Get Mystery Box with random crypto!

ስልጤ ዞን ኮሚዩኒኬሽን - SILTIE ZONE COMMUNICATION

የቴሌግራም ቻናል አርማ szcommunication2012 — ስልጤ ዞን ኮሚዩኒኬሽን - SILTIE ZONE COMMUNICATION
የቴሌግራም ቻናል አርማ szcommunication2012 — ስልጤ ዞን ኮሚዩኒኬሽን - SILTIE ZONE COMMUNICATION
የሰርጥ አድራሻ: @szcommunication2012
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.58K

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2022-09-01 16:02:04
የአንድ ፓርቲ ጥንካሬ የሚለካው ባለው ጠንካራ አባል፣አደረጃጀትና አሰራር እንዲሁም የተሰነደ እና ግልፅ የሚመራበት ፍልስፍና ሲኖረው ነው፤በመሆኑም ጠንካራ አባላትን ለማፍራት በሚደረገው ጥረት ሁሉም አመራራችን ብቃት ያለው የአመራርነት ሚናውን ሊወጣ ይገባል።

አቶ ቀድሩ አብደላ ላጊ የስልጤ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ

ምንጭ፦የስልጤ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ህዝብ ግንኙነትና ሚዲያ ዘርፍ ነው
330 views13:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 18:38:12
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የአልጄሪያ ጉብኝት ለሁለቱ አገራት ጠንካራ የትብብር ግንኙነት ወሳኝ ነው- የአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ራምታኔ ላማምራ

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የአልጄሪያ ጉብኝት ለሁለቱ አገራት ጠንካራ የትብብር ግንኙነት ወሳኝ መሆኑን የአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ራምታኔ ላማምራ ገለጹ።

በአልጄሪያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት እያደረጉ የሚገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ፤በአልጀርስ የሰማዓታት መታሰቢያ ሙዚየም እና ግዙፉን ሳይዳል የመድሃኒት ፋብሪካ ጎብኝተዋል።

ከአልጀሪያ ፕሬዝዳንት አብዱልመጅድ ታቡኔ ጋርም የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል።

የአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ራምታኔ ላማምራ፤የጠቅላይ ሚኒስትሩ የአልጄሪያ ጉብኝት ለሁለቱ አገራት ጠንካራ የትብብር ግንኙነት ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ፤ቀደም ሲል በአልጄሪያ ጉብኝት ማድረጋቸውን አስታውሰው የአሁኑ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉብኝትም ለሁለቱ አገሮች የትብብር ግንኙነት መጠናከር ጉልህ ሚና ያለው መሆኑን ተናግረዋል።

የመሪዎቹ ጉብኝት በአገራቱ መካከል ጠንካራ ግንኙነት መኖሩንና ውጤታማ ትብብር ስለመኖሩም የሚያረጋግጥ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጠቅሰዋል።

ሁለቱም አገራት የአፍሪካ ችግሮች በአፍሪካዊ መፍትሔ እልባት እንዲያገኙ በአፍሪካ ህብረት የሚደረገውን ጥረት የሚደግፉ መሆኑን ተናግረዋል።

ኢትዮጵያና አልጄሪያ የኢንዳስትሪ ልማት የተሻለ ዕድገት ለማምጣት ቁልፍ መሆኑን በመገንዘብ እየሰሩበት መሆኑንም ገልጸዋል።

አንድ ሉዓላዊ አገርና ሕዝብ የተፈጥሮ ሀብቱን የማልማት እና የመጠቀም መብት ያለው መሆኑንም ተናግረዋል።

በዚህ መሰረትም የአፍሪካ አገራት መልካም ጉርብትና እንዲኖራቸውና ችግሮቻቸውንም በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ አልጄሪያ ትደግፋለች ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
459 views15:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 16:35:10 በባለፈው የ2014 የበጀት አመት የተመዘገቡ ስኬቶችን በማስቀጠልና በማጠናከር በ2015 የዞኑን ህዝብ የልማትና መልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በአግባቡ መመለስ አማራጭ ያሌለው ጉዳይ በመሆኑ አመራሩ ከመቼውም በላይ በትጋት ሊሰራ እንደሚገባ የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሊ ከድር አሳሰቡ።

ዋና አስተዳዳሪው ይህን ያሉት የስልጤ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ከአጠቃላይ ከዞን ማዕከል አመራሮች እና በዞኑ ከሚገኙ የከተማ አስተዳደሮችና የወረዳ አስተባባሪ አካላት ጋር የ2014 በጀት ዓመት የአመራር የተግባር ግምገማና የ2015 በጀት የፈፃሚ ማዘጋጃ መድረክ በተጀመረት ወቅት ነው።

በዚህ መነሻም የስልጤ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት የ2014 በጀት ዓመት "ለብልጽግና ጉዟችን ስኬት በተደራጀ መንገድ እንረባረባለን" በሚል መሪ ሀሳብ የአመራር የተግባር ግምገማና የ2015 በጀት የፈፃሚ ማዘጋጃ መድረክን እያካሄደ ይገኛል።

የውይይት መድረኩ የመሩት የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሊ ከድር እንዳሉት በሀገራዊ በለውጡ ሂደት ያጋጠሙ ፈተናዎችና ተግዳሮቶችን በመቋቋም ዛሬ ላይ ደርሰናል።

አሁንም ከተለያዩ የውስጥና የውጭ ጠላቶች ፈተናዎች እናጋጠሙን ይገኛሉ ያሉት አቶ አሊ ከድር እነዚህንና መሰል የሚያጋጥሙ ሀገራዊና ከባቢያዊ ፈተናዎችን ተቋቁሞ ሀገርን ማሻገር የሚያስችል አመራር የሚያስፈልግበት ወቅት ላይ ነን።ይህንን ለማሳካት ደግሞ ይሄ መድረክ ከፍተኛ አስተዋጾን የሚያበረክት በመሆኑ ሁሉም ተሳታፊ አመራሮች በመድረኩ የሁለት ቀናት ቆይታ ውስጥ የሚጠበቁ ግቦችን ለማሳካት ሚናውን ሊወጣ እንደሚገባ አሳስበዋል።

መድረኩን ከዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ጋር በመሆን የመሩት የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ቀድሩ አብደላ ባሳለፍነው የ2014 የስራ ዘመን በዞናችን የተጀመሩ የልማትና መልካም አስተዳደር ቁልፍ ተግባራትን ለማጠናቀቅ የአመራሩን ቁርጠኛ የሆነ ትግልና ትጋት የሚያበረክተው ሚና ከፍተኛ ነው ሲሉም አስረድተዋል።

በሳለፍነው የበጀት አመት የተመዘገቡ ስኬቶችን በማስቀጠልና በማጠናከር በ2015 የዞኑን ህዝብ የልማትና መልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በአግባቡ መመለስ አማራጭ ያሌለው ጉዳይ ነው ያሉት የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት አቶ ቀድሩ አብደላ ናቸው።

ይህም በመሆኑ የዞናችን መላው አመራር የሀገራችንን የብልጽግና ጉዞን የሚያቀጭጩና የሚገዳደሩ ጉዳዮችን ነቅቶ በመከታተል የለገራችንን ብልጽግና ከዳር ለማድረስ በሚደረው ርብርብ ከመቼውም ጊዜ በላይ ተግተን ልንሰራ ይገባል ያሉት አቶ ቀድሩ አብደላ በሌላ በኩል በየደረጃው ህብረተሰቡ ለሚያነሳቸው የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የአመራሩ ውጤታማነት የላቀ ሚና ኣለው ብለዋል።

አጠቃላይ የዞኑን አመራር ጨምሮ በዞኑ የሚገኙ የወረዳ አስተዳዳሪዎች፣የከተማ አስተዳደር ከንቲባዎችና የየመዋቅሮቹ የአስተባባሪ አካላት የመድረኩ ተሳታፊዎች ናቸው።

ይህ መድረክ ለተከታታይ ሁለት ቀናት የሚቆይ ሲሆን መድረኩ ላይም በ2015 የበጀት አመት በትኩረት ሊሰራባቸው በሚገቡ ነጥቦችና በሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ በጥልቀት በመምከርና በመገምገም የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።
573 views13:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 16:35:09
507 views13:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 22:29:20 የአለም የጤና ድርጅትን ለአሸባሪው ሕወሃት መሳሪያነት መጠቀም ወንጀል ነው፦ሄርሜላ ሀረጋዊ

የአለም የጤና ድርጅትን ለአሸባሪው ሕወሃት የፕሮፖጋንዳ መሳሪያነት መጠቀም ወንጀል ነው ስትል ታዋቂዋ ጋዜጠኛ ሄርሜላ አረጋዊ ለድርጅቱ ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ጋቢ ስተርን በጻፈችው ደብዳቤ ገለጸች።

የአለም ጤና ድርጅት ሀላፊ ዶክተር ቴዎድሮስ አድሀኖም የአሸባሪው ሕወሃት ቡድን ግንባር ቀደም አመራር ከሆኑ ግለሰቦች መካከል አንዱ እንደሆኑ በመጥቀስ አሸባሪው ሕወሃት በብረሃን ነጻ አውጪ በመምሰል በጭለማ የሚገድል በጭካኔ የተሞላ ኢትዮጵያዊው ፋሽት ነው ብላለች።

አሸባሪው ሕወሃት ግዜው እንዳበቃ መላ የአፍሪካ ቀንድ ህዝቦች መስክረዋል ያለችው ሄርሜላ የአም የጤና ድርጅት የቂም ዘር በአፍሪካ ምድር በመዝራት በህዝቦች መካከል ጉድጓድ እየቆፈረ ነው ብላለች።

የትግራይ ህዝብ በአሸባሪው ሕወሃት አመራር እና በጤና ድርጅቱ ሀላፊ ቴዎድሮስ አድሃኖም ምክንያት መከራን እያሳለፉ ይገኛሉ ስትል የገለጸች ሲሆን አሸባሪው ሕወሃት ሚሊዮኖችን ያለፍላጎታቸው ለመግዛት የትግራይ ህዝብን እንደ ማሲያዣነት እየተጠቀመበት ይገናል ብላለች።

ከባለፈው የሚያዚያ ወር ጀምሮ አስፈላጊ የሆነ እርዳታ ወደ ትግራይ ክልል በመጓጓዝ ላይ እንደሚገኝ የአለም የምግብ ፕሮግራም ቢያስታውቅም ዘ ጋርድያን ጋዜጣ በክልሉ ባለው ረሃብ ምክንያት ሴቶች እና ልጃገረዶች የአስገድዶ መደፈር ወንጀል እየተፈጸመባቸው እንደሚገኙ አስታውቋል።

ወደ ትግራይ የሚሄደውን እርዳታ ማን እየተጠቀመበት እንደሚገኝ የምትጠይቀው ሄርሜላ “እርደታውን የተጠቀመበት ማነው የአሸባሪው ሐወሃት አባላት፣የትግራይ ህዝብ ወይስ በትግራይ እየተንቀሳቀሱ ያሉ የተረድኦ ድርጅቶች አባላት” ስትል ትጠይቃለች።

እንደ አለም የጤና ድርጅት በህዝብ ዘንድ የቀረችውን እንጥፍጣፊ ተአማኒነት ወደ ጎን በመተው አሸባሪው ሕወሃትን መደገፍ በትውልዶች ዘንድ ለዘመናት የማይረሳ ግፍ ነው ብላለች።

ድርጅቱ አፍሪካውያን የሚያነሱዋቸውን ጥያቄዎች በተገቢው መንገድ መመለስ ባይችልም ብዙዎች በማህበራዊ የመገናኛ መንገዶች እየተናገሩ ይገኛሉ ያለችው ሄርሜላ ለድርጅቱ ኮሙኒኬሽን ሀላፊ ያስገባቸው ድብዳቤ ማህደር የሚቀመጥ እና የድርጅቱን አጸያፊ ፕሮፖጋንድ የሚያጋልጥ ነው ብላለች።

source ENA
184 views19:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 22:29:17
175 views19:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 21:07:13 "በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተገኙ ስኬቶችን በማጠናከር በ2015 የክልሉን ህዝብ የልማትና መልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ የአመራር ትጋት ያስፈልጋል" አቶ ርስቱ ይርዳ

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተገኙ ስኬቶችን በማጠናከር በ2015 የክልሉን ህዝብ የልማትና መልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በተሟላ መንገድ ለመመለስ የአመራር ትጋት እንደሚያስፈልግ የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ርስቱ ይርዳ ገለጹ።

የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች የ2014 በጀት ዓመት የተግባር አፈጻጸምና የ2015 ፈጻሚ አመራሮች ማዘጋጃ መድረክ በሐዋሳ ከተማ ተጀምሮ እየተካሄደ ነው።

በመድረኩ ላይ የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ርስቱ ይርዳው እንደገለጹት በ2014 በጀት ዓመት የተጀመሩ የልማትና መልካም አስተዳር ስራዎችን ለማጠናቀቅ በተሰሩ ስራዎች የተሻሉ ስኬቶች ተመዝግበዋል።ያደሩ የህዝብ ጥያቄዎችን ለመመለስ የተቀመጡ ግቦችም ውጤት እያስመዘገቡ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በ2015 በጀት ዓመት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተመዘገቡ ስኬቶችን በማጉላትና ድክመቶችን በማረም ለተሻለ ውጤት በየደረጃው ያሉ አመራሮች ራሳቸውን ሊያዘጋጁ እንደምገባም አቶ ርስቱ አሳስበዋል።

የደቡብ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤ ኃላፊ አቶ ጥላሁን ከበደ በበኩላቸው የክልሉ አመራሮች በፓርቲው መርነት የተከናወኑ ተግባራትን ለማስፈፀምና የህዝቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን ለማሳካት ያሳዩት ቁርጠኝነት የሚደነቅ መሆኑን ገልጸዋል።

በተለይ የክልሉን ህዝቦች የአደረጃጀት ጥያቄዎችን በሰከነ መንገድ ለመመለስ የተጀመሩ ስራዎች እስከአሁን በተረጋጋ ሁኔታ እንድካሄድ አመራሩ ላደረገው አበርክቶም ምስጋና አቅርበዋል።ብልጽግና ፓርቲ የህዝቦችን የቆዩና ያደሩ የልማት፣የመልካም አስተዳርና ሌሎች ጥያቄዎችን ለመመለስ ለህዝቡ በገባው ቃል መሠረት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በተያዘው በጀት ዓመት በክልሉ የምነሱ ጥያቄዎችን በተደራጀና በሰከነ መንገድ ለመመለስ ፓርቲው አቅዶ እየሰራ መሆኑን ገልፀው፣ተግባሮችን በብቃት የሚፈጽሙ አመራሮችን ማዘጋጀት የዛሬው መድረክ ዋነኛው ዓላማ መሆኑን ገልፀዋል።

በፈፃሚ ማዘጋጃ መድረኩ ባለፈው በጀት ዓመት ስኬቶችና ጉድለቶችን በአግባቡ በመፈተሽ ጥንካሬዎቹ እንድቀጥሉ፣ የድክመቶቹ ምንጮችም ተለይተው እንደምታረሙ እንድሁም ለቀጣይ ተልዕኮ የተዘጋጀ አመራር የሚፈጠርበት መድረክ መሆኑን አቶ ጥላሁን ገልጸዋል።

መድረኩም ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት የሚቆይ ሲሆን የክልሉ ካብኔ አባላት የዞንና ልዩ ወረዳ አስተባባሪ አባላትና ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች መሳተፋቸውን የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ዘግቧል።
255 views18:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 21:07:11
249 views18:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-03 19:26:41 በስልጤ ዞን የሳንኩራ ወረዳ አስተዳደር ለሀምሳ አለቃ ማሙሽ ከድር ሁሴን የ3መቶ ካሬ የመኖሪያ መስሪያ ቦታ በስጦታ ማበርከቱን አስታወቀ።

የወረዳው አስተዳደር ከወረዳው ከተማ ልማትና ቤቶች ጽ/ቤት እና ከረግዲና ማዞሪያ ማዘጋጃ ቤት ጋር በጋራ በመሆን ለሀምሳ አለቃ ማሙሽ በዛሬው ዕለት በማዞሪያ ከተማ ያበረከተው የ3መቶ ካሬ የመኖሪያ መስሪያ ቦታ ግለሰቡ የሀገር ሉዓላዊነት በማስከበር ረገድ በፍጹም ወታደራዊ ዲሲፕሊን ሀገርን እያገለገለ የሚገኝ መሆኑን ተከትሎ ነው።

ሀምሳ አለቃ ማሙሽ ከድር ሁሴን በሳንኩራ ወረዳ ረግዲና ቀበሌ ተወልዶ ያደገ ሲሆን ከዛሬ 9 ዓመታት በፊት የሀገርን ዳር ድንበርና ሉዓላዊነት ለማስከበር በፍቃደኝነት የመከላከያ ሰራዊትን በመቀላቀል የሀገር ደጀንነቱን በተግባር እያስመሰከረ የሚገኝ የቁርጥ ቀን ልጅ ነው።

በዚህም መሰረት የወረዳው አስተዳደር ከወረዳው ከተማና ቤቶች ልማት ጽ/ቤት ጋር በመሆን ሀምሳ አለቃ ማሙሽ በፍጹም የሀገር ፍቅርና ወታደራዊ ዲስፕሊን ለሀገር ሰላም መከበርና አንድነት እያበረከተ ያለውን ታላቅ አስተዋጽኦ በማሰብ በረግዲና ከተማ የ3መቶ ካሬ የመኖሪያ መስሪያ የሚሆን ቦታ በስጦታነት አበርክተዋል።

በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ተማም ፊጣሞ ሀምሳ አለቃ ማሙሽ ከድር ቅድሚያ ለሀገሩ በመስጠት ለሀገር ሉዓላዊነት መከበር እየከፈለ ላለው መስዋዕትነት ምስጋናቸውን በማቅረብ የቤት መስሪያ ቦታ ስጦታው ወታደሩ ፍጹም ወታደራዊ ዲስፕሊን በመላበስ እያበረከተ ለሚገኘው አስተዋጽኦ ምስጋና ለማቅረብ በማለም የተበረከተ ነው ብለዋል።

ሀምሳ አለቃ ማሙሽ ከድር በራያ ቆቦ ግንባር እያገለገለ የሚገኝ ሲሆን ስጦታው ለእረፍት ወደ ቤተሰቡ በመጣበት ወቅት የተበረከተ ነው በተሰጠው ቦታ የወረዳው ከተማ ልማት ጽ/ቤት ቤት ሰርቶ የሚያስረክብ ስለመሆኑም ተጠቁሟል።

በርክክቡ ወቅትም የወረዳው አስተባባሪ አካላትና ሌሎች አመራሮችን ጨምሮ የሀይማኖት አባቶች እና የሀገር ሽማግሌዎች ተገኝተዋል ሲል የወረዳው ብልጽግና ፓርቲ ህዝብ ግንኙነትና ሚዲያ ዘርፍ ዘግቧል።
328 views16:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-03 19:26:40
316 views16:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ