Get Mystery Box with random crypto!

Teddy Afro

የቴሌግራም ቻናል አርማ teddyafronet — Teddy Afro T
የቴሌግራም ቻናል አርማ teddyafronet — Teddy Afro
የሰርጥ አድራሻ: @teddyafronet
ምድቦች: ሙዚቃ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 12.77K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ በቴዲ አፍሮ አድናቂዎች የሚመራ የTelegram ድህረ ገፅ ነው። በFacebook በInstagram እንዲሁም በዚሁ በTelegram ሰፋ ያለ ተከታዮችን ያፈራው "Teddy Afro net" ሁሌም ስለቴዲ አፍሮ በታማኝነት ያገለግላሉ። በሁሉም የመገናኛ ብዙሃን /ድህረ-ገፆች/ ትልቅ ድርጅት ሆነን ስለምንወደው #ቴዲ_አፍሮ ለዓለም ህዝብ በቂ መረጃ ተደራሽ እናደርጋለን።
Admin @PoetTataafro

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2022-08-10 19:42:28
ቴዎድሮስ እሥኪ-ነግሥ የተሰኘውን መጽሐፍ በተጨማሪ መደብሮች እና ከተሞች ላይ ቢቀርብ ብላችሁ በጠየቃችሁን መሰረት በአዲስ አበባ፣ በባህርዳር እና በጎንደር ከዚህ በታች በተጠቀሱት የስልክ አድራሻዎች ማግኘት የምትችሉ መሆኑን ለመጠቆም እንወዳለን። በተጨማሪም በሌሎች ከተሞች ላይ የምትኖሩ በፖስታቤት መላክ ስለጀመርን ለበለጠ መረጃ ብለን በጠቀስነው ስልክ ብትደውሉ ያላችሁበት ከተማ ድረስ የሚላክ መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን።

መጽሐፉን ከዚህ በታች በተጠቀሱት መደብሮች እና ከተሞች በጊዚያዊ ማግኘት ይችላሉ።

ጃፋር መጽሐፍ ቤት /አዲስ አበባ/

ስታዲየም ነጃ መጽሐፍ መደብር 0910990259 /አዲስ አበባ/

መሳለሚያ ሆናልያት ህንፃ ቢሮ ቁጥር 156 ተኬ ማን ፕሮሞሽን 0911518012 ወይም 0921935862 /አዲስ አበባ/

አራት ኪሎ 0901197837 /አዲስ አበባ/

በክልል ከተሞች

ጎንደር +251912426975

ባህርዳር +251930364060

ደብረ ማርቆስ +251980535473

#ለበለጠ መረጃ 0975550865 ይደውሉልን።
5.7K viewsedited  16:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-09 09:33:49
Twitter ላይ በታዋቂ ሰዎች ስም በተከፈቱ ሀሰተኛ የTwitter ገጾች ላይ ቴዲ አፍሮን ጨምሮ በሌሎች የአገራችን ታዋቂ ሰዎች ላይ የሚደረጉ የጥላቻ ንግግሮች ተጠናክረው እየቀጠሉ ይገኛሉ። እነዚህ ነገሮች ሀሰት መሆናቸውን በስፋት ተደራሽ ለማድረግ እና እነዚህን የስም አጠልሺ ገጾችን ለማዘጋት ሁሉም ሰው የበኩሉን ሊወጣ ይገባል።

የኛን የTwitter ገጽ ይቀላቀሉ።

https://twitter.com/teddyafro_net
4.7K views06:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-01 19:46:48 https://vm.tiktok.com/ZMNqkkjyY/?k=1
5.7K views16:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-29 12:58:26
‹‹አቡነ ጴጥሮስ የተገደሉ ዕለት እዚያው ነበርኩ፡፡ መጀመሪያ በእጃቸው ይዘውት የነበረውን መጽሐፍ ቅዱሳቸውን ተሳለሙት። ቀጥለውም በያዙት መስቀል አማትበው ሕዝቡን ባረኩ። የኪሳቸውንም ሰዓት አውጥተው ካዩ በኋላ መልሰው ከኪሳቸው ከተቱት። ወዲያው ወታደሮቸ በሩምታ ተኩሰው ገደሏቸው። ይህ እንደሆነ አስገዳዩ ኮሎኔል ተመልካቹን ሕዝብ አጨብጭቡ ብሎ አዘዘና ተጨበጨበ። ማታ ከአስገዳዩ ኮሎኔል ጋር ተገናኝተን ስንጫወት ‹በዚህ ቄስ መገደል እኮ ሕዝቡ ተደስቷል› አለኝ። ‹እንዴት?› ብለው ‹አላየህም ሲያጨበጭብ?› አለኝ። ‹ባታውቀው ነው እንጂ የሕዝቡ ባሕል ሲናደድም ያጨበጭባል› አልኩት። ‹እንዴት?› ቢለኝ እጄን አጨብጭቤ አሳየሁት።››

አቡነ ጴጥሮስ ሲገደሉ በቦታው ሆነው የተከታተሉት ሙሴ ፓይላክን የተባሉ ግለሰብ በወቅቱ የነበረውን ሁኔታ ለጳውሎስ ኞኞ ከነገሩት የተወሰደ።

ሀገራችን ኢትዮጵያ የቆየችው በዕልፍ መስዋዕትነት ነው። በትላንቱ መስዋዕትነት ያሁኑ ትውልድ በሰላም እና በተድላ ይኖር ዘንድ መብት ነበረው። ምክኒያቱም በቂ የሆነ መስዋዕትነት የተከፈለለት እድለኛ ትውልድ ስለሆነ። ዳሩ ግን ጽድቁ ቀርቶብኝ በቅጡ በኮነነኝ እንዲሉ ሆነና ነገሩ ዛሬም ከግማሽ በላይ በሆነው ልባችን መከራ አዝለን እንኖራለን። በአመት ሺ ጊዜ አዝነን አንድ ጊዜ ብቻ ደስ እንሰኛለን። እሱም ጣዕሙ እንደቀድሞ በሆነልን እያልን....

ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!

ስለከበረው መስዋዕትነታቸው አባቶቻችንን እናመሰግናለን።
7.3K views09:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-28 21:00:11 ቴዎድሮስ እስኪነግሥ ከተሰኘው መጽሐፍ ከገጽ 204-206 ካለው የተወሰደ።

የምትሰማውን ሳይሆን የሚሰማህን ተከተል,!

ኢትዮጵያ የጀብድና መስዋዕትነት እንዲሁም የአሸናፊነት ምልክት እንጂ በምርኮ የምትበዘበዝ የተሸናፊዎች መገለጫ አይደለችም፡፡ ጀግኖቿ በህይወት እያሉም ሆነ በሞታቸው ውድቀትና ባርነትን ድል ነስተው፣ ሀገርና ህዝብን በነጻነት ያቆዩ ናቸው፡፡ በዘመን መፈራረቅ ውስጥ እነዚህ ታላላቅ ሰዎች ለሚወዱት ሀገርና ህዝብ ራሳቸውን ዝቅ በማድረግ ኢትዮጵያና ህዝቦቿን ከፍ አድርገው ህይወታቸውን ያለስስት ገብረዋል፡፡ እኒህ ከሀገርና ከህዝብ በፊት ራስን መስዋዕት ማድረግ የሚቀድማቸው ቀደምት አባቶቻችን እንዳለመታደል ሆኖ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እሳት አመድን ወለደ እንደሚባለው ከላይ እስከ ታች የተሰገሰጉ ባለጊዜ ሹመኞች ባላጠለቁት ሱሪ፣ ባልነበሩበት የጦር ግንባር፣ የድል አጥቢያ ሽለላና ፉከራቸውን እያቀለጡ ሀገርን ለባንዳ፣ ህዝባቸውን ለባርነት አሳልፈው ሲሰጡ ይስተዋላል፡፡

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የመረማመጃ ምንጣፋቸውን አንስተው በባዶ እግር ጉዞ እሾህ ተጎዝጉዞ የሚኖሩ ኢትዮጵያ ከኔ ጀመረች ባይ ተራማጆችን መመልከት የተለመደ ነገር እየሆነ መጥቷል፡፡ በሰላም ተኝቶ ለማደር ቀርቶ ቆሞ ለመራመድ እንኳን ከእግር በፊት ዋስትና የሆናቸውን የቀደሙት አባቶቻችንን ደምና አጥንት እየከሰሱና እያንኳሰሱ የተያይዞ ገደል ጉዟቸውን ተያይዘውታል፡፡ ይህ ጊዜ የሰጠው ባለ ጠባብ ቅል አዕምሮ የሰፊዋንና ታላቋን ሀገር ነባር ርስት ሸንሽኖ ህዝብን ለመበታተን በመጣደፍ ለሰይጣን ወዶ ገብነቱን በመፍቀድ ሽምጥ የሚጋለብ ፈረስነቱን ተያይዞታል፡፡ ልዩነት እየዘራ የሰው አንገት ያጭዳል፤ ጎተራና ገበታውም የአቤል ስጋና ደም ከሆነ ሰንብቷል፡፡

በዚህ መርህ አልባ የህይወት አዙሪት ቅኝት ብዙኀኑ የውሸት ገናናዎች በእውነት ተፈትነው ይወድቃሉ፡፡ ባለራዕዩ የጥበብ ሰው በአባቶች ቅን አመለካከትና በመንፈሳዊ ጸጋ ከዘመነ መሳፍንት አዙሪት ወጥታ እያበበች የነበረችውን ሀገር ትንሽዬ መንደር ያደረጓትን ሹማምንት በአደባባይ መታገሉ ከሞት በታች የሆነ ብዙ ዋጋ አስከፍሎታል፡፡ ይሁን እንጂ ከራሱ ዝና የቀደምት ሀገሩን ክብርና የህዝብ ነጻነት ለማስከበር ሞትም ቢመጣ ጽዋውን ሊጋተው ወስኖ ጉዞውን በመጀመሩ ምንም ዓይነት ፈተና ከጉዞው ሊያስቆመው አልቻለም፡፡

በጥቂት የሚቆጠር እድሜ ውስጥ ዋጋው ተለክቶ የማይታወቅ ዕልፍ ዘርፈ-ብዙ ስራ የሰራው ጥበበኛ የወገኖቹ የጸብ ጠብመንጃ ላይ በፍቅር ቁሞ የፈሰሰውን ደም ለማድረቅ፣ የተደፋውን ለማቅናት፣ የደረቀውን ለማለምለም ደፋ ቀና እያለ ሲታትር ውቡን የወጣትነት እድሜውን ለሀገሩ ገብሯል፡፡ ቴዲ ከብዙዎቹ የሚለየው የሚሰማውን ውስጡ የሚለውን፣ የሚሰሙትን፣ ጆሯቸውን የሰጡትን እንጂ በየመንገዱ የሚሰማውን አልተከተለም፡፡ ጥላቻን ጆሮው ሲሰማ ውስጡን ፍቅር ገባው፤ መከፋፈልን ጆሮው ሲሰማ አንድ መሆን ውስጡን ገዛው፤ የወደፊቱን ጭንቅ በጆሮው ሲሰማ ልቡ የወደፊቱ ብርሃን አየው፤ ያንንም ሲከተልና ሲያቀነቅን የኖረ የመልካም መሆን አርአያ ጀግና አርቲስት ነው፡፡

መጽሐፉን ከዚህ በታች በተጠቀሱት መደብሮች ማግኘት ይችላሉ።

ስታዲየም ነጃ መጽሐፍ መደብር 0910990259

ለገሀር በጋሻው መጽሐፍ መደብር 0911656729

ለገሀር ማድያ ያሬድ መጽሐፍ መደብር 0913094097

መሳለሚያ ሆናልያት ህንፃ ቢሮ ቁጥር 156 ተኬ ማን ፕሮሞሽን 0911518012 ወይም 0921935862

አራት ኪሎ 0901197837

ፒያሳ አምፒር ታረቀኝ መጽሐፍ መደብር 0983294565

ለበለጠ መረጃ 0975550865 ይደውሉልን።
6.1K views18:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-28 21:00:05
ቴዎድሮስ እስኪ ነግሥ
4.0K views18:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-28 20:12:45
በአትሌቲክሱ ዘርፍ በአገሬ አሜሪካ ኦሪገን ግዛት ላይ ተካሂዶ በነበረው በ18ተኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና አራት /4/ ወርቅ፣ አራት /4/ ብር እና ሁለት /2/ ናህስ በጥቅሉ አስር /10/ ሜዳሊያዎችን በማንሳት አገራችን ኢትዮጵያ በዓለም የሁለተኛ ደረጃነትን እንድትይዝ እና ለዚህ አንጸባራቂ ድል እንድትበቃ ያስቻላችሁ መላው የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን አባላት በሙሉ ከልብ ልናመሰግናችሁ እንወዳለን።

ኢትዮጵያ ስሟ በዓለም ከፍ ይል ዘንድ ብሎም ኢትዮጵያውያን ወደ ብሄራዊ ስሜታቸው ይመለሱ ዘንድ እንዲህ ያሉ አነቃቂ እና አርኪ ተግባሮች በሁሉም ዘርፎች ይደገሙ ዘንድ መልካም መሆኑን ለማስታወስ እወዳለሁ። ሁሉም ኢትዮጵያ ሲል ማየት ደስ ይላል።

4 4 2

#WorldAthleticsChamps

✎ #ታታ_አፍሮ /ነፃ ብዕር/
4.0K views17:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-27 19:29:46
የአክብሮት ሰላምታዬን በማስቀደም ከሰሞኑ በምድረ አሜሪካ ኦሪገን ግዛት ተካይዶ በነበረው 18ተኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በተቀዳጀነው አንፀባራቂ ድል የተሰማኝን ደስታ ስገልፅ በተለይም በአሁኑ ወቅት ሀገራችን ካለችበት ተጨባጭ ሁኔታ አንፃር ከመቼውም ጊዜ በላቀ ብሔራዊ ስሜታችን ሊጠናከር በሚገባበት በእዚህ ታሪካዊ እና ወሳኝ ሰዓት ይህን አኩሪ ድል ላስመዘገቡ ባለውለታ ውድ ጀግኖች አትሌቶቻችን እና እንዲሁም ይህ የተቀናጀ ውጤት እንዲመጣ ከፍተኛ አስተዎፆ ላደረጉ ጀግናዋ አትሌት ኮማንደር ደራርቱ ቱሉን ጨምሮ ለአሰልጣኞች እና ለመላው የሉካን ቡድኑ አባላት በሙሉ ከፍ ያለ የአክብሮት ምስጋናዬን እያቀረብኩ ነው::

በእዚህ አጋጣሚ ለመላው ኢትዮጵያዊያን ወገኖቼ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክቴን ለማስተላለፍ እወዳለሁ::

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!
ፍቅር ያሸንፋል
ቴዎድሮስ ካሳሁን
(ቴዲ አፍሮ)
4.2K views16:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-26 18:34:28
ቴዎድሮስ እስኪ-ነግሥ /የቴዲ አፍሮ የህይወት ጉዞ/

"የሰው ልጅ በኖረበት በየትኛውም የዓለም ስፍራ፥ ባለጸጋ ሆነ ድሃ፣ አለቃ ሆነ ምንዝር በምድር በቆየባቸው ዘመናት የፈጸመው መልካምም ሆነ መጥፎ ተግባር በትውልዶች የህይወት ገጽ ውስጥ በአንዳች መልኩ መስፈሩ አይቀሬ ነው። በዚህ የህይወት ፍሰት ውስጥ ያለፈ ሁሉም ሰው ደግሞ የኋላ ዳና፣ የዛሬ አሻራ፣ የነገም ራዕይ አለው።"

እነሆ የክቡር ዶክተር አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን /ቴዲ አፍሮ/ የትላንት፣ ዛሬና ነገ መልክ፡፡

መጽሐፉን ከነገ ጀምሮ በነዚህ በታች በተጠቀሱት መደብሮች ማግኘት ይችላሉ።

ስታዲየም ነጃ መጽሐፍ መደብር 0910990259

ለገሀር በጋሻው መጽሐፍ መደብር 0911656729

ለገሀር ማድያ ያሬድ መጽሐፍ መደብር 0913094097

ሜክሲኮ ኤልያስ አምደ መጽሐፍ መደብር

መሳለሚያ ሆናልያት ህንፃ ቢሮ ቁጥር 156 ተኬ ማን ፕሮሞሽን 0911518012 ወይም 0921935862

አራት ኪሎ 0901197837

ካዛንቺስ መላ ህንጻ ጦቢያ መጽሐፍ መደብር 0913108312

ፒያሳ አፒር ታረቀኝ መጽሐፍ መደብር 0983294565

እንዲሁም በሁሉም የመጻፍ መደብሮች ያገኛሉ
ለበለጠ መረጃ 0975550865 ይደውሉልን
4.8K views15:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-23 20:01:31 https://vm.tiktok.com/ZMNQ7b7gR/?k=1
5.2K views17:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ