2022-11-27 21:15:54
ትብብራችሁ አስፈልጎኛል!!!
ከታች በምስሉ የምትመለከቷት እህታችን ጀንበሬ ሁሴን ትባላለች ። ትውልድ ቦታዋ ደቡብ ወሎ መቅደላ ወረዳ ኮሬብ ሲሆን ገና በለጋ እድሜዋ ሳውድ አረቢያ ለስራ ሄዳ ለተወሰኑ አመታት መስራት ብትችልም በሰው ሀገር ላይ የአልጋ ቁራኛ ከሆነች 7 ወራት አልፏታል።
አባቷን በልጅነት ያጣች ሲሆን አይዞሽ የሚል ወንድም እንኳን አልታደለችም። እህቷ እንደሷ በስደት የቆየች ሲሆን የእህቷን ስቃይ ማሰብ አቅቷት በቅርቡ ሀገር ቤት ገብታለች። እናቷ አቅመ ደካማ ናቸው። ላለፉት 2 ሳምንታት ገንዘብ አሰባስበን ወደ ሀገር ትገባ ዘንድ ሙከራ ብናደርግም የሚያስፈልገውን ያክል ገንዘብ ማሰባሰብ አልቻልንም። አንድ ወንድማችን ከተኛበት ሆስፒታል ሄዶ ማዬት የቻለ ሲሆን የሚያስፈልገው ገንዘብ መሰብሰብ ከተቻለ አገሯ መግባት ትችላለች።
እህት ወንድሞቼ መለመንን ማንም ይጠየፋል። በነዚህ አጋጣሚዎች ግን ሌላ አማራጭ የሌለን በመሆኑ ጉዳዩን ወደ እናንተ ለማምጣት ግድ ሆኖብናል። የምትችሉ በገንዘብ የማትችሉ ይሄን ፖስት በማድረግ አቅም ላላቸው ይደርስ ዘንድ ታግዙን ዘንድ እንጠይቃለን።
ለገንዘብ ማሰባሰቡ ግሩፕ የከፈትን ሲሆን ሊንኩም ከስር ተቀምጧል።
https://chat.whatsapp.com/FaC7mCeGzDpHXvutwL7rgv
5.2K views18:15