Get Mystery Box with random crypto!

ስንክሳር በየቀኑ

የቴሌግራም ቻናል አርማ sinksar — ስንክሳር በየቀኑ
የቴሌግራም ቻናል አርማ sinksar — ስንክሳር በየቀኑ
የሰርጥ አድራሻ: @sinksar
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.00K
የሰርጥ መግለጫ

የአመቱን ስንክሳር በየቀኑ የሚቀርብበት ማብራሪያው ላልቀረበበትም የበለጠ እንድናነብ የሚረዳን መማማሪያ ነው።
" ዓለምን ወይም በዓለም ያሉትን አትውደዱ:: በዓለም ያለው ሁሉ: እርሱም የሥጋ ምኞትና የዓይን አምሮት: ስለ ገንዘብም መመካት ከዓለም ስለ ሆነ እንጂ ከአባት ስላልሆነ: ማንም ዓለምን ቢወድ የአባት ፍቅር በእርሱ ውስጥ የለም:: ዓለሙም: ምኞቱም ያልፋሉ::" 1ዮሐ. 2:15
# ያጋሩ

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-08-27 11:27:08
190 views08:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 11:26:57 በመተሐራ ቅዱስ ሚካኤል በወጣቶች ሲፈለፈል የነበረው አስደናቂ ዋሻ ተጠናቀቀ!
ይህ ከታች በፎቶ የምትመለከቱት በመተሐራ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ህንጻ ቤተመቅደስ ፊት ለፊት የሚገኘው በብርቱዎቹ የናታኔም ወጣቶች ተሰርቶ የተጠናቀቀው እጅግ አስደናቂ ዋሻ ነው። ጥቂት ክፍተት ያለው ዋሻ አስቀድሞ በደብሩ ግቢ ውስጥ ነበር።

ይህንንም በልዩ ልዩ ጊዜ የነበሩና ወደ ስፍራው የመጡ ታላላቅ አባቶች በዋሻው የእጣን መዓዛ አልፎ አልፎም ብርሃን ይታያል በማለት ምስክርነታቸውን ይሰጡ ነበር።

የከተማው ኦርቶዶክሳዊም ይህን ዋሻ በተመለከተ ቁጥር በቁጭት እንደሌሎች ገዳማት ተሰርቶ አገልግሎት መስጠት የሚጀምረው መቼ ነው ? በማለት በቁጭት ይናገር ነበር።

ነገር ግን ከባድና ተጨማሪ ስራ የሚጠይቅ በመሆኑ ተሰርቶ የጸሎት ቤት፣ ለሱባኤ መዝጊያ ሆኖ ለማየት ለዘመናት ከጉጉት ያለፈ አልነበረም።
ገናናው መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ስራውን የሚሰራበት ዘመኑ ደረሰና የመተሐራ ቅዱስ ሚካኤል ናታኔም የምንጣፍ ማህበር ልጆቹን አስነስቶ ከፍተኛ ዋጋ በመክፈል ሙሉ ለሙሉ ዓለት የሆነው የዋሻ ክፍል ከፍተኛ የሆነውን ሙቀት ታግዞ በላብ እየታጠበ ከፍተኛ ተጋድሎ በመፈጸም ያለማቋረጥ በመዶሻ እየፈረከሰ፣በዶማ እየናደ በአካፋ እየዛቀ እሳት በሚተፋ ዋሻ ውስጥ በከፍተኛ ትጋት በድንጋይ ስለት እግራቸው እየተቆረጠ በመዶሻ እጃቸው እየተቀጠቀጠ በከፍተኛ የደስታ ስሜት ተጋድሎ በመፈጸም የዋሻውን ስራ ሙሉ ለሙሉ ከፍጻሜው አድርሰውታል።

አሁን እንደምትመለከቱት በጣም ሰፊ የሆነ ቁመቱም በጣም ከፍ ስላለ ቀዝቃዛ የሆነ ለጸሎትና ለሱባኤ ምቹ የሆነ ዋሻን ጠርበው አጠናቀዋል። በማህበሩ አባል በሆነች በወጣት እርብቃ የተሳሉ የቤተክርስቲያን ትውፊት የጠበቁ ቅዱሳን ስዕላትም ተለጥፈው ሙሉ ለሙሉ ተጠናቋል።እነዚህ ብርቅዬ የመተሐራ የተዋህዶ ልጆች ሙሉ አባላቱ የግል ስራቸውን ጭምር በመተው ለዚህ ታላቅና አስደናቂ ተግባር ዋጋ ከፍለዋል። በእውነት በዚህ ዘመን ድንጋይ ፈልጦ ዋሻ የሚገነባ ያውም በከተማ ከማየት በላይ ምን የሚያስደስት ነገር አለ ? ምንም።

ደግሞም እነዚህ ልጆች ሁሌም መከባበራቸው ፣መዋደዳቸውና ለአገልግሎት ያለቸው ትጋትና ብርታት በሚሰሩት በጎ ተግባር ከከተማው አልፈው በመላው ገዳማትና አድባራት የደብራቸውን ስም በወርቅ ቀለም እያጻፉ ነው።የእነርሱን ደግሞ በመንግሥተ ሰማያት!።

እቅዳቸው ተሳክቶ ዋሻውም ከፍጻሜ ደርሶ በብጹዕ አባታችን አቡነ ጎርጎርዮስ የምስራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የዝ/ሐ/ብ/ቅ/ ገብርኤል ተመርቆ አገልግሎት ሊጀምር ጥቂት ቀናት ብቻ ቀርተውታል። አምላክ ለምርቃቱ ቀን ለመድረስ ይፍቀድልን።

የመተሐራ ቅዱስ ሚካኤል ናታኔም ማህበር ወጣቶች የአግልግሎት ዘመናቸው በቤቱ ይለቅ።ቅዱስ ሚካኤል ጥላ ከለላ ጋሻ መከታ ሆኖ ፍጻሚያችሁን ያሳምርላችሁ።

ይህንን ያደረገ የቅዱስ ሚካኤል አምላክ የተመሰገነ ይሁን

መምህር ኤፍሬም ሀብተ ማርያም
( የኤፍሬም ዕይታዎች )
177 views08:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 00:05:16 † ስንክሳር ነሐሴ 21 †

እንኳን ለቅዱሳት አንስት ኄራኒ ሰማዕት: ንግሥተ ሳባ እና ንግሥት ዕሌኒ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †

†ቅድስት ኄራኒ ሐዋርያዊት ሰማዕት †

† ይህቺ ቅድስት ወጣት መልክ ከደም ግባት: ምግባር ከሃይማኖት: ስም ከመልካምነት የተባበረላት ሰማዕት ናት:: #ኄራኒ ማለት "ሰላማዊት: የተወደደች" ማለት ነው:: አንድም በጥሬው "ሰላምና ፍቅር" ማለት ነው::

ቅድስት ኄራኒ በመጀመሪያው መቶ ክ/ዘመን በታናሽ እስያ የንጉሥ #ሉክያኖስ ልጅ ናት:: ከተወለደች ጀምሮ ስለ ክርስትና ሰምታ አታውቅም:: ምክንያቱም አባቷ ጣዖት አምላኪ ከመሆኑ ባለፈ ክርስቲያኖችን ይቀጣ ስለ ነበር ነው::

ልጁን ማንም እንዳያገኛት ሲል ንጉሡ ለቅድስት ኄራኒ ቤተ መንግስት ሠራላት:: ማንም እንዳይገባ በዙሪያው 12 አጥር አጠረበት:: ጣዖቶቹን እንድታጥን አገልጋዮችንም ሾመላት::

ምናልባት አጥር ሰውን ሊከለክለው ይችላል:: #እግዚአብሔር ግን እግዚአብሔር ነውና ምንም አይከለክለውም:: ጌታ ደግሞ ይህቺን ወጣት ለወንጌል አገልግሎት ይፈልጋታል:: አንድ ቀን አባቷ: ልጁ ምሑር እንድትሆንለት አለ የተባለ ሽማግሌ ፈላስፋ ቀጠረላት::

ጥበበ እግዚአብሔር ማለት ይሔ ነው:: አባቷ ይሕ ሽማግሌ ማንን እንደሚያመልክ አልተረዳም:: አረጋዊው እጅግ የተዋጣለት ክርስቲያን ነው:: ግን ማንም አያውቅበትም:: አረጋዊው ቅድስት ኄራኒን ዝም ብሎ ሊሰብካት አልወደደም::

መጀመሪያ በስነ ምግባር አነጻት:: ቀጥሎ ግን "ጌታ ሆይ! ጐዳናህን ምራት" እያለ ይጸልይላት ገባ:: ጌታችን ልመናውን ሰምቶታልና ቅድስቷ አንድ ቀን ግሩም ራዕይን አየች::

እርሷ ለማዕድ ተቀምጣ ሳለ: የምሥራቅና የምዕራብ መስኮቶቿም ተከፍተው ሳሉ: በምሥራቁ መስኮት ነጭ ርግብ በአፏ የወይራ ዝንጣፊ (ቆጽለ ዘይት) ይዛ ገባችና ማዕዷ ላይ አኑራው ሔደች:: እርሷን ተከትሎ ደግሞ ንስር በአፉ አክሊል ይዞ ገብቶ ማዕዷ ላይ ጥሎት ሔደ::

በ3ኛው ግን ቁራ: እባብ በአፉ ይዞ በምዕራቡ መስኮት ገብቶ ማዕዷ ላይ ጥሎት ወጣ:: ቅድስት ኄራኒ ያየችው ራዕይ ቢጨንቃት ሽማግሌ መምሕሯን "ተርጉምልኝ" አለችው::

እርሱም "ልጄ ሆይ! ለዘመናት ስጠብቀው የነበረ ምኞቴን ነው ጌታ ያሳየሽ:: የሕልምሽ ትርጉም እንዲህ ነው:- ነጭ ርግብ የመንፈስ ቅዱስ (የሃይማኖት) ምሳሌ ናት:: የወይራ ዝንጣፊው ደግሞ #ማሕተመ_ጥምቀት( #ሜሮን) ነው:: ቁራ የክፉ ነገሥታት ምሳሌ ሲሆን እባብ የመከራ ምሳሌ ነው::

ንስር ድል የመንሳት ምልክት ሲሆን አክሊል ደግሞ የመንግስተ ሰማያት ምሳሌ ነው:: ልጄ! ክርስቲያን ሆነሽ የሚደርስብሽን ሁሉ ጌታ አሳይቶሻል" ብሎ ተርጉሞላት ተሰናበታት::

እርሷም ወደ ምሥራቅ ዙራ ጸለየች:- "የማላውቅህ አምላክ ሆይ! ወደ እውነትህ ምራኝ" ስትል ለመነች:: በዚያች ሰዓት የእግዚአብሔር መልአክ መጥቶ አጽናናት:: የሚያጠምቃትም እንደሚልክላት ነገራት::

በዚያን ጊዜ አባቷ ገብቶ "ልጄ! ከመሣፍንቱ ላንዱ ልድርሽ ስለሆነ ምን ትያለሽ?" አላት:: "3 ቀን ስጠኝ" አለችውና ሰጣት:: ወደ ጣዖቶቹ ዕለቱኑ ወርዳ "ላግባ ወይስ ይቅርብኝ?" አለቻቸው:: ከቀድሞም በወርቅ የተለበጡ ድንጋዮች ናቸውና ዝም አሉ:: በሙሉ ቀጥቅጣ ሰባብራቸው ተመለሰች::

በዘመኑ #ቅዱሳን_ሐዋርያት(በተለይ እነ #ቅዱስ_ዻውሎስ) በሕይወተ ሥጋ ነበሩና ከቅዱስ ዻውሎስ ደቀ መዛሙርት አንዱ ቤቷ እንደ ተዘጋ ገባ:: ክርስትናን ከጥንቱ እስከ ተፍጻሜቱ አስተምሮ አጠመቃት::

በ3ኛው ቀን አባቷ "ምን መከርሽ?" ቢላት "የእኔ ምክር #መርዓተ_ክርስቶስ(ሰማያዊ ሙሽራ) መሆን ነው" አለችው:: አባቷ ደነገጠ:: እጅግ ስለ ተናደደ ወደ አደባባይ አውጥቶ: አስሮ መሬት ላይ ጣላትና በመቶ የሚቆጠሩ ፈረሶች እንዲረግጧት አደረገ::

በወቅቱ ሰው የሚጠብቀው የአካሏን ቁርጥራጭ ነበር:: ነገር ግን ጌታ ከእርሷ ጋር ነበርና ልብሷ እንኩዋ ጭቃ አልነካም:: አባቷ ንጉሥ ሉክያኖስና ሠራዊቱ ያዩትን ማመን አልቻሉም:: ሁሉም ድምጻቸውን ከፍ አድርገው "ከክርስቶስ በቀር ሌላ አምላክ የለም" አሉ:: ቅድስት ኄራኒ ምንም ሳትናገር ይህንን ሁሉ ሰው ማረከች::

ወዲያውም ንጉሡ መልእክተኛ ልኮ: የቅዱስ ዻውሎስ ደቀ መዝሙርን አስጠርቶ: ከነ ቤተሰቦቹ ተጠመቀ:: የዚህን ዓለም ክብር ንቆም ንግሥናውን ተወ:: የጸሎት ሰውም ሆነ:: የቅድስት ኄራኒ ተጋድሎ ግን ቀጠለ::

በአካባቢው የነበረ ንጉሥ መጥቶ የአባቷን መንግስት ቀማ:: እርሷንም እጅግ አሰቃያት:: እርሱ አልፎ አርማንዮስ የሚባል ንጉሥ እንዲሁ አሰቃያት:: እርሱም አለፈ:: ከእርሱ ቀጥሎ የመጣው ንጉሥ ብዙ መከራዎችን በእርሷ ላይ አደረሰ:: በጦርም ጐኗን ወግቶ ገደላት::

ከጥቂት ሰዓታት በሁዋላ ግን ልክ ከእንቅልፉ እንደሚነቃ ሰው ተነስታ ጠራችው:: በጣም ደንግጦ "አምላክሽ አምላኬ ነው" ሲል አመነ:: ከ30,000 በላይ ሠራዊቱን ይዞም ተጠመቀ::

ቅድስት ኄራኒ በቀረ ሕይወቷ በስብከተ ወንጌል እስያን አድርሳለች:: ጌታ አብርቶላት: እርሷም አብርታ: እልፍ ፍሬን አፍርታ: በዚህች ቀን ዐርፋለች:: የሐዋርያትንም: የሰማዕታትንም አክሊል ተቀዳጅታለች::

ንግሥተ ሳባ

† ይሕቺ ኢትዮዽያዊት ከ3 ሺ ዘመናት በፊት የነበረች ደግ እናት ናት:: በሥጋዊ ደረጃ ከታንዛንያ እስከ #የመን ያስተዳደረች ስመ ጥር ንግሥት ስትሆን በመንፈሳዊው ደረጃ ደግሞ እግዚአብሔር የቀባውን ሰው ፍለጋ ወደ #ኢየሩሳሌም ተጉዛለች::

ከዚያውም አምልኮተ እግዚአብሔርን ከሥርዓተ ኦሪት ጋር አምጥታለች:: ድንግልናዋን ለታላቁ #ንጉሥ_ሰሎሞን ሰጥታ #ምኒልክን ወልዳለች:: ይህቺ ንግሥት በጌታችን (በፈጣሪ) አንደበትም ተመስግናለች:: (ማቴ. 12:42) በስምም " #ሳባ: #አዜብና #ማክዳ ተብላ ትታወቃለች:: ዛሬ ዕለተ ልደቷ ነው::

† ቅድስት ዕሌኒ ንግሥት †

† ይሕቺ ቅድስት የቅዱስ #ቆስጠንጢኖስ እናቱ: የመስቀሉ ወዳጅ: የቤተ ክርስቲያን ባለውለታ የሆነች ክብርት እናት ናት:: ይህቺም ቅድስት የተወለደቺው በዚሁ ዕለት ነው::

† የቅዱሳት እናቶቻችን አምላክ እህት እናቶቻችንን ከክፋትም: ከጥፋትም: ይሠውርልን:: ለሃገርም: ለሃይማኖትም የሚጠቅሙ ሴቶችንም ጌታ አይንሳን:: በረከታቸውም ይደርብን::

† ነሐሴ 21 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ተዝካረ ፍልሠታ ለማርያም ድንግል (6ኛ ቀን)
2.ቅድስት ኄራኒ ሐዋርያዊት (ሰማዕት)
3.ቡርክት ንግሥተ ሳባ (ልደቷ)
4.ቅድስት ዕሌኒ ንግሥት (ልደቷ)

† ወርኀዊ በዓላት
1.ቅድስት ድንግል እግዝእትነ ማርያም ወላዲተ አምላክ
2.አበው ጎርጎርዮሳት
3.አቡነ ምዕመነ ድንግል
4.አቡነ አምደ ሥላሴ
5.አባ አሮን ሶርያዊ
6.አባ መርትያኖስ ጻድቅ

††† " #ንግሥተ_አዜብ በፍርድ ቀን ከዚህ ትውልድ ጋር ተነስታ ትፈርድበታለች:: የሰሎሞንን ጥበብ ለመስማት ከምድር ዳር መጥታለችና:: እነሆም ከሰሎሞን የሚበልጥ ከዚህ አለ::" †††
(ማቴ. 12:42)

† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †


ቤተሰብ ይሁኑ

https://t.me/Sinksar
https://t.me/Sinksar
https://t.me/Sinksar
179 views21:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 21:40:48 በዛወርቅ አስፋው (ይቅርታ) Bezawork Asfaw የንስሀ መዝሙር

211 views18:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 21:40:20
204 views18:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 20:53:06
209 views17:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 11:18:19 ዩቱይብ እየገባችሁ አበረታቷቸው።
የቀሲስ ሰለሞን የመጀመሪያ ስራቸው ነው።
እግዚአብሔር ቀሪ ጊዜያቸውን የሚያገለግሉበት እድሜ እና ጤና ይስጥልን።


222 viewsedited  08:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 06:45:02

216 views03:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 20:18:39 *ከመረጥሁት ጋር ቃልኪዳኔን አደረግሁ*።
መዝሙረ ዳዊት 89 : 3

*በዚህች ዕለት እግዚአብሔር አምላክ ለእናትነት ለመረጣት ለንጽሕት ቅድስት ድንግል ማርያም የገባላትን የምህረት ቃል ኪዳን እንዘክራለን። በእውነቱ እመብርሃንን ስለተቀበለችው ፍጹም ቃል ኪዳን በየወሩ 16ኛ ቀን ኪዳነ ምህረት ብለን በቅድስት ቤተክርስቲያን በክብር እንዘክራታለን።*

*እውነት ነው እግዚአብሔር አምላካችን ቃል ኪዳን የገባው ለመረጣቸው ብቻ ነው። የኪዳነ ምህረት መመ ረጥ ደግሞ ልዩ ነው: ቅዱስ ዳዊት እንዲህ ብሎ እንደዘመረላት፦*

*እግዚአብሔር ጽዮንን መርጦአታልና፥ ማደሪያውም ትሆነው ዘንድ ወድዶአታልና፥ እንዲህ ብሎ፦*

*ይህች ለዘላለም ማረፊያዬ ናት፤ መርጫታለሁና በዚህች አድራለሁ።*
    መዝ 131(132)

*እንግዲህ የምህረት ቃል ኪዳንን ታላቅ እውነት እንረዳና እንጠቀምበት ዘንድ ከዚህ በታች ያለውን ምንባብ ከልባችን በማንበብ እንድንገነዘበው ቅድስት ሥላሴ ምስጢሩን ይግለጡልን።*

   *ቀስቲቱም በደመና ትሆናለች፤ በእኔና በምድር ላይ በሚኖር ሥጋ ባለው በሕያው ነፍስ ሁሉ መካከል ያለውን የዘላለም ቃል ኪዳን ለማሰብ አያታለሁ።*
ኦሪት ዘፍጥረት 9 : 16

*እግዚአብሔርም ኖኅን በእኔና በምድር ላይ በሚኖር ሥጋ ባለው ሁሉ መካከል ያቆምሁት የቃልኪዳን ምልክት ይህ ነው አለው* ።
ኦሪት ዘፍጥረት 9 : 17

*ከመረጥሁት ጋር ቃልኪዳኔን አደረግሁ፥ ለባሪያዬም ለዳዊት ማልሁ* ።
መዝሙረ ዳዊት 89 : 3

*እውነት ነው አምላካችን እግዚአብሔር ከመረጣቸው ጋር ቃል ኪዳን ገብቷል። ለምሳሌ ለአባታችን ለአብርሃም እንዲህ ብሎ ቃል ኪዳን ገብቶለታል፦*

(ዘፍጥ 12 )
------------
1 *እግዚአብሔርም አብራምን አለው፦ ከአገርህ ከዘመዶችህም ከአባትህም ቤት ተለይተህ እኔ ወደማሳይህ ምድር ውጣ።*

2 *ታላቅ ሕዝብም አደርግሃለሁ፥ እባርክሃለሁ፥ ስምህንም አከብረዋለሁ፤ ለበረከትም ሁን፤*

3 *የሚባርኩህንም እባርካለሁ፥ የሚረግሙህንም እረግማለሁ፤ የምድር ነገዶችም ሁሉ በአንተ ይባረካሉ።*

*ይገርማል* !

*እግዚአብሔር አምላክ ለአብርሃም ይህን የመሰለ ታላቅ ቃል ኪዳን የገባለት ለምንድን ነው? መልሱ፦ አብርሃም የእግዚአብሔር ሰው ስለ ነበረ ነው።*

*እመቤታችን  ቅድስት ድንግል ማርያም ደግሞ የአብርሃም አምላክን 9 ወር ከ5 ቀን በማህጸኗ የተሸከመች ናት! የአብርሃም አምላክን የወለደች ናት! የአብርሃም አምላክን ጡት ያጠባች ናት! የአብርሃም አምላክን በጀርባዋ አዝላ፣ በክንዷ ታቅፋ ጉንጮቹን እየሳመች በመአዛው ፍጹም ደስታ እያደረገች ያሳደገች ናት! የአብርሃም አምላክን 3 ዓመት ከ6 ወር በጀርባዋ አዝላ ከእስራኤል ወደ ግብጽ ከዚያም ወደ ኢትዮጵያ የተሰደደች ናት! የአብርሃም አምላክን 33 ዓመት ከ3ወር አብራው የኖረች ናት! የአብርሃም አምላክ በመስቀል ሲሰቅል መስቀሉ ስር ተገኝታ በመሪር የሀዘን ጦር የተወጋች ቃል ኪዳንም የተቀበለች ናት!*
*ይህ ሁሉ የሆነው ቅዱስ ዳዊት በትንቢት እንደተናገረ በእርሱ በእግዚአብሔር ከአለም ሁሉ ተለይታ የተመረጠች ስለ ሆነች ነው።*

*እግዚአብሔር ጽዮንን መርጧታል  ማደሪያውም ትሆነው ዘንድ ወዷታል* ::
መዝሙረ ዳዊት 132 : 13

*እናም ለተመረጠች እናቱ እግዚአብሔር አምላክ የገባላት ቃል ኪዳን ለአብርሃም ከገባው ቃል ኪዳን የላቀ ነው። እርሷ ከአብርሃም ትበልጣለችና! በስምሽ ለተራበ ያበላ፣ ለተጠማ ያጠጣ፣ ለታረዘ ያለበሰ፣ ቤተ ክርስቲያን ያሳነጸ፣ የታመመውን የታሰረውን የጎበኘ፣ ለቤተ ክርስቲያን ጧፍ እጣን ዘቢብ እና ንዋየ ቅድሳት የሰጠ እምርልሻለሁ የዘላለም ህይወት እሰጠዋለሁ: ብሎ ታላቅ የምህረት ቃል ኪዳን ገብቶላታል።*

*እናም እግዚአብሔር ለመረጣት ቅድስት እናቱ የምህረት ቃልኪዳን ( ኪዳነ ምህረት ) እያሰብን፤  ፍጹም ቃል ኪዳን በገባላት በተወደደ ልጇ ፊት ከፍጥረት ሁሉ የተመረጠች እናታችን ኪዳነ ምህረት በአማላጅነቷ እንድትቆምልን በዚህች ወርሃዊ የኪዳነ ምህረት በዓል በፊቷ እንቁም:: ሀገራችን፣ ቤተ ክርስቲያናችን እና ህዝበ ክርስቲያኑ ከገባንበት ታላቅ ፈተና እናታችን ኪዳነ ምህረት በተወደደ ልጇ ፊት ቆማ ምህረቱን ታሰጠን::                     በርትተን በኪዳነ ምህረት ፊት ቆመን እንጸልይ ዛሬም ያለንበት ወቅት እጅግ እጅግ እጅግ በጣም ከባድ ወቅት መሆኑን ዛሬም ደግሜ አሳስባለሁ።*

*ብሩህ  ቀን*
219 views17:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 06:27:53



129 views03:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ