Get Mystery Box with random crypto!

Orthodox

የቴሌግራም ቻናል አርማ yeemariyaam21 — Orthodox O
የቴሌግራም ቻናል አርማ yeemariyaam21 — Orthodox
የሰርጥ አድራሻ: @yeemariyaam21
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 8
የሰርጥ መግለጫ

በገጠር ኢትዮጽያ ቅድስት ቤተክርስቲያን ሁለንተናዊ መረጃ እና የአገልግሎት ማነቃቂያ ለመስጠት የተከፈተ መንፈሳዊ የዘገባ እና የድጋፍ ማሰባሰቢያ ቻናል ነው

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2022-07-09 08:16:29
@yeemariyaam21
@yeemariyaam21
@yeemariyaam21
3.7K viewsedited  05:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-09 07:57:46 የዝምታ ጊዜ አስፈላጊነት

ለአንድ አማኝ ክርስቲያን ከእግዚአብሔር ጋር መቀመጡና ከእርሱ ጋር ህብረት መፍጠሩ እንደ ምን ያለ የተባረከ ልዩ መብት ነው! እንዲህ ያለው ሁኔታ ነው ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅን "ስትጸልይ ከእግዚአብሔር ጋር እየተነጋገርህ አይደለምን? ይህ እንደ ምን ያለ ልዩ መብት ነው!" በማለት በአድናቆት እንዲናገር ያደረገው። በአጠቃላይ የዝምታ ጊዜ ማለት ይህ ነው። አንተ በዚህ ልዩ መብትህ ሐሴት ማድረግ ትፈልጋለህ?

ምስጋና ይግባውና የዝምታ ጊዜን ጥቅም በኢየሱስ ክርስቶስ ሕይወት ውስጥ መገንዘብ ትችላላችሁ ፤ እርሱ ፍለጋውን እንከተለው ዘንድ ምሳሌ ትቶልን ሄዶአልና ፤1ኛ ጴጥ 2:21። አምላካችን በየዕለቱ ማልዶ በመነሣት ገለልተኛ ወደ ሆነ ቦታ እየሄደ ይጸልይ ነበር ፤ ማር 1:35። ሌሊቱንም ሙሉ ሲጸልይ ያድር ነበር ፤ ሉቃ 6:12። አብዝቶ ይጸልይ የነበረውም ወደ ምድረ በዳ በመሄድ ነበር ፤ ሉቃ 5:16።

በእርግጥ ለክርስቶስ ጸሎት አስፈልጎት ነበር እንዴ?

በሥላሴ መካከል ያለው አንድነት የማይለያይ ለመሆኑ ጥርጥር የለውም። በዚህ ምክንያት ወልድ ለአብ እንዲህ በማለት ተናግሮአል ፦ ". . አባት ሆይ ፤ በእኔ እንዳለህ እኔም በአንተ፤. . " ዮሐ 17። መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይህን ያደረገው የእርሱን ፈለግ ለሚከተሉ ሰዎች ሁሉ ከእግዚአብሔር ጋር ለሚኖራቸው ቁርኝት ማስረጃ እንዲሆን ነው።

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ያሉትን ሰዎች ሕይወት ስንመለከት ለመንፈሳዊ ሕይወታቸው የበጀውን የዝምታ ጊዜ ጥቅም መገንዘብ እንችላለን። በመቀጠል ጥቂት ምሳሌዎች ቀርበውልናል፦

ሀ/ ነቢዩ ዳዊት።

እንደ ንጉሥነቱ ፣ እንደ መሪነቱና እንደ ፈራጅነቱ ባተሌ ሰው ቢሆንም እንኳ ዘወትር በማለዳ ከእግዚአብሔር ጋር ብቻውን የሚሆንበት ጊዜ ነበረው። "በማለዳ ድምፄን ትሰማለህ ፤ በማለዳ በፊትህ እቆማለሁ ፤ እጠብቃለሁም።" መዝ 5:3።

ለ/ ዳንኤል

ነብዩ ዳንኤል ብቻውን ከእግዚአብሔር ጋር ሆኖ በመጸለይ ጊዜውን ማሳለፍን ልማድ አድርጎት ነበር። ንጉሡ ይህን እንዳያደርግ በጽሑፍ ቢከለክለውም እንኳ ግድ አልሰጠውም። ይልቁንም እንዲህ ነበር ያደረገው ፦ "ዳንኤልም ጽሕፈቱ እንደ ተጻፈ ባወቀ ጊዜ ወደ ቤቱ ገባ፤ የእልፍኙም መስኮቶች ወደ ኢየሩሳሌም አንጻር ተከፍተው ነበር ፤ ቀድሞም ያደርግ እንደ ነበረ በየዕለቱ ሦስት ጊዜ በጉልበቱ ተንበርክኮ በአምላኩ ፊት ጸለየ፣ አመሰገነም።" ዳን 6:10።

እስቲ ለዚህ ድንቅ ዓረፍተ ነገር ትኩረታችሁን ስጡት ፣ "ቀድሞም ያደርግ እንደ ነበረ. . " ለሚለው። የዝምታን ጊዜ ማሳለፍ በእርሱ ሕይወት ውስጥ የማያቋርጥ ልማድ ነበረ።

ሐ/ ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ

ቅዱስ ጴጥሮስ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በህብረት በሚካሄደው ጸሎት ላይ ከነበረው ተሣትፎ በተጨማሪ በየዕለቱ በአንድ ልብ ሆነው ለጸሎት ሲሰበሰቡ አብሮ ይገኝ ነበር። እርሱ ጊዜውን ለጸሎት ያውል ነበር። ስለ ቅዱስ ጼጥሮስ መጽሐፍ ቅዱስ " . . . ጴጥሮስ በስድስት ሰዓት ያህል ይጸልይ ዘንድ ጣራው ወጣ።" (ሐዋ 10:9) የሚል ቃል ዘግቦ እናነባለን።

እነዚህንና ሌሎች ብዙ ተጨማሪ ምሳሌዎችን መሠረት አድርጋችሁ ስትመለከቱ ከእግዚአብሔር ጋር የሚሆን የጸሎትና የዝምታ ጊዜ ያለውን ጥቅም መገንዘብ ትችላላችሁ። ከእግዚአብሔር ጋር የሚደረግ የቅርብ ግንኙነት በመንፈስ ለተሞላ ሕይወት ሀይል መሣሪያ ነው።

የግብጽ ኦሮቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን አባት ዘካርያስ ቡትሮስ እንደ ጻፋት

@yeemariyaam21
@yeemariyaam21
@yeemariyaam21
4.0K viewsedited  04:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 13:24:44
ወድ የድንግል ማርያም ልጆች

እስከዛሬ ድረስ የድንግል ማርያም ልጆችን ቁጥር ለመጨመር የተለያዩ ማስታወቂያ መለቀቁ ይታወሳል።

ከዛሬ ጀምሮ ምንም አይነት ማስታወቂያ የማይለቀቅ መሆኑን ለማሳወቅ እወዳለሁ

ስላለፈው ስህተት ይቅርታ እጠይቃለሁ

የተለያዩ ወጣቶችን በተመለከተ እና መንፈስን የሚደስ በተጨማሪም መንፈሳዊነት የሚጠናከርበትን ትምህርቶች መልቀቅ እንጀምራለን እናተም ሌሎች ሼር ማድረግ አትርሱ።

እግዚአብሔር ይመስገን ስለሁሉም



@yeemariyaam21
@yeemariyaam21
@yeemariyaam21
4.3K viewsedited  10:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 09:23:30
ልደታ ለማርያም የአስራት ሀገርሽን ኢትዮጵያ እና ህዝቦቿን ጠብቂን አሜን አሜን አሜን
3.8K views06:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 09:21:14
የመጀመሪያው አዳሪ የአብነት ት/ቤት በአሜሪካ

መልካም ዜና ነው

"ወይኩን ቡሩከ ስሙ ለእግዚአብሔር
እምሥራቀ ጸሐይ እስከነዐረብ ይትአኰት ስሙ"

ስለ ሁሉም ነገር የእግዚአብሔር ስሙ ከጸሐይ መውጫ እስከ መጥለቂያ ድረስ የተመሰገነ ይሁን!!! እግዚአብሔር ረድቶን በአሜሪካን ሀገር የመጀመሪያውን አዳሪ የአብነት ትምህርት ቤት በፈረንጆች በጋ (Summer Camp) ጀምረናል። ሁሉም ነገር እንደ ጀማሪ ሳይሆን ልክ እንደነባር እንዲሆንልን የእግዚአብሔር ቸርነት አግዞናልና ይክበር ይመስገን!

ወላጆች በዓላማው አምነውበት ልጆቻቸውን ከስድስት እስከ ስምንት ሳምንት ድረስ ሰጥተውናል! እኛም ተረክበን የምንችለውን እያደረግን ነው። አባቶች እየመጡ እያስተማሩ ፈሪሐ እግዚአብሔር፣ ፍቅረ ቤተ ክርስቲያን ያድርባቸው ዘንድ የተቻለውን እያደረጉ ነው! ሁላችሁም በጸሎታችሁ አስቡን!!!
........................................................
ከብዙ ድካም በዋላ የመጀመሪያ መልካም ስራ እግዚአብሔር ይመስገን እንዲህ አደረኩ አይባልም እና ሌሎችም እኔን አሳብ ማስቀጠል ትችላላችሁ ሙሉ መረጃዎችን እሰጣቸዋለሁ ከፈለጋችሁ

ለክፋት ለምትፈልጉ ለቤተክርስቲያን ከሆነ ማንኛውንም በነገር በነፃ አማክራቹዋለው

ለማንኛውም የእኔን የስነልቦና የማማከር አገልግሎት የቴሌግራም ቻናል ከፈለጋችሁ

https://t.me/BiniGirmachew

እየገባችሁ ማንበብ ትችላላችሁ
3.8K views06:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ