሽራው ጋር ለዘላለም ቃል ኪዳን ያደረገቺው ቤተ-ክርስትያንም በዚህ የንግስ ዘመን አብራ(አብረን) ከበጉ ጋር ለአንድ ሺህ አመት እንነግሳለን።ራእይ 20፥6 ምን እሱ ብቻ እነዛ መቶ አርባ አራት ሺህ ወጣቶቹም አብረው ይነግሳሉ።እነዛ ለአውሬውና ለምስሉ አንሰግድም ምልክቱን በግንባራችን አንቀበልም ያሉትም ይነግሳሉ።ራእይ 20፥4 ኢየሱስ ለሺህ አመት እቺን አለም ይገዛታል።ያን ጊዜ አሁን እያሳተ ያለው ዲያቢሎስ ለአንድ ሺህ አመት በጥልቅ አሕዛብን እንዳያስት ይታሰራል።የጥልቁንም መክፈቻና ታላቁን ሰንሰለት በእጁ የያዘ መልአክ ከሰማይ ሲወርድ አየሁ።የቀደመውንም እባብ ዘንዶውን እርሱም ዲያብሎስና ሰይጣን የተባለውን ያዘው፥ ሺህ ዓመትም አሰረው፥ ወደ ጥልቅም ጣለው አሕዛብንም ወደ ፊት እንዳያስት ሺህ ዓመት እስኪፈጸም ድረስ በእርሱ ላይ ዘግቶ ማኅተም አደረገበት፤ ከዚያም በኋላ ለጥቂት ጊዜ ይፈታ ዘንድ ይገባዋል።ራእይ 20፥1-3

በጣም የገረመኝና የደነቀኝ ነገር ልንገራችሁ።እቺ ዓለም በአዳም ኃጢአት ምክንያት እርግማን እንደደረሰባት በዘፍጥረት ላይ አይተናል።ሰው በሰራው ኃጢአት ፍጥረትን ጨምሮ አዛብትዋል።ለምሳሌ አዳም በኃጢአት ሳይወድቅ በፊት በኤደን ገነት ለሁሉም ለእንስሶች ስም ያወጣላቸው እርሱ ነው።ዘፍጥረት ላይ ገብታችሁ አንብቡት እንስሳቱም ሁሉ በአዳም ፊት በአካል እግዚአብሔር እያሳለፋቸው ከመንፈሳዊ አለም በሚያገኘው መገለጥ አንበሳ፣ ነብር፣ ቀጭኔ ወዘተ... እያለ ስም የሰጣቸው እርሱ ነበር።የሚገርመው አሁን ለማየት የሚያስፈሩን እንስሶች ያን ግዜ አዳምን ጫፉን አልነኩቱም ነበር።አሁን አንዱ እንስሳ አንዱን አድኖ ሲመገብ በዛን ሰዕት ግን የትኛውንም እንስሳት ሌላውን አድኖ አይበላም ነበር።ታድያ ለምንድነው አሁን የሰው ልጅ የዱር እንስሳትን ሲያይ የሚፈራው ስም እንዳላወጣላቸው? አንበሳስ የሰውን ልጅ ድንገት ጫካ ላይ ካየ ለምንድነው እንደምግብ ሁኖ የሚታየው? አዳምንስ ያን ጊዜ ለምን አልበላውም? አሁን ለምን ሰውን ሲያይ መብል መሰለው? ለዚህ ጥያቄ መልስ አንድ ነው የሰው ልጅ በሰራው ኃጢአት ምክንያት ነው።

አዳምን ያልበሉ እንስሶች እኔን አይበሉኝም ብሎ የሚያምን ሰው እስኪ ጫካ ይሂድና እንየው ከማሩት፤ ኃጢአት ሳይሰራ በፊት ሳር በል የነበሩት እንስሶች ሁሉም አይምሩትም ነበር።ለምን? ምክንያቱም አዳም በሰራው ኃጢአት የዚቺ አለም ስርዕት ስለተቀየረ።አንበሳ አሁን ስጋ በል የሆነው ኃጢአት ሳይሰራ በፊት እኮ ሳር በል እንስሳ ነበር።የሚገርማችሁ በኖህ ዘመን ይሄ ነገር ተመልሶ ነበር።እግዚአብሔር ኖህን ከሁሉም እንስሶች ሁለት ሁለት አድርገህ መርከቡ ላይ እንዲገቡ አድርግ ብሎ ሲያዘው።በአንድ መርከብ ላይ ያሁላ እንስሳ ተስማምተው አንዱ አንዱን ሳይበላ እንዲቀመጡ አደረገ።ኖህን እራሱ ጫፉን አልነኩትም።ታድያ በዚህ አንድ ሺህ አመት ንግስ ግዜም በዘፍጥረት ላይ የነበረው ስርዕት እግዚአብሔር ይመልሰዋል።አሁን ያለው የአለም ስርዕት ሁሉም ይቀየራል።እንዴት አትሉም!? ስጋ በል የሆነው አንበሳ ሳር በል ይሆናል።ላምና ድብ አብረው ይሰማራሉ፥ ግልገሎቻቸውም በአንድነት ያርፋሉ፤ አንበሳም እንደ በሬ ገለባ ይበላል።ኢሳይያስ 11፥7

ይሄ ትንቢተ ኢሳይያስ ላይ የተጻፈው ትንቢት ተፈጻሚነት የሚያገኘው በዚህ በሺህ አመት የንግስ ጊዜ ነው።አሁን ያሉት የዱር አራዊቶች በናሽናል ጂኦግራፊ ላይ አንዱ አንዱን እያሳደደ እያደነ ሲበላ የምናየው የሺህ አመት ጊዜ ወደዚህ ወደዘፍጥረት ቃል ይመለሳሉ።“ለምድርም አራዊት ሁሉ፥ ለሰማይም ወፎች ሁሉ፥ ሕያው ነፍስ ላላቸው ለምድር ተንቀሳቃሾችም ሁሉ የሚበቅለው ሐመልማል ሁሉ መብል ይሁንላቸው፤ እንዲሁም ሆነ።ዘፍጥረት 1፥30 አዎ! ሳር በል የነበሩ እንስሶች ሰው በሰራው ኃጢአት ምክንያት ስጋ በል ሁነዋል።በሺህ አመት ግን ይቀየራል።አንበሳም እንደላም ሳርን ይመገባል።ምን ይሄ ብቻ ያኔ የሚኖሩ አሕዛብም የዱር አራዊቶቹን አይፈሩም።የሚጠባውም ሕፃን በእባብ ጕድጓድ ላይ ይጫወታል፥ ጡት የጣለውም ሕፃን በእፉኝት ቤት ላይ እጁን ይጭናል።ኢሳይያስ 11፥8 በዚህ ሰዕት አንድ ህጻን በእባብ ጉድጓድ ከእባብ ጋር ልጫወት ቢል እባቡ አይምረውም።ያን ጊዜ ግን ሃሌሉያ! እንደአሁኑ አይሆንም።አሁን ነብርና ፍየል በአንድ ሁኖው መተኛት አይችሉም።ምክንያቱም ነብሩ ፍየልዋን በተኛችበት ቁርሱ ያደርጋታል።የሺህ አመት ጊዜ ግን ይሄ አይሰራም “ተኵላ ከበግ ጠቦት ጋር ይቀመጣል፥ ነብርም ከፍየል ጠቦት ጋር ይተኛል፤ ጥጃና የአንበሳ ደቦል ፍሪዳም በአንድነት ያርፋሉ፤ ታናሽም ልጅ ይመራቸዋል።ኢሳይያስ 11፥6

ይ----ቀ----ጥ----ላ----ል
@Yezelalemhiywet
@Yezelalemhiywet
@Yezelalemhiywet
2.9K viewsedited  06:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-30 09:47:48 የዘመን መጨረሻ!
ክፍል~ሰባት

እስራኤልን በአስራ አንደኛው ሰዕት በጉ በአርማጌዶ ምድር ነገስታቶቹን ድል ሊነሳ ይደርስላታል።ይሄ የሆነበት ምክንያት ነገስታቶቹ በእስራኤል ላይ በጣም ሲበረቱባቸው፥ በዛም ምክንያት እስራኤላውያን ኪዳን ወዳላቸው አምላክ ቀና ይላሉ።በዛን ሰዕት በህይወት የሚተርፉትም ሁሉም እስራኤላውያን ይድናሉ።ኪዳን ኢየሱስነው። በዛን ጊዜ ሁሉም ያዩታል።ሲመጣም አማኞችን ሊነጥቅ እንደመጣው እስከደመና ድረስ ሳይሆን እስከ ምድር ድረስ ይመጣል።የሚመጣው አንድም ነገስታትን ድል ሊያደርግ፣ ለእስራኤል የገባውን ኪዳን ሊፈጽምና በምድር ለአንድ ሺህ አመት ብቻ የሚመሰረተው የእግዚአብሔርን መንግስት ለመመስረት ነው።አርማጌዶ ላይ የሚደረገው ውግያ በዓለም ላይ ታይቶ የማይታወቅ የተለየ ነው።ፍጡር አምላኩንና ጭፍራዎቹን ሊወጉ የሚሰለፉበት ጦር።ነገስታትም በፈረሱም የተቀመጠውን ጭፍራዎቹንም ይወጉ ዘንድ አውሬውና የምድር ነገሥታት ጭፍራዎቻቸውም ተከማችተው አየሁ።ራእይ 19፥19

ዮሐንስ በራእይ ያየውን ተመልከቱ።ምስራቃውያንና ሌሎች የዓለም ነገስታት፣ በአውሬው፣ በሐሰተኛው ክርስቶስና በሐሰተኛው ነቢይ ጋር በመሆን ከሰማይ የሚገለጠውን ንጉስና አብረው የሚመጡትን አማኞችን ለመውጋት ይከማቻሉ።አሁን የምታዩትን መሳሪያ ያን ጊዜ ሊጠቀሙበት አርማጌዶ ላይ ይሰበሱቡታል።ሲያስቁ።ኢየሱስ እፍፍ ቢል እንደሚተኑ አላወቁም።የሚገርመው መጽሐፍ ሲናገር ይጨፈልቃችዋል ነው የሚለው።ነገስታት የሚያግዛቸው ብዙ ነገር አለ፤ በጉ ኢየሱስ ግን ብቻውን ይረግጣችዋል።በደምም የተረጨ ልብስ ተጐናጽፎአል፥ ስሙም የእግዚአብሔር ቃል ተብሎአል።ራእይ 19፥13 በደም የተረጨው ልብስ፥ እርሱን ለመውጋት የሚሰለፉትን ነገስታት እንደሚጨፈልቃቸውና በምድርም ታይቶ የማይታወቅ ደም እንደሚፈስ ለማሳየት ነው።

አንድም መልአክ በፀሐይ ውስጥ ቆሞ አየሁ፥ በሰማይም መካከል ለሚበሩ ወፎች ሁሉ፦ መጥታችሁ የነገሥታትን ሥጋና የሻለቃዎችን ሥጋ የብርቱዎችንም ሥጋ የፈረሶችንም በእነርሱም የተቀመጡትን ሥጋ የጌታዎችንና የባሪያዎችንም የታናናሾችንና የታላላቆችንም ሁሉ ሥጋ እንድትበሉ ወደ ታላቁ ወደ እግዚአብሔር እራት ተከማቹ ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኸ።ራእይ 19፥17-18 አንበሳውን ሊወጉ የተዘጋጁ ነገስታት በበጉ ድል አድራጊት ይጠናቀቃል።በሰባት ወር ተሰብስቦ የማያል የሰው ልጅ ሬሳ በዛ ምድር የሚበዛበት ጊዜ፣ ደም ጎርፍ እስኪመስል በምድር የሚጨቀይበት ጊዜ ይሆናል።በነጭ ፈረስ ላይ የነበረውም ልብሱ በደም የተረጨ ነበር ይላል ቃሉ።ኦ ጌታ ሆይ! ከዚህ ቁጣ ስለሰወርከንና በቁጣው ሰዕት አብረንህ በከበረ ማንነት ስለምንገለጥ እናመሰግንሃለን።ሙሽሪት የሙሽራዋን ድል አድራጊነት በአካል አብራው የምትመለከትበት ወቅት ነው።ሃሌ ሉያ!አሜን።

አውሬውም ተያዘ በእርሱም ፊት ተአምራትን እያደረገ የአውሬውን ምልክት የተቀበሉትን ለምስሉም የሰገዱትን ያሳተ ሐሰተኛው ነቢይ ከእርሱ ጋር ተያዘ፤ ሁለቱም በሕይወት ሳሉ በዲን ወደሚቃጠል ወደ እሳት ባሕር ተጣሉ።የቀሩትም በፈረስ ላይ ከተቀመጠው ከአፉ በሚወጣው ሰይፍ ተገደሉ፤ ወፎችም ሁሉ ከሥጋቸው ጠገቡ።ራእይ 19፥20-21 እዚህ ጋር ማስተዋል ያለብን በዛን ሰዕት ጌታ ኢየሱስ ድል የሚነሳቸው የሚጨፈልቃቸው በዛ ጦር ላይ የተሳተፉትን ነገስታትና አውሬውን ነው።የተቀሩትን አይነካም።በዛ ጦር ያልተሳተፉ አሕዛቦችና እስራኤላውያንን አይነካም።በምዕራፍ ስድስት ላይ በሱባኤው አጋማሽ ላይ የአውሬውን ምልክት የተቀበሉት ሁሉ ከአውሬውና ከሐሰተኛው ነቢይ ጋር ወደ ጥልቅ ይጣላሉ።ሐሰተኛው ክርስቶስም ወደ እሳት ይጣላል።በዛን ቀን ማንም በበጉ ፊት የሚቆም አይኖርም።ምክንያቱም ኢየሱስ ያን ጊዜ ወደምድር የሚመጣው እንደሚታረድ በግ ሁኖ ሳይሆን እንደሚያገሳ አንበሳ ነው።

@Yezelalemhiywet
@Yezelalemhiywet
@Yezelalemhiywet
1.7K viewsedited  06:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ