Get Mystery Box with random crypto!

🌷❤️🌹 ውብ ፍቅር🌹❤️🌷

የቴሌግራም ቻናል አርማ wbfqr — 🌷❤️🌹 ውብ ፍቅር🌹❤️🌷
የቴሌግራም ቻናል አርማ wbfqr — 🌷❤️🌹 ውብ ፍቅር🌹❤️🌷
የሰርጥ አድራሻ: @wbfqr
ምድቦች: ሽያጭ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 507

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2021-04-02 19:30:13 ለውብ ቀን!


አብሮ መጨፈርን ሰጥቶ፣ አብሮ ማልቀስን ማን ነጠቀን?



ሁሉም ከሳሽ ፤ሁሉም ምሁር ፤ሁሉም ጨዋ፤ ሁሉም ወቃሽ ፤ሁሉም ሊቅ፤ ሁሉም አዛኝ፤ ሁሉም አቅጣጫ ጠቋሚ ፤ ሁሉም አውሪ ፤ሁሉም ብያለው ባይ ፤ ሁሉም ጆሮ አልባ ነው።

ተመሳሳይ ሃሳብ፤ ተመሳሳይ ምልከታ፤ ተመሳሳይ ህልም ፤ተመሳሳይ ዜና ፤ተመሳሳይ ክስ ፤ተመሳሳይ ውዳሴ ፤ተመሳሳይ አቋም ፤ተመሳሳይ ድጋፍ ፤ተመሳሳይ ሙግት ።

የቡድን ጀግና፤የቡድን ተቆርቋሪ ፤የቡድን ተከራካሪ ፤የቡድን ተከላካይ ፤ቡድናም እይታ ፤የቡድን ጭብጨባ ፤ የቡድን ሳቅ ፤የቡድን ሙሾ ፤ የቡድን ሙግት ፤የቡድን መልስ ። የቡድን ጩኸት

ሃላፊነት የሚወስድ አንድም የለም ። ዝቅጠት ላይ አስተዋፅዖ እንደ አበረከተ የሚያወራ ።አንድም የለም። ሁሉም ጣት ቀሳሪ ፤ ሁሉም ዳር -ነኝ ባይ ነው ።



ሃይማኖታችን ጥንጥ ሞራል ፤ጥንጥ ርህራዬ ትንሽ መተዛዘን ካልፈጠረልን ምን ይሰራልናል ???

የሃይማኖት ስፍራዎች ለምን ግንባቸው ተሸንሽኖ ቤት አልባ ሰዎች አይኖሩበትም??

መስበኪያ ስፍራዎች ለምን ወደ መበየጃ ወደ መሸመኛ ፤ወደ መጥለፍያ ቦታዎች አይቀየሩም ።

እምነት አልባ ህዝብ ውስጥ ይሄ ሁላ ማምለክያ ግንብ ምን ይረባል !!

በዚህ ደረጃ እርስ በእርስ ተጠያይፈን እርስ በርስ ተጨካክነን እርስ በእርስ እየተሳደድን ምን ያስተሳስረናል ???

እርስ በእርስ በሚበላላ ህዝብ ውስጥ ያለች አገርን እንደምን ማፍቀር ይቻላል? ?? ምኗ ይናፍቃል ??

ከዚህ በኋላ የትኛው አገዳደል ፤የትኛው አበዳደል ፤የትኛው ግፍ ያስበረግገን ይሆን ??
የቱም !

ይታክታል!!! እውነት ይታክታል!!!!!
#ልብ_ይስጠን_ይስጣቸው!::


@Yewqetabugida67
189 views16:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-19 22:04:29
የፍቅር ቦታው ልብ ነው። ልብ ደግሞ ንፁህ ወርቅ ነው። ፈጣሪ በመለኮታዊ ሃይሉ ያነጠፈው፤ ያብረቀረቀው ወርቅ ቢኖር ልብ ነው።

የፍቅር ፀዳል ውበት የሚንፀባረቀው በልብ መስታወት ውስጥ ነው። ነፀብራቁ፣ ደግሞ፣ በፈጣሪ ፍቅር፣ ይገለፃል።

#ወዳጄ_ልብ_እንዳይቆሽሽ_ጠብቀው

@Yewqetabugida67
202 views19:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-19 21:17:27 ስጦታው

ከአንድ ሰው በራፍ ላይ ቁጭ ብሎ ድንች የሚሸጥ ምሲኪን ሰው ነበረ። የቤቱ ባለቤት ሁሌም ወደ ውጪ ሲወጣ ይህንን ምስኪን ሰው ይመለከተው ነበረ። ቀኑን ሙሉ ብርድና ጸሀይ እየተፈራረቀበት ኑሮን ለማሸነፍ መድከሙ ስላሳዘነው በአቅሙ ሊረዳው ወሰነ። ነጋዴው አንዷን ድንች በ50 ሳንቲም ነበር የሚቸረችረው። ታዲያ ይህ ሰው ምስኪኑን ነጋዴ ለመርዳት በማሰብ በየቀኑ የአንድ ድንች ዋጋ እየሰጠው ለመሄድ ወሰነ። በየቀኑ 50 ሳንቲሙን እየሰጠው በአንጻሩ ምንም ድንች ሳይቀበል ይሄዳል። ከብዙ ጊዜ በኋላ ይህ ሰው እንደለመደው 50 ሳንቲሙን አኑሮለት ጉዞውን ቀጠለ። ድንገት ከኋላው “ጌታዬ” የሚል ጥሪ ይሰማል። ዞር ብሎ ሲመለከት ምስኪኑ ነጋዴ ነበር በሩጫ የደረሰበትና የጠራው። ሰውየው በፈገግታ “ከስንት ጊዜ በኋላ ለምን በቀን በቀን 50 ሳንቲም በነጻ እየሰጠሁ እንደማልፍ ልጠይቀኝ ነው ያስቆምከኝ?” አለው ነጋዴው ግን እያለከለከ “አይደለም ኸረ” ሲል መለሰ። ይሄኔ ሰውየው ግራ ገብቶት “እና ለምን አስቆምከኝ?” ቢለው “የድንች ዋጋ 75 መግባቱን ልነግርዎት ነው፤ እናም ስሙኒ ይጎድላል” አለው አሉ።

ይህንን ታሪክ ቁልጭ አድርጎ የሰው ልጅን የአልጠግብ ባይነትና ያለማመስገንን ባህሪ የሚያንጸባርቅ ነው። ልክ እንደዚህ ምስኪን ነጋዴ ነጻ በሚሰጠን ነገር ላይ እንኳን እንደራደራለን። የእኛ ባልሆነው ሀብት እንሟገታለን። በቸርነት በተሰጠን ነገር ሁሉ ይበልጥ እንጠይቃለን። ሃምሳ ሳንቲም ለምን በነጻ ተሰጠኝ ሳይሆን ለምን ስሙኒ ጎደለ የሚል አመለካከት ስላለን እኮ ነው አብዛኛዎቻችን ባለን ነገር መደሰት የሚያቅተን።

ብዙ ጊዜ ከፈጣሪ ጋርም ሆነ በየእለት ኑሮዋችን በነገሮች ላይ የምንደራደረው ልክ እንደዚህ ምስኪን ነጋዴ ነው። በነጻ የሚሰጠንን 50 ሳንቲም ሳይሆን የኑሮዋችንን ዋጋ እራሳችን ተምነን ቀሪው ጎደለ ብለን እንሟገታለን። ስዎች የሚሰጡንን ነጻ ፍቅር፤ ነጻ ክብር፤ ነጻ እምነት ዋጋ የማንሰጠው ቀሪውን ስሙኒ ስለምናስብ ነው። እኛ በባህሪያችን ነጻ የሆነን ነገር ዋጋ አንሰጠውም እንደውም አንድ ተናጋሪ ሰዎች አይምሮዋችንን በደንብ የማንጠቀምበት ነጻ ስለተሰጠን ነው ሲል ሰምቸው ግርምት ጭሮብኝ ነበር። እውነት እኮ ነው፤ የላፕቶፓችንን ያህል አይምሮዋችንን ዋጋ አንሰጠውም። ላፕቶፓችንን ቫይረስ እንዳይነካው የምንጠነቀቀውን ያህል አይምሮዋችን እንዳይበከል አንጠነቀቅም።የሚያስደንቀው ግን የሰው ልጅ በምንም ያህል ገንዘብ ሊገዛቸው የማይችላቸው ሀብቶቹ በሙሉ በነጻ የሚያገኛቸው ናቸው።

በ50 ሳንቲሙ ያልተደሰተና ያላመሰገነ ሰው ስሙኒ ቢጨመርለት ምን ዋጋ አለው? በየቀኑ የሚቸረን 50 ሳንቲም ከበቂ በላይ ነው፤ አንዳንዴ ስሙኒው ይቀራል ብለን ሰጪውን ባናስቀይም መልካም ነበር፤ ነገር ግን ሰው ነን!!! ብዙ ጊዜ ደስታችንን የሚነጥቀን የ “ስሙኒ ይቀራል” አይነት አመለካከታችን ነው። የተሰጠንስ 50 ሳንቲም? የተሰጠን ነጻ ፍቅር፤ ነጻ ክብር፤ ነጻ እምነት፤ ነጻ ጤንነት፤ እነዚህ ሁሉ የ ሰጠንን ፈጣሪ እናመስግነው እንጂ አናማረው ::

@Yewqetabugida67
188 views18:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-18 01:12:28
ልብ

#በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የልብ_ቅርፅ ምልክት የፍቅር ምልክት ተደርጎ መወሰድ የጀመረው በ1250ዎቹ የነበረ ሲሆን ዛሬም ድረስ ከልብ ለመነጨ ፍቅር ወካይ ነው፤ይህ ግን በሞሮኮ አይሰራም በሞሮኮ የፍቅር ምልክት በልብ ሳይሆን በጉበት ይወከላል። ከልቤ እወድሃለው/ሻለሁ ከምትለው/ላት ከጉበቴ እወድሃለሁ/ሻለው ብትል የበለጠ ታማልላለህ ይህ ባይሆን ግን #ከልቤ ምናምን ካልክ ልብ አውልቅ ተብለህ/ሽ ትደቋሳለህ/ሽ፡፡


@Yewqetabugida67
160 views22:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-17 22:04:08 #በዓለም_ላይ_3_ዐይነት_ሰዎች_አሉ!

1, የተቀመጡ ሰዎች
2, የተሰረቁ ሰዎች
3, ባለ ራዕይ ሰዎች

#የተቀመጡ_ሰዎች

የሚባሉት ህይወትን በ TV ነው የሚያዩት፣ ትችትን ፣ ነቀፌታን ፣ተግዳሮት የማይፈልጉ ፣ አሸናፊነትንም ሆነ ሀላፊነትን አይወዱም ባአጠቃላይ [Challenge Life] አይፈልጉም።

#የተሰረቁ_ሰዎች

ሌላዉን መስሎ መኖር ምኞታቸው ነው። የራሳቸው የሆነ አቋምም ሆነ ማንነት የላቸውም። የተሰረቀ ሰው ራሱን ከሌላ ጋር እያወዳደረ ነው የሚኖረው።

#ባለራዕይ_ሰዎች

ነፃ እና ተፈጥሯዊ ሰዎች ናቸው። የበታችነት ስሜት አይሰማቸውም!! መተባበር፣ ፍቅር እና ማህበራዊ ተቆርቋሪነት መገለጫቸው ነው።እነዚህ ሰዎች በቅድሚያ፦
ማህበረሰቡን
ሲቀጥል ቤተሰባቸው
በመጨረሻ ራሳቸዉን የሚያስከትሉ ናቸው።

እንዲህ አይነት ሰው ካርታውን ያለማጭበርበር የሚጫወት እንጂ የሚያሸንፍ አይደለም።

ሁሉም ጥሩ ይሆናል ዋናው ነገር ሰላምና ጤና

@Yewqetabugida67
162 views19:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-17 22:01:21 . #ድንቅ_እናት

ባለቤቷ ከሞተ በኋላ ልብሱን ቁም ሳጥን ውስጥ አንጠልጥላው በየጊዜው ገንዘብ ታስቀምጥበታለች ። ልጆቿ ለተለያየ ጉዳይ ወጪ ሲጠይቋት ሂዱ ቁም ሳጥን ውስጥ
ከአባታችሁ ደረት ኪስ ውሰዱ ትላቸዋለች "
እነሱም የሚያስፈልጋቸውን ብቻ ቆጥረው ከአባታቸው ኪስ ይወስዳሉ ከዕለታት አንድ ቀን ልጆቹ እናታቸውን ለምን እንደዚህ እንደምታረግ ሲጠይቋት የአባታችሁ ሩህሩህነትና ለጋስነት እንድታውቁትና አባታችሁ እዛም ሆኖ ለእናንተ እንደሚጨነቅ እንድታውቁ (አባት የሞተበት ) ነን ብላችሁም እንዳታስቡ ለማስታወስ ነው!::

#አስተዋይ_እናት_ትምህርት_ቤት_ናት_የምንለው_ለዚህ_ነው!::


@Yewqetabugida67
149 views19:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-01 16:37:55
#መልካም_የድል_በዓል_ይሁንልን!
212 views13:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-27 22:26:25
ምን መሰላችሁ በዓለማችን በዶክተሮች የጽሁፍ አጣጣል በዓመት ከ6000 ሰው በላይ ይሞታል፡፡ ለምን ቢሉ በታዘዘለት የመድኃኒቱ ዓይነትና ስም በፋርማስቲቶች በትክክል አለመነበብ አለመለየት/አለመታወቁ/::
215 views19:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-27 22:15:34 #ልጄ
ሁሌም በተወሰደብን ልክ ሳይሆን በቀረን ልክ እናስብ
አለም በሮጡላት ልክ ትፋለች።

ጊዜ መሰላል ነው
የወጡት ሲወርዱ....የወረዱት ሲወጡ
ይገናኛሉ።

የሚያድግ ልጅ አይጥላህ
የሚሞት ሽማግሌ አይርገምህ ።

በሰው ላለመጠላት ሰው አትጥላ
ሰው ሰው መሆኑን አትርሳ ።

ሁሉም ሰው በቆሰለው ልክ ነው
ሚደማው ።

ካለፈው ትላንት ይልቅ
የሚመጣው ነገ የተሻለ ነው።

በህይወትህ ውስጥ ስለ ምንም ነገር መቀደድ
አትጨነቅ መልሰህ ለመስፋት አስብ።

የሰው ልጅ ባህሪው ያለፈው ህይወቱን ይመስላል። እንዴት ቢሉ ራስዎት ይጠይቁ

@Yewqetabugida67
189 views19:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-20 17:44:46 ከእለታት ሁለት ቀን እንዲህ ሆነ
አንዲት ዝሆን እና ውሻ በተመሳሳይ ጊዜ አረገዙ።
ከሦስት ወራት በኋላ ውሻይቱ ስድስት ቡችላ ወለደች።
ከስድስት ወራት በኋላ ደግሞ እንደገና ውሻይቱ አረገዘች።
በዘጠኝ ወር ውስት እንደገና ስድስት ቡችላ ደገመች።
እንዲህ እያለ ጉዳዩ ቀጠለ።
በአስራ ስምንተኛው ወር ውሻይቱ ለዝሆኗ ጥያቄ ጠየቀች።
"እርግጠኛ ነሽ እርጉዝ ነሽ? ሁለታችንም በተመሳሳይ ጊዜ
እርጉዝ ነበርን እኔ ለሦስተኛ ጊዜ ነፍ ቡችላ ወለድኩ።
እንደምታያቸውም ልጆቼ አድገውም ትላልቅ ውሻ ሆነዋል
ነገር ግን አንቺ እስካሁን እርጉዝ ነሽ ምን እየተካሄደ ነው?"
ብላ ውሻይቱ ዝሆኗን በጥያቄ አጠደፈቻት።
ዝሆኗም ረጋ ብላ መመለስ ጀመረች "የሆነ ነገር እንዲገባሽ
እፈልጋለው። እኔ የተሸከምኩት ነገር ቡችላ አይደለም። እኔ
የተሸከምኩት ዝሆን ነው። እሱንም በሁለት ዓመት ውስጥ
አንዴ ብቻ ነው መውለድ የምችለው። እና ግን የወለድኩት
ዕለት አንዴ ብቻ መሬቱን ሲረግጠው ምድር ሁሉ
ይሰማታል። የኔ ልጅ መንገድን ሲያቋርጥ የሰው ልጅ ቆሞ
በአድናቆት ያየዋል። እናም ምን ልልሽ ፈልጌ መሰለሽ እኔ
የተሸከምኩት ነገር በጣም ጠንካራ እና ታላቅ የሆነ ነገር
ስለሆነ ፅሞና እና ጥንቃቄ ያስፈልገዋል፡፡"
=============
እናም ጌታው ከጎንህ ያለው ሰው ሺ ጊዜ ውጤት ያመጣ
ቢመስልህ የራስህ እቅድ እና ውጥን ላይ ተስፋ
እንዳትቆርጥ። በፍፁም በሌላ ውጤት እንዳትቀና።
ሁሌም በልብህ "የኔ ጊዜ ይመጣል" በል ጊዜው ደርሶ
የአንተ ጊዜ መሬት ሲረግጥ ያኔ አንተን አያድርገኝ ልክ
እንደዝሆን ልጅ መንገዱን ሲያቋርጥ ሰው ቆሞ በአድናቆት
እንደሚያሳልፈው ያኔም ሰው ሁሉ ለአንተ አድናቆት ይቆማል። ለአንተ የፈለከው ነገር በቶሎ በቶሎ ብታገኝም እኔም የፈለኩት ነገር አሻሽሎ አምሮና አስተካክሎ ስለሚሰጠኝ ነው እንጂ ረፍዶበት አቅቶትም እንዳይመስልህ አይደለም ፈጣሪ ለልጁ ዘይግይቶ ወይም አርፍዶ አያውቅምና፡፡ አንድ አባባል አለች ሁሌም ደስ ምትለኝ ፦ #እናት ለህጻን ልጇ ሥጋ ከእነ አጥንቱ አትሰጠውም ይወጋዋል ብላ ስለምታስብ መርምራ ወይም አኝካ ነውና ምትሰጠው፣ አምላክም ግን ከዚህም በላይ ለልጆቹ ያማረውን የተሻለውን ስለሚሰጥ ፈልጎ እንጂ ያልበሰለ ፍሬ አድሎ አያውቅም፡፡
ብሩህ ቀን ይሁንላችሁ !
#እውቀት አቡጊዳ
215 views14:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ