Get Mystery Box with random crypto!

🗣 ወቅታዊ_መረጃ 🇪🇹

የቴሌግራም ቻናል አርማ wekitawi_meraja — 🗣 ወቅታዊ_መረጃ 🇪🇹
የቴሌግራም ቻናል አርማ wekitawi_meraja — 🗣 ወቅታዊ_መረጃ 🇪🇹
የሰርጥ አድራሻ: @wekitawi_meraja
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 14.40K
የሰርጥ መግለጫ

This is national and international News and advertising channel
🇪🇹🇪🇹🇪🇹"ስለኢትዮጲያ ሳትሰማ ያሳለፍከው ቀን እንደባከነ ይቆጠራል" 🇪🇹🇪🇹🇪🇹
⏭▶️➡️ ሀገራዊና አለም አቀፋዊ ዜናዎችን በፍጥነት ይደርሶታል።🔚

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-08-31 19:44:25 ሰበር ዜና

በዋግ ኽምራ ዞን በዝቋላ ወረዳ ስር የነበረና ጁንታው ይተማመንበት የነበረው የቅዳሚት ማዕከል ምሽግ በጥምር ሃይሉ ሙሉ በሙሉ ተደምስሷል:: በዚህም ምክንያት ጁንታው ወደ አብርገሌ ከተማ እየሸሸ ነው አብርገሌ ማለት ለሰቆጣ 65 ኪሎ ሜትር ይርቃል ለመቀሌ ደግሞ 45 ኪሎ ሜትር ይርቃል

እያመመው መጣ
ቻናላችንን በመቀላቀል
ዓለም-አቀፋዊ እና አገር-አቀፍ መረጃዎችን በቴሌግራም ገፃችን ይከታተሉ።
@Merja01
3.5K views16:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 17:55:59
#Update

የደሴ ነዋሪዎች አካባቢያቸውን በንቃት በመጠበቅ የከተማዋን ሰላም ሊያስጠብቁ እንደሚገባ የደሴ ከተማ አስተዳደር ገልጿል።

ነዋሪዎች በሚነዙ ሀሰተኛ ወሬዎች፣ መረጃዎችና አሉባልታ አትደናገሩ ብሏል።

ማንኛውም የተለየና አጠራጣሪ ነገር ሲመለከቱ ነዋሪዎች ለጸጥታ ኃይል በማሳወቅ ሀላፊነታቸውን እንዲወጡም ተጠይቋል።

ከተለያዩ አከባቢዎች ለመጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ ማድረግ እንደሚገባ ነገር ግን በዚህም መሃል ሰርገው ሊገቡ የሚችሉ የጥፋት ኃይሎች ካሉ በመከታተል ለሚመለከተው የጸጥታ ኃይል መጠቆም እንደሚገባ አስተዳደሩ ገልጿል።

የባንክና መሰረታዊ አገልግሎቶች ክፍት ሆነው እየተሰጡ መቀጠል እንዳለባቸው አፅንኦት የተሰጠ ሲሆን አገልግሎት በሚያቋርጡና ዋጋ አላግባብ በሚጨምሩ ነጋዴዎች ላይ ጥብቅ እርምጃ እንደሚወሰድ ማስጠንቀቂያ ተላልፏል።

በከተማው የታወጀውን አሰገዳጅ ህግ ሁሉም ሊያከብረው የሚገባ ሲሆን ጥሰት የሚታይ ከሆነ አስተዳደሩ ትእግስት እንደማያደርግና እርምጃ እንደሚወስድ አጥብቆ አስጠንቅቋል።

በሌላ በኩል ፤ የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር በየመዝናኛ ቤቶችና ህዝብ በሚሰበሰብበት ቦታዎች ላይ አሉባልታ ወሬ በማናፈስ ህብረተሰቡ እንዳይረጋጋ በማድረግ ኗሪው በፍርሃት ከተማውን ለቆ እንዲወጣ ተልዕኮ ይዘው የሚንቀሳቀሱ ግለሰቦች እንዳሉ ገልጿል።

ህብረተሰቡ ይህንን በማወቅ በአሉባልታ ሳይደናገር የራሱን ጥንቃቄ እንዲያደርግ መልዕክት አስተላልፏል።

የከተማው ጸጥታ ማዋቅር የከተማውን ሰላም ለማስጠበቅ እየሰራ መሆኑንም የገለፀ ሲሆን ህብረተሰቡ ተደራጅቶ አካባቢውን እንዲጠብቅ ጥሪ አቅርቧል።

ወልድያን በተመለከተም ዛሬም #ሰላማዊ ሁኔታ የቀጠለ ሲሆን ነዋሪዎች ከአሉባልታ በመራቅ አካባቢያቸውን በንቃት እንዲጠብቁና ድጋፋቸውን እንዲያጠናክሩ ጥሪ ቀርቧል።
https://t.me/Merja01
1.1K views14:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 14:21:10
ከመንግስት የተሰጠ መግለጫ




ሼር በማድረግ ትክክለኛዉን መረጃ ለሌሎች ተደራሽ ያድርጉ። ለበለጠ መረጃ ቴሌግራም
https://t.me/Merja01
2.2K views11:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 14:15:08 ከጋዝጊብላ ወረዳ ፀጥታ ም/ቤት በወቅታዊ የፀጥታና ደህንነት ጉዳይ የተላለፈ ውሳኔ!

1ኛ. ማንኛውም እግረኛ ከምሽቱ 2፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ንጋቱ 12፡00 ሰዓት ድረስ መንቀሳቀስ በጥብቅ የተከለከለ ነው።

2ኛ. የጠላትን ሀሳብና እንቅስቃሴ በመደገፍ አሉባልታ በማናፈስ በህብረተሰብ መካከል ሽብርና ውዥንብር በሚነዙ የተሳሳተ መረጃ የሚያሰራጩ አካላት ላይ በህግ እንዲጠየቁ ተወስኗል።

3ኛ. ለህዝብ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማትን ማለትም ምግብ ቤት፣ ሱቆች፣ ወፍጮ ቤቶች፣ባንክ ቤቶች እና ሌሎች መሠል የህዝብ አገልግሎት መስጫ ተቋሞችን መዝጋት የተከለከለ ነው።

4ኛ. ወቅታዊ ሁኔታውን ምክንያት በማድረግ በምርትና አገልግሎት ላይ ተገቢ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪ ማድረግ, ምርትን በመሠወር ዕጥረት እንዲከሰት ማድረግ በህግ ያስጠይቃል።

5ኛ. ለጸጥታ ስራ ስምሪት ከተሰጣቸው ተሸከርካሪዎች ውጭ ማንኛውም ተሸከርካሪ ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ንጋቱ 12፡00 ሰዓት ድረስ መንቀሳቀስ በጥብቅ የተከለከለ ነው።

6ኛ. ከጸጥታ መዋቅሩ ውጭ በየትኛውም ሰዓትና ቦታ የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ በጥብቅ የተከለከለ ነው፡፡

7ኛ. በከተማችን የሚገኙ የመንግስትና የግል ታጣቂዎች መንግስት በሚያሰማራው የፀጥታ ስራ በቅንጅትና ቁርጠኝነት ተሳታፎ በማድረግ ህዝብና መንግስት የጣለባችሁን ሃላፊነት መወጣት ይኖርባችኋል፣ ሃላፊነታቸውን በማይወጡት ላይ አስፈላጊውን ርምጃ ይወሰዳል።

8ኛ. ማንኛውም ማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚ ግለሰብ ሆነ ድርጅት የትኛውንም ሚዲያ ተጠቅሞ ስለጦርነት: ስለ ጥምር ጦሩ እንቅስቃሴ: ስምሪት: አቋምና የትጥቅ ሁኔታ መዘገብ መረጃዎችን ማሰራጨት በጥብቅ የተከለከለ ነው።

9ኛ. ማንኛውም ግለሠብ በከተማው አጠራጣሪ እንቅስቃሴ ወይም ድርጊቶች፣ ጸጉረ ልውጥ ሰዎች፣ አጠራጣሪ ግለሰብ ተሽከርካሪ ወዘተ ሲታዩ ለጸጥታ ተቋማት የመጠቆም ግዴታ አለበት።

10ኛ. በመንግስት ከተፈቀደላቸው የፀጥታ አካላት ውጭ ማንኛውም አካል የመከላከያ: የልዩ ሀይል: የፌዴራል እና የመደበኛ ፓሊስ መለዮ በከፊል ሆነ ሙሉ መልበስ በጥብቅ የተከለከለ ነው፣ ለብሶ የተገኘ በህግ ይጠየቃል።

11ኛ. ማንኛውም የቤት አከራይ ወይም አልጋ ቤቶች ተከራዮቻቸውን ማንነታቸውን የሚገልፅ ህጋዊ መታወቂያ ስለመኖራቸው የማረጋገጥና መታወቂያውን ኮፒ በማድረግ ለፀጥታ ተቋም በወቅቱ የማሳወቅ ግደታ አለባቸው።

12ኛ. ከወቅታዊ የጸጥታ ጉዳዮች ጋር ተያይዞ በምግብ ቤቶች፣ በመጠጥ ቤቶች፣ በካፌዎችና ፊልም ቤቶች ከምሽት 1:00 ሰዓት በኋላ ማንኛውም አገልግሎት መስጠት የተከለከለ ነዉ

13ኛ. በማህበራዊ ሚዲያ ሆነ በማናቸውም የግንኙነት አይነት ሀሰተኛ መረጃ፣ በሬ ወለደ ወሬ በመንዛት በህዝብ ላይ አላስፈላጊ ውዥንብርና ስጋት መፍጠር በህግ ያስጠይቃል። ህዝቡም መረጃዎችን ከትክክለኛ የመረጃ ምንጭ ብቻ በመውሠድ በበሬ ወለደ ወሬ ሳይደናገጥ መደበኛ ተግባሩን በተረጋጋ መንገድ እንዲያከናወን እናሳስባለን።

የጋዝጊብላ ወረዳ ፀጥታ ም/ቤት

ሼር በማድረግ ትክክለኛዉን መረጃ ለሌሎች ተደራሽ ያድርጉ። ለበለጠ መረጃ ቴሌግራም
https://t.me/Merja01
2.1K views11:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 14:15:08
2.0K views11:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 14:08:32
መከላከያ “ይህ ሁሉ ሕዝብ ለህወሃት ምንም አያደርግም እባካችሁ ተመለሱ” ቢልም በሰላሙ ጊዜ አራሽ በችግር ጊዜ ተኳሽ የሆነው የሁመራ ገበሬ ግን ትጥቁን ሸካክፎ ወደ ማይካድራ ላይ በሺዎች የጨረሰብን ህወሃትን ለመበቀል ከዚህ የተሻለ ጊዜ አናገኝም ተውን እንዋጋበት በማለት ግንባር እየተመመ ይገኛል።

ሼር በማድረግ ትክክለኛዉን መረጃ ለሌሎች ተደራሽ ያድርጉ። ለበለጠ መረጃ ቴሌግራም
https://t.me/Merja01
2.1K views11:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 07:00:01 ኢትዮጵያን የብጥብጥ ማዕከል ለማድረግ ሲሰሩ በነበሩ 111 ህገወጥ የዲጂታል ሚዲያዎች ላይ ክስ ተመስርቷል- የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን

ነሐሴ 24 ቀን 2014 (ኢዜአ) በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ሀሰተኛ መረጃዎችን በማሰራጨት ኢትዮጵያን የብጥብጥ ማዕከል ለማድረግ ሲሰሩ በነበሩና በመገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ህጋዊ እውቅና በሌላቸው 111 የዲጂታል ሚዲያዎች ላይ ክስ መመስረቱን የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

በኮሚሽኑ የታክቲክ ወንጀሎች ምርመራ ምክትል ዋና መምሪያ ሃላፊ ረዳት ኮሚሽነር ብርሃኑ አበበ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በተደራጁና የሽብር ወንጀሎች፣ በሙስና፣ በፋይናንስና ንግድ ነክ፣ በታክስና ጉሙሩክ ወንጀሎች ላይ ጥቆማዎችን መነሻ በማድረግ ምርመራዎች ተከናውነዋል።

በዚህም መሰረት 2 ሺህ 668 ጥቆማዎችን በመቀበል 1 ሺህ 438 መዝገቦችን መርምሮ ለፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ መላካቸውንም ገልጸዋል፡፡

ከዚህ ውስጥ ሀገሪቱን የብጥብጥ ማዕከል ለማድረግ ሲሰሩ በነበሩና ሀሰተኛ የማህበራዊ ሚዲያ ስያሜ በመጠቀም ሲንቀሳቀሱ በነበሩ አካላት ላይ ክስ መመስረቱን ተናግረዋል፡፡

እነኚህ አካላት ህዝብን ለአመጽ በማነሳሳት ድብቅ ዓላማቸውን ለማሳካት ሲንቀሳቀሱ እንደነበርም በምርመራ መረጋገጡን ነው ያብራሩት።

መረጃ ተጣርቶባቸው ክስ የተመሰረተባቸው 111 የሚሆኑት የዲጂታል ሚዲያዎች በመገናኛ ብዘሃን ባለስልጣን ህጋዊ እውቅና እንደሌላቸው ተናግረዋል፡፡

በአሁኑ ጊዜም የእነኚህ ህገወጥ የዲጂታል ሚዲያ ባለቤቶች በህግ ቁጥጥር ስር ውለው ጉዳያቸው እየታየ መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡

በበጀት ዓመቱ በሞባይል ባንኪንግ ገንዘብ በማጭበርበር የባንኮችን መልካም ስም የማጉደፍ ወንጀል የፈጸሙ ግለሰቦች በቁጥጥር መዋላቸውን ገልጸዋል።

ግለሰቦቹ ከ57 ሚሊየን ብር በላይ መዝረፋቸው በምርመራ በመረጋገጡ ክስ ተመስርቶባቸዋል ነው ያሉት።

የፌደራል ፖሊስ የአገልግሎት ተደራሽነቱን በማስፋት በተለያዩ ክልሎች ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶችን ከፍቶ የወንጀል ምርመራዎችን እንደሚያጣራ ገልጿል።

ሼር በማድረግ ትክክለኛዉን መረጃ ለሌሎች ተደራሽ ያድርጉ። ለበለጠ መረጃ ቴሌግራም
https://t.me/Merja01
2.9K views04:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 07:00:01
2.7K views04:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 06:55:13
የምዕራብ እዝ አዛዥ የነበረው የህውሃቱ ጀኔራል ፍስሃ ኪዳኑ(ፍስሃ ማንጁስ) ማለት ይሄ ነው ከአንቶኖቭ አውሮፕላኑ ጋር በጀግናው አየር ሃይልችን ጥቃት የጋየው::

ሼር በማድረግ ትክክለኛዉን መረጃ ለሌሎች ተደራሽ ያድርጉ። ለበለጠ መረጃ ቴሌግራም
https://t.me/Merja01
2.7K viewsedited  03:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 21:10:07 የላሊበላ ከተማ የፀጥታ ምክር ቤት ወቅታዊ ሁኔታን መነሻ በማድረግ የሰዓት ዕላፊ ገደብን ጨምሮ ሌሎች ውሳኔዎችን አሳልፏል

ውሳኔዎቹ ፦

ከምሽቱ 1:00 ሰዓት እስከ ንጋቱ 12:00 ሰዓት ወደ ከተማዋ መግባትም ሆነ መውጣት አይቻልም።

ማንኛውም ተሽከርካሪ ከምሽቱ 1:00 ሰዓት በኋላ እስከ ንጋቱ 12:00  ድረስ መንቀሳቀስ አይቻልም።

ከተፈቀደለት አካል ውጭ የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ በጥብቅ ተከልክሏል።

በመንግስት ዕውቅና ካለው የፀጥታ አካል ውጭ የፀጥታ አካላትን የደንብ ልብስ ለብሶ መንቀሳቀስ በፍፁም አይቻልም።

የላሊበላ ከተማ አስተዳደር ህዝቡ በሀሰተኛ ወሬ እና አሉባልታ ሳይደናገር አካባቢውን በንቃት እንዲጠብቅ መልዕክት አስተላልፏል።

ሼር በማድረግ ትክክለኛዉን መረጃ ለሌሎች ተደራሽ ያድርጉ። ለበለጠ መረጃ ቴሌግራም
https://t.me/Merja01
3.2K views18:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ