2021-07-10 07:17:26
#ፈጣሪ_አህያን_ፈጠረና_እንዲህ_አለው….
አህያ ትሆናለህ፡፡ ሸክሞችን በጀርባህ በመሸከም ፀሐይ ወጥታ እስክትጠልቅ ድረስ ያለመታከት ትሰራለህ። የምትመገበው ደግሞ ሳር ነው፡፡ ምንም አይነት ኢንቴለክት(የማሰብ፣የማመ ዛዘን ችሎታ) የለህም፡፡ እናም
50 ዓመት ትኖራለህ፡፡
አህያው እንዲህ ሲል መለሰ…
አህያ እሆናለሁ ችግር የለውም ነገር ግን
50 ዓመት በጣም ብዙ ነውና ሃያውን ብቻ ስጠኝ፡፡ እግዚያብሔርም የፍላጎቱን ሰጠው፡፡
✰ ✰ ✰
#ፈጣሪ_ውሻን_ፈጠረና_እንዲህ_አለው….
የሰውን ልጅ ቤት ትጠብቃለህ፡፡ የሰው ልጅም እውነተኛ ጓደኛ ትሆናለህ፡፡ ከጌታህ የሚጣልልህን ፍርፋሪ ትመገባለህ፡፡ እናም
30 ዓመት በሕይዎት ትኖራለህ፡፡ ውሻም ትባላለህ፡፡
ውሻው ሲመልስ…
ጌታየ
30 ዓመት እጅግ ብዙ ነው አስራ አምስቱ ዓመት ይበቃኛል አለ፡፡ ፈጣሪም የፍላጎቱን ሰጠው…
✰ ✰ ✰
#ፈጣሪ_ዝንጀሮን_ፈጠረና_እንዲህ_አለው….
ዝንጀሮ ትሆናለህ፡፡ በዛፎች ቅርንጫፍ ወዲያና ወዲህ እየተንጠላጠልክ ትርኢት ትሰራለህ፡፡ በድርጊትህም አስገራሚ ትሆናለህ እናም
20 ዓመት ትኖራለህ፡፡ ዝንጀሮው ሲመልስ…
ሃያ ዓመት መኖር በጣም ብዙ ነውና አስሩ ብቻ ይበቃኛል አለ፡፡ ፈጣሪም የሚኞቱን ሰጠው፡፡
✰ ✰ ✰
#በመጨረሻም_ፈጣሪ_አዳም_ጋ_ደረሰ__ፈጠረና|እንዲህ አለው….
የሰው ልጅ ትባላለህ፡፡ በምድር ላይ ካሉት ፍጡራን አመዛዛኝ፣ አሳቢና ምክኒተዊ ፍጡር አንተ ብቻ ነህ፡፡ በሌሎች ፍጡራን ላይ ለመንገስም የማሰብ ችሎታህን ትጠቀማለህ፡፡ በሌሎች ፍጡራን ላይ ነግሰህም
20 ዓመትን ትኖራለህ አለው። የሰው ልጅ የተሰተውን የማሰብ ችሎታው ተጠቅሞ ሲመልስ…
ጌታዬ እሺ! የሰው ልጅ እሆናለሁ፡፡ ነገር ግን ሃያ ዓመት መኖር እጅግ ሲበዛ ትንሽ ነው፡፡ ስለሆነም ሠላሳ ዓመት አህያው የተቃወመውን፣ አሥራ አምሥት ዓመት ውሻው አልፈልገውም ያለውን እናም ደግሞ አስሩን ዓመት ዝንጀሮው የማይፈልገውን ስጠኝ ሲል ጥያቄውን አቀረበ (ከራሱ ጋር የሌሎችን ደማምሮ
75 ዓመት አደረሰው)፡፡ ፈጣሪም የፍላጎቱን ሰጠው…
#እናም የሰው ልጅ ሕይዎት ከዛን ጊዜ ጀምሮ
20ውን ዓመት #እንደ_ሰው ይኖራል (ሳያገባ ትዳር ሳይመሰርት ለአንድ ሆዱ ሲኖር ማለት ነው)፡፡
ከዛ በኋላ አግብቶ ትዳር ሲመሰርትና የቤተሰብ ኃላፊ ሲሆን
30ውን ዓመት ልክ #እንደ_አህያው የአህያውን ሚና ወስዶ ይኖራል፡፡ የቤተሰብ ኃላፊነቱን ይሸከማል፤ የአባወራነቱን ኃላፊነት ለመወጣትም ቀን ከሌት ያለመታከት ይሰራል፡፡ ቀጥሎም ልጆቹ እያደጉ ሲሄዱ
15ቱን ዓመት ልክ #እንደ_ውሻው አይነት ኑሮን ይመራል፡፡ ቤቱን ይጠብቃል ይንከባከባል፣ ከልጆቹ ተርፎ የሚሰጠውንም ይበላል፡፡ አርጅቶ እየሸመገለ በሄደ ጊዜም ጡረታ ይወጣና
10ሩን ዓመት #እንደ_ዝንጀሮው አኗኗር ዘይቤ ይኖራል፡፡ ልጆቹን አጎራብቶ ከአንደኛው ቤት ወደ ሌላኛው ቤት በመዘዋወር የልጅ ልጆቹን በማጫወት፣በማዝናናት ያለፉ ዘመናትን ታሪክ በማውራት ያሳልፋል፡፡
#ሕይዎት_ማለት_ይች_ናት!
@Yewqetabugida67
222 views04:17