የሰርጥ አድራሻ:
ምድቦች:
ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች:
2.24K
የሰርጥ መግለጫ
👉የቀኑ አዳዲስ ቀናዊ ውሎዎች ዜናዎች እንደደረሱ እናቀርብሎታለን
👉የደረሱንን ዜናዎች አጠናክረን እናቀርባለን
👉ስለ ሴንጆ ፕሪምየር
ሊግ ውጤቶች እናወራለን
👉ትኩስ ዜና ካሎት ለቦቱ ይላኩ ቢቻል ከፎቶ እና ከነ ሙሉ መረጃው ብትልኩልን ምርጥዬ ነው
ብቻ እርሶ ቻናላችንን ሼር ያርጉ
ሀሳብ አስተያየቶን @senjonewsgp
ያድርሱን @senjonewssbot
Ratings & Reviews
Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.
5 stars
0
4 stars
0
3 stars
2
2 stars
0
1 stars
0
የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3
2022-07-14 17:51:48
በየትኛውም የስራ ሰዓቶች ብትሄዱ ዩኒፎርሙን የሚለኩላችሁን አካላት ማግኘት ትችላላቹ
748 views14:51
2022-07-14 17:49:03
ስለ ክረምት
የቅዱስ ዮሴፍ አዳማ የ2014 ዓ.ም የትምህርት ዘመን መጠናቀቁን ተከትሎ በዚህ ክረምት ለተማሪዎቹም ሆነ ከሌላ ቦታ መተው መማር ለሚፈልጉ ተማሪዎች የክረምት ትምህርትን በማዘጋጀት ሰኞ ሀምሌ 11 የሚጀምር ይሆናል
በመሆኑም የክረምት ትምህርት ለመማር ፍላጎቱ ኖሯቹ እስካሁን ያልተመዘገባቹ ተማሪዎች ከዚህ ቀደም የለቀቅናቸውን ዜናዎች በመመልከት ምዝገባችሁን መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን
አዲስ ተማሪ ሆናቹ የክረምት ትምህርት ለመከታተል እና ለቀጣይ አመት በትምህርት ቤቱ ለመቀጠል ፍላጎቱ ያላቹ አዲስ ተማሪዎች ትምህርት ቤቱ ከክረምት ትምህርት በኋላ የአዲስ ገቢ ተማሪዎችን ጥያቄ መቀበል ስለሚጀምር ስለ ትምህርት ቤቱ ለማወቅ የክረምት ትምህርቱን ብትማሩ መልካም ነው
ነገር ግን የክረምት ትምህርቱን ስለተማራቹ ብቻ ትምህርት ቤቱን ትቀላቀላላቹ ማለት አይደለም ያ የሚሆነው ትምህርት ቤቱ ባስቀመጠው መስፈርት መሰረት መሆን አለበት መስፈርቱም ከሌላ ትምህርት ቤት የመጡበት የውጤት መጠን ከ75% በላይ መሆን እና የክረምት ትምህርቱን ተከታትለው የሚያመጡት ውጤት ከ75% በላይ መሆን እና ትምህርት ቤቱ ለመግቢያ ፈተና ብሎ ያስቀመጣቸውን ፈተናዎች በተገቢው መንገድ ማለፍ ይጠበቅባቸዋል
ከላይ የተጠቀሱትን መስፈርቶች እና ከሌላ ትምህርት ቤት የመጡበት ፋይል በመመልከት ጥሩ ስነምግባር ያላቸው ተማሪዎች ከሆኑ ትምህርት ቤቱን መቀላቀል የሚችሉ መሆኑን ልናሳውቅ እንወዳለን
[ት/ቤቱ]
@senjonews
@senjonewsgp
745 views14:49
2022-07-14 17:33:57
እዛው ትምህርት ቤት ብታሰፉ በቀጣይ አመት ካላስፈላጊ እንግልቶች እና መጉላላቶች የምትድኑ ይሆናል
729 views14:33
2022-07-14 17:32:04
ዩኒፎርም
ቅዱስ ዮሴፍ አዳማ ለቀጣይ የትምህርት ዘመን ትክክል ነው ብሎ ያማነበትን ዩኒፎርም ጨርቅ እና ደረጃ አውጥቶ ለተማሪዎቹ አቅርቧል
እናም በቀጣይ አመት ተማሪዎች የሚለብሱት የዩኒፎርም ጨርቅ እና ደረጃውን እራሱ ትምህርት ቤቱ ዘንድ የሚገኝ ሲሆን የጨርቁን አይነት ለማወቅ እዛው ትምህርት ቤት ድረስ በመሄድ ነው መመልከት ትችላላቹ
የጨርቁን አይነት ከተመለከታቹ በኋላ ትምህርት ቤቱ ባቀረባቸው ሰፊዎች ጨርቁን ማሰራት እንደምትችሉ አልያም ሌላ ቦታ የማሰራት ሀሳብ ካላቹ የጨርቁን አይነት ት/ት ሄዶ በመመልከት ከውጩ ጨርቁን በመግዛት ማሰራት እንደምትችሉ ትምህርት ቤቱ ያሳውቃል
ነገር ግን ትምህርት ቤቱ ካስቀመጠው የጨርቅ አይነት ውጪ አሰርቶ የሚመጣን ተማሪ ትምህርት ቤቱ የማይቀበል መሆኑን ልትረዱ ይገባል
ሌላው የሸሚዝ አይነት ማንኛውም መሆን ይችላል ግን ያልሳሳ መሆን አለበት ሹራብም ግዴታ አይደለም
የጨርቁን ዋጋ እና የስፌት ብር እዛው በመገኘት መጠየቅ የምትችሉ መሆኑን ልናሳውቅ እንወዳለን
ሌሎች ጉዳዮች ሲኖሩ ይዘን ምንመለስ ይሆናል
[ት/ቤቱ]
@senjonews
@senjonewsgp
743 views14:32
2022-07-14 17:18:08
ምዝገባቹን ያላጠናቀቃቹ ነባር ተማሪዎች ነገ የመጨረሻ ነው
725 views14:18
2022-07-14 13:02:54
𝙱𝚛𝚎𝚊𝚔𝚒𝚗𝚐
@senjonews
@senjonewsgp
802 viewsedited 10:02
2022-07-12 22:37:44
የ2015 ዓ.ም የቅዱስ ዮሴፍ አዳማ ለተማሪዎቹ ወጥ የሆነ የዩኒፎርም ስርዓት እንደሚኖር በካርድ ቀን ለወላጆችም ለተማሪዎችም አሳውቋል
እናም ከላይ በምስሉ ላይ የዩኒፎርሞቹ ጠቅላላ ዋጋዎች ተቀምጠዋል
በተያያዘ ሹራብ አለመጨመርም ትችላላቹ ከጠቅላላ ዋጋው ላይ የሹራብ ዋጋውን መቀነስ ትችላላቹ
ማሳሰቢያ:- ዩኒፎርሙ የሚሰፋው በትምህርት ቤቱ ሀላፊነት ነው
መች መለካት እንደሚጀመር ወደፊት የምናሳውቃቹ ይሆናል
@senjonews
@senjonewsgp
1.0K views19:37
2022-07-12 21:02:16
ዉድ ቤተሰቦች ነገ እና ከነገወዲያ በንግድ ባንክ #1000320396054 በዚ አካውንት ቁጥር 260 birr natural 228 birr social አስገብታቹ ወንድም አማኑኤል ጋር መታቹ እንድታወራርዱ ስንል እናሳስባለን።
በተጨማሪ ደሞ የከፈላቹበትን ወረቀት ግዴታ ራሳቹ ነው ይዛቹ መምታት ያለባቹ ምትሞሉት ነገር እና ምፈርሙት ነገር አለ
630 views18:02
2022-07-10 22:41:47
ይሄ ከሀይ ስኩል ብቻ የተሰናበቱትን ነው የሚያሳየው ክቡራን
1.4K views19:41
2022-07-10 22:29:22
ለቀጣይ
ቅዱስ ዮሴፍ አዳማ ለ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የነባር ተማሪዎቹን ምዝገባ ነገ ሀምሌ 4 ይጀምራል
ምዝገባውም የሚከናወነው ከKG-12ክፍል ያሉትን የሚያካትት ይሆናል
ለ9ኛ ክፍል ተመዝጋቢዎች ከነገ ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 5 ቀናት ምዝገባችሁን አጠናቁ
ለ11ኛ ክፍል ተመዝጋቢ ተማሪዎች ደግሞ የማህበራዊ ሳይንስ እና የተፈጥሮ ሳይንስ ዘርፋችሁን በምዝገባው ቀን የምትመርጡ በመሆነ በቶሎ ምዝገባችሁን ብታጠናቅቁ መልካም ነው
በተጨማሪ ለክረምት ትምህርት ፈላጊዎች ደግሞ ብር 400 በመያዝ ትምህርት ቤቱ ቅጥር ግቢ በመገኘት ምዝገባችሁን መፈፀም ትችላላቹ
የነባር ተማሪዎችን የምዝገባ ሂደት ከዚህ ቀደም ጥንክራችን ላይ ገልፀነዋል መልስ ብላቹ መመልከት ትችላላቹ
በአዲስ ተማሪዎች የምዝገባ ጉዳይ አዲስ መረጃ የሚኖር ከሆነ የምናደርሳቹ ይሆናል
መልካም ጊዜ
@senjonews
@senjonewsgp
1.4K viewsedited 19:29