የሰርጥ አድራሻ:
ምድቦች:
ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች:
239
የሰርጥ መግለጫ
በቻናላናችን የሚሰጡ ነገሮች
መንፈሳዊ ትምህርቶች
መንፈሳዊ ምክሮች
መንፈሳዊ መዝሙር
መንፈሳዊ ጥያቄዎች
መንፈሳዊ ስዕልዎች
በየለቱ ስንክሳር
Ratings & Reviews
Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.
5 stars
0
4 stars
1
3 stars
0
2 stars
0
1 stars
1
የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች
2022-06-15 17:53:21
ስንክሳር ዘወርኀ ሰኔ ፰፩ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሰኔ ስምንት በዚች ቀን አምላክን የወለደች በሁለት ወገን ድንግል የሆነች የእመቤታችን ማርያም የታወቀችው በውኃ ምንጭ ዘንድ ያለች የቤተክርስቲያንዋ ቅዳሴ ነው።
እርሱም ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእርሷ ጋር ወደ ግብጽ አገር ተሰዶ ሲመለስ ያፈለቀው የተባረከ መታጠቢያ ነው፤ ይህም እንዲህ ነው ለጻድቁ ዮሴፍ የእግዚአብሔር መልአክ በሕልም ተገልጾለት ሕፃኑንና እናቱን ይዘህ ወደ ግብጽ አገር ሒድ አለው።
ዮሴፍም ነቅቶ ተነሣ ክብር ይግባውና ሕፃኑን ጌታችንን እናቱንና እኅቷ ሰሎሜን ይዞ ወደ ግብጽ አገር ሔዱ በዚያም በውስጧ ባሉ በብዙ አገሮች እየዞሩ ሦስት ዓመት ከስድስት ወር ኖሩ።
ሄሮድስም ከሞተ በኋላ የእግዚአብሔር መልአክ ለዮሴፍ ሁለተኛ ተገለጠለት ወደ እስራኤልም አገር ሕፃኑንና እናቱን ይዞ እንዲመለስ አዘዘው፤ በሚመለሱም ጊዜ ወደ መዓልቃ ደረሱ ከዚያም ወደ መጣርያ አገር ደረሱ ይቺም ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ውኃ ያፈለቀባትና የመታጠቢያ ቦታ የሆነች ናት እርሷም እስከ ዛሬ አለች ሰዎችም ከአገሩ ሁሉ ከየነገዱ ሁሉ መጥተው አምላክን ወደ ወለደችና በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ ወደ ጸናች ቅድስት ድንግል እመቤታችን ማርያም ይለምናሉ ከተባረከውም የውኃ ምንጭ ታጥበው ከደዌያቸው ሁሉ ይድናሉ በዛሬዪቱ ቀን ከከበረች ቤተ ክርስቲያንም ይባረካሉ።
እርሷን እመቤታችንን ለመረጣትና ለወደዳት በሥጋም እናቱ ላደረጋት ስለርሷም ዘመድ ለሆነንና ወደርሱ ላቀረበን ወራሾቹም ላደረገን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን።
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ ለማግኘት //
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
55 views14:53
2022-06-15 08:13:08
#ወዳጆቼበዕውቀትና የሥራ ልምድ የተሻለ ከሚባል ሰው ጋር አብሮ መሥራት ያስደስትህ #ይሆናል። በዓለም አቀፍ ደረጃ ስመ ጥር ከሆነ ባለሙያ ጋር መሥራት ደግሞ ያለውን ስሜት በቃላት ለመግለጽ ሊከብድህ ይችላል። ነገር ግን #በእግዚአብሔር ቤት የሚያገለግል ሰው ከማን ጋር የሚሠራ #ይመስልሃል? #ሐዋርያው እንዲህ ሲል ይመልሳል "ከእርሱ(እግዚአብሔር) ጋር አብረን የምንሠራ ነንና"። (1ኛ ቆሮ 3፥9) ለጥበቡ ስፍር ቁጥር ከሌለው፣ ሁሉን ከሚችልና በሁሉ ካለ #አምላክ ጋር አብሮ #ከመሥራት የሚበልጥ ክብር ከየት ይገኛል?! የዕውቀት ተከፍሎ ካለበት፣ ስሕተት ሊገኝበት ከሚችል ደካማ ሰው ጋር አብሮ መሥራት ይህን ያህል #የሚያኮራ ከሆነ፣ ሁሉን ከሚያውቅ ፈጽሞ ከማይሳሳት ኃያል #አምላክ ጋር "አብሮ ሠራተኛ መሆን" ምን ያህል እጥፍ ድርብ #ያኮራ_ይሆን?! #_ሰናይ_ቀን
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ ለማግኘት //
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
50 views05:13
2022-06-14 08:06:36
#ሥላሴ_ኃይሌ መመኪያዬ ነው
በሥላሴ ስም ጠላቴ ሰይጣንን እክድዋለሁ
እግዚአብሔር ከዓለም በፊት በመንግሥቱ ነበረ እግዚአብሔር #በሦስትነቱ እግዚአብሔር በመለኮቱ አለ ከጎኅና ከጽባሕ ከብርሃናት መመላለስም በፊት እግዚአብሔር በመንግስቱ ነበረ፡፡
{ቅዳሴ ዲዮስቆሮስ}
#ሥላሴ_ማለት ሠለሰ ሦስት አደረገ ከሚለው የግዕዝ ግሥ የተወሰደ ሲሆን ትርጓሜውም #ሦስትነት ማለት ነው፡፡ #ሥሉስ_ቅዱስ ማለት ደግሞ ልዩ ሦስት ማለት ነው፡፡ #አብ ፍጹም መልክእ ፍጹም ገጽ ፍጹም አካል አለው፣ #ወልድም ፍጹም መልክእ ፍጹም ገጽ ፍጹም አካል አለው፣ #መንፈስቅዱስም ፍጹም መልክእ ፍጹም ገጽ ፍጹም አካል አለው።
#የእግዚአብሔር የአንድነትና የሦስትነት ባለቤት ስለሆነ #ሥላሴ ይባላል ።
#የአብረሃሙ_ስላሴ ከክፉ ይጠብቀን
ሀሳብ ምኞታችን ተሳክቶ በደስታ እንድንኖር ይርዳን አሜን
#___ሰናይ____ቀን
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ ለማግኘት //
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
49 views05:06
2022-06-11 19:41:59
"… ከዛሬው ቅዱስ ጋብቻው በፊት…
• ቃና ዘገሊላ
• ሕማማት
• ኢትዮጵያዊ ጃንደረባ
• የብርሐን እናት
…ተብለው በስሙ የሚጠሩ ልጆችን ብቻውን አምጦ የወለደው ዲን ሔኖክ ኃይሌ በዛሬው ዕለት ደግሞ ከወ/ሪት ሳምራዊት ደመቀ ጋር ብፁዓን ሊቃ ነጳጳሳት፣ አባቶች ካህናት፣ ወንድሞች ዲያቆናት፣ መምህራነ ወንጌል እና ዘማርያን፣ እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በቅደስት ቤተ ክርስቲያን ዓለሙ ሁሉ እያየው አምላካዊና መለኮታዊ ሕግ በይፋ በቅዱስ ቁርባን አትሞ በመሃላ ፈጽሞታል። “ስለዚህ ሰው አባቱንና እናቱን ይተዋል፥ በሚስቱም ይጣበቃል፤ ሁለቱም አንድ ሥጋ ይሆናሉ።” ዘፍ 2፥24።
"…መልካም ጋብቻ…!!
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ ለማግኘት //
https://t.me/manew_maryamn_tewyemilegn
669 viewsedited 16:41
2022-06-11 13:15:38
በዛሬዋ ዕለት ሰኔ ፬ ፳፻፲፬ዓ.ም. ጋብቻኽን በቅድስት ቤተክርስቲያን ሥርዓት የፈጸምከው - እናት ቤተክርስቲያንን ለበርካታ ዓመታት ያገለገልከው አሁንም እያገለገልክ የምትገኘው ሊቁ መምህራችን ፣ወንድማችን ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ እና እህታችን ሳምራዊት
የፈጸማችኹትን ጋብቻ፤
የይስሐቅንና የርብቃን ጋብቻ የባረከ አምላክ፤ የትዳር ሕይወታችኹን ይባርክላችኹ፥ ያጣምራችኹ፥ ያዋሕዳችኹ
እግዚአብሔር አምላክ በሕይወታችኹ ሞገስ ይኾናችኹ ዘንድ በፍቅርና በጤና ይባርካችኹ ዘንድ መልካም ምኞታችን ነው!
#መምህራችን_መልካም_ጋብቻ
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
54 views10:15
2022-06-11 07:43:49
"አንድ ወንድና አንዲት ሴት የተጋቡት (የሚጋቡት) መንግሥተ ሰማያትን ለመውረስ በሚያደርጉት ጉዞ ላይ አብረው እየተጋገዙ ለመሔድ ከኾነ፥ ትዳራቸው ታላቅ የኾነ ደስታን ያመጣላቸዋል፡፡"
#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
#መምህራችን_መልካም_ጋብቻ @Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
53 views04:43
2022-06-10 19:39:07
በክፉ ቀን ወዳጅ ሰው ባይኖር
መልካም የነበረው ፊቱን ቢያዞር
የቀረበ ሲርቅ ያጀበኝ ቢበተን
ቀና ብየ ሳይ ግን አላጣውም አንተን
በደስታም ይሁን በሀዘን፣በማግኘትም ይሁም በማጣት: በክፉም ይሁን በመልካም ቀን አብሮነቱ የማይለይ፣ ሁኔታን የማያይ፣ ወረት የሌለበት እውነተኛና ታማኝ ወዳጅ እግዚአብሔር ብቻ ነው።
በሁሉም ሁኔታ ውስጥ አብሮነቱ ያልተለየን አምላክ ይመስገን
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ ለማግኘት //
https://t.me/manew_maryamn_tewyemilegn
1.0K views16:39
2022-06-10 07:33:51
#
__ወዳጄ
ከፍ ከፍ ትል
ዘንድ #ትሑት ሁን፤ ባለጸጋ ትሆን ዘንድ #ድኻ ሁን፤ ትጠግብ ዘንድ #ረኃብን ውደዳት። ጤነኛ ትሆን ዘንድ የመብል ሸክምን አቅልል፤ ትከብር ዘንድ #ተዋረድ፤ ደስ ይልህ ዘንድ #አልቅስ፤ ትኖር ዘንድ #ሙት፤ ትበራ ዘንድ ትጋ። ትድን ዘንድ በማስተዋል #ጸልይ፤ ኃጢአትህን ይቅር ይልህ ዘንድ አብዝተህ #ጹም፤ ታገኝ ዘንድ #ፈልግ፤ ታተርፍ ዘንድ ለመነገድ ተፋጠን። ባለጸጋ ትሆን ዘንድ በብርሃናውያን መንገድ ትመላለስ ዘንድ #መስቀልህን ተሸከም፤ ሥጋህን ጥላት #ነፍስህን አንጻት።
#_ሰናይ_ቀን
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ ለማግኘት //
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
54 views04:33
2022-06-09 07:48:39
"እውነት እላችኋለኹ፥ ከሴቶች ከተወለዱት መካከል ከመጥምቁ #ዮሐንስ የሚበልጥ አልተነሣም" (ማቴዎስ ፲፩፣፲፩)
“የቅዱሳኑ ሞት በእግዚአብሔር ፊት #የከበረ ነው።” መዝ.፻፲፭/፻፲፮፡፲፭
የዛሬዋ ዕለት የጌታ ባሪያ፣ #የትሕትና መምህር፣ ካህን፣ ነቢይ፣ ባህታዊ ፣ የበረሃ ምርኮኛ #መጥምቀ_መለኮት ቅዱስ ፍልሠቱ የምትታሰብባት ናት!
ከዚኽ ደገኛ ነቢይ በረከት ይክፈለን! ሀገራችንንም እኛንም በእውነት ይማረን - አሜን!
#_ሰናይ_ቀን
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ ለማግኘት //
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
55 views04:48
2022-06-08 18:46:49
❖ #ማርይስሐቅ_እንዲህ_ይላል
#ለመጸለይ_ስትቆም_በእሳትፊትእንደቆምክያልበጥንቃቄ_ይሁን"
❖ #የአባቶች_አባት_አብርሃምም
"እኔ አፈርና አመድ ስሆን ከጌታዬ ጋር እነጋገር ዘንድ እነሆ አንዴ ጀመርሁ" አለ
ዘፍ 18፥27
❖ #ስለዚህ_አንተም_ጌታሆይ_በፊትህ_ለመቆም_እኔማነኝ? በአንተ ፊት የሚቆሙ መላእክት፣ ኪሩቤል፣ ሱራፌል፣ ስፍር ቁጥር የሌላቸው ኃይለ ሰማያት ናቸው፤ እንዴት ራሴን ከእነዚህ ቅዱሳን ጋር አስተካክለሁ?" እያልክ በትህትና ጸልይ!
#ብፁእ_አቡነ_ሺኖዳ_ሣልሳዊ
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ ለማግኘት //
https://t.me/manew_maryamn_tewyemilegn
1.4K views15:46