Get Mystery Box with random crypto!

|| Sᴇʟʟᴜ ᴀʟʟᴇ ɴᴇʙɪʏ ﷺ ||

የቴሌግራም ቻናል አርማ sellu_resul — || Sᴇʟʟᴜ ᴀʟʟᴇ ɴᴇʙɪʏ ﷺ ||
የቴሌግራም ቻናል አርማ sellu_resul — || Sᴇʟʟᴜ ᴀʟʟᴇ ɴᴇʙɪʏ ﷺ ||
የሰርጥ አድራሻ: @sellu_resul
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2
የሰርጥ መግለጫ

وَمَنْ أَحْسَنُ قَوْلًۭا مِّمَّن دَعَآ إِلَى ٱللَّه وَعَمِلَ صَٰلِحًۭا وَقَالَ إِنَّنِى
مِنَ ٱلْمُسْلِمِينَ
ወደ አሏህ ከጠራና መልካምንም ከሠራ እኔ ከሙስሊሞች ነኝ ካለም ሰው ይበልጥ ቃሉ ያማረ ማን ነው።
ISLAMIC KNOWLEDGE FOR ALL ©

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-09-27 11:06:11 ‍ "ሀፍሲ"
ክፍል ሶስት
ፀሐፊ፦ ኑዕማን ኢድሪስ

... ዴቭ ትክክለኛ ሰሙ ዳዉድ ነዉ። ዳዉድ ከመሆኑ (እስልምናን ከመቀበሉ) በፊት ዳዊት ነበር። አላህ ቀጥተኛዉን መንገድ የመራዉ ማህበራዊ ሚዲያ በሚጠቀምበት ወቅት የኡስታዝ አቡ ሀይደርን ትምህርት ተከታትሎ ነዉ። በተለይ ፖስተር ሀይሉ እና ኡስታዝ አቡ ሀይደር ያደረጉትን ሀይማኖታዊ ዉይይት በተመለከተ ጊዜ የእስልምና ትክክለኛነት ተገለጠለት። በቤተሰቦቹ ከፍተኛ ጫና ቢያድርበትም እስልምናን ከተቀበለ በኃላ እስላማዊ ዒልምን በማደን የእዉቀት አድማሱን አስፍቷል። አሁን ደግሞ ኸይር ስራዎች ላይ ለመሳተፍ የዐመሉን ሷሊህ ጀመዓ አባል ሆኗል።

ክፍት ወደሆነዉ ወንበር ሲቀመጥ ከሀፍሲ ፊት ለፊት ነበር። ሀፍሲን የሆነ ቦታ አይቷታል ነገር ግን የት እንዳያት ማስታወስ አልቻለም። ትዝ የሚለዉ ነገር እሷን ባያት ጊዜ አጠገቡ ለነበረዉ ጓደኛዉ ቆንጆ እንደሆነች ነግሮታል።

ሸኽ አጃኢቡ "እንግዲህ ሁሉም ተሟሉማ አደል?" አሉ ኡስማንን እያዩ። አይኑን ከሀፍሲ ላይ አልነቀለም። እሷም በተመሳሳይ በአይኗቿ ዴቭን አልተፍታችዉም።  "አዎ ተሟልተዋል። እንጀምር..." አለና "ለአዲሱ አባላችን ራሳችንን እናስተዋውቅና ሹራችንን እንጀምራለን" ብሎ ራሱን ማስተዋወቅ ጀመረ። "ኡስማን እባላለሁ በሒሳብ አያያዝ (አካዉንቲንግ) የመጀመሪያ ድግሪ ሲኖረኝ አሁን ላይ በንግድ ስራ ተሰማርቻለሁ።" ከሱ በመቀጠል የሀፍሲ ተራ ነዉ። ዴቭ የዚችን ዉብ ልጅ ማንነት ለማወቅ ጓጉቷል። "ሀፍሷ እባላለሁ። የክሊኒካል ፋርማሲ ተመራቂ ተማሪ ነኝ" በጣም አጭር ነበር። ዴቭ ማወቅ የፈለገበት ድረስ አልተጓዘችም። የትዳር ሁኔታ መገለጽ ነበረበት። ሁሉም በየተራ ራሳቸዉን ካስተዋወቁ በኃላ ኡስማን "በመጨረሻ አዲሱ የጀመዓችን አባል ራሱን ያስተዋውቀናል" በማለት እድሉን ለዴቭ ሰጠዉ።

"ዳዉድ እባላለሁ። ከአዳማ ዩኒቨርሲቲ በኮምፒዉተር ሳይንስ የተመረቅኩ ሲሆን አሁን በግል ድርጅት ዉስጥ ተቀጥሬ በመስራት ላይ እገኛለሁ።" በተመሳሳይ ሁኔታ ሀፍሲ ማወቅ የፈለገችዉን ዴቭ አልገለጸም። "ምናልባትም ባለትዳር ይሆናል" ብላ አሰበች።

.
.
.

"ደስ የሚል ጀመዓ ነዉ። እናንተን በመተዋወቄ ደስ ብሎኛል።" አለ ዴቭ። ከቢሮ እንደወጡ ሳሪ ዴቭንና ሀፍሷን አስተዋውቃቸዋለች። ስማቸዉን ድጋሜ ከመተዋወቅ የዘለለ ግን ሌላ ነገር አላወሩም።

"ሳሪ ወደ ሰፈር ነሻ?"
"አዎ ዴቭ ትሸኘናለህ?" አለችዉ የሀፍሲን ፍቃደኝነት ለማወቅ ወደሷ እየተመለከተች
"እኔም ወደሰፈር ነኝ። አብረን እንሂድ!" ብሎ መኪናዉን ከፈተላቸዉ።

"ዱሩን ገደሉን ባህሩን ጥሼ
ጥሪ ደርሶኛል ልምጣ መልሼ
የጉድጓዱን ጥግ ያን አስፈሪዉን
ያልፈዋል እግሬ ጥቁር ዋሻዉን
አልፈራም አልፈራም ........" ለስራና ለወኔ የሚያነሳሳዉን ተወዳጅ ነሽዳ በትንሹ ተከፍቶ እያዳመጡ ነዉ። ከሶማሌ ተራ ተነስተዉ ወደ ጦር ሀይሎች እያመሩ ነዉ። ሀፍሲ ምን እንደምታወራ ግራ ገብቷታል። ከኃለ ወንበር ሁና በመኪናዉ ስፖኪዮዎ በጨረፍታ ትመለከተዋለች። እሱም በተመሳሳይ ቀና እያለ ያያታል። በጣም ተፈራርተዋል። ድንገት አይኖቻቸዉ ሲገጣጠሙ ሁለቱም በድንጋጤ ያቀረቅራሉ። መተያየታቸዉ ያቁም እንጂ ልቦቻቸዉ የተገጣጠሙ ይመስላሉ።

... ለማፍቀር ማሰብ አያስፈልገዉም። ፍቅር በተፈጥሮ የሚለገስ ቅጽበታዊ የልብ መሻት ነዉ። አዎ! ሀፍሲ በጣም ብዙ ወንዶችን ታዉቃለች። በጓደኝነትም፣ ለትዳርም የሚመጡ አያሌ ናቸዉ። ነገር ግን ስለ ፍቅርም ሆነ ስለ ትዳር አስባም ሁና አልማ አታዉቅም። ከኡስማን የጋብቻ ጥያቄ ዉጭ ሁሉንም ፊት ለፊት እንደማትፈልጋቸዉ ነግራቸዋለች። የኡስማንን ጥያቄ ግን አሁንም አልመለሰችለትም።

ከሹራዉ ከመዉታቸዉ በፊት ሸኽ አጃኢቡ በጣም አስቸኳይ ለሆነ ሀጃቸዉ ፈልገዉት ኡስማን ሀፍሲን የማናገር እድል አላገኘም። አራት ወር ሙሉ ሲጠብቀዉ የነበረዉን የጋብቻ ጥያቄ መልሱን ሳያዉቀዉ አሁንም ሌላ ቀን ሊያስቆጥር ነዉ።

"ዴቭ እዚህ ልዉረድ ሀፍሲ ቤተል ስለሆነች እሷን ሸኛት። ደሞ ትዛዝ ነዉ።" ብላ እየሳቀች ከመኪናዉ ልትወርድ ስትል ሀፍሲ "ኧረ አታስቸግሪዉ በታክሲ መሄድ እችላለዉ።" አለች ለመግደርደር ያክል ነበር።
"በይ አትቅበጪ አዝዤዋለሁ ያደርስሻል"
"ታዛዥ ነኝ አለቃ!" የዴቭ መልስ ነበር።

ከፒያሳ ጀምረዉ ጦርሀይሎች እስከሚደርሱ ሳሪ ብቻ እያወራች ነበር። አሁን ግን ሳሪ ወርዳለች። ዴቭ በዝምታ ሊያስደብራት አልፈለገም።

"ዝምተኛ ነሽ ልበል። ጓደኛሽንኮ በወሬ አላገዝሻትም።" ወሬ ለመጀመር ያክል እንጂ እየፈራ ነበር።
"አይ ዝምተኛ እንኳ አይደለሁም!" አጭር መልስ ደነገጠ። የማዉራት ፍላጎት አይኖራት ይሆናል ብሎ በማሰብ በደጋሜ ፈራ ተባ እያለ "ያዉ የኔ ስራ ካንቺ ጋር ያገናኘዋል መሰል። የኮምፒዉተር ባለሙያ ስለሆንኩ የጀመዓዉን ስራዎች በማህበራዊ ሚዲያ ማስተዋወቅና ገንዘብ ማሰባሰብ ነዉ"
"ልክ ነህ በጥሩ ሁኔታ እንደምሰራ ተስፋ አደርጋለሁ!" ሀፍሲ ስለጀመዓዉ ከልቧ ትጨነቃለች። ሰዉ መርዳት ያስደስታታል። የተቸገሩ ሰዎች በሷ ምክንያት ሲያገኙ፤ ለተከፉ ሰዎች የሳቅና የደስታ ሰበብ መሆን ሁሌም ምትመኘዉ ነዉ።
"ኢንሻ አላህ ከአላህ ጋር ጥሩ እሰራለሁ ብዬ አስባለሁ። ስለዚህ አንዳንድ መረጃዎች ካንቺ እፈልጋለሁ"
"እዚጋ ልዉረድ?" አለችዉ። ደነገጠ። ከጦር ሀይሎች ቤተል ቅርብ መሆኑን ዘንግቶት ብዙ እንጓዛለን ብሎ አስቦ ነበር። መኪናዉን የመንገዱን ዳር ካስያዘ በኃላ ወደሷ ዙሮ በደንብ አያት እዉነትም ዉብ ነች። "ጨረቃ የጥቁሩ ሰማይ ድምቀት እንደሆነችዉ ሁሉ ሀፍሲ ለዚች አለም ዉበት ናት።" ብሎ አሰበ።
"ስልክ ቁጥርሽን ስጭኝና ሚያስቸግረኝ ነገር ካለ እየደወልኩ እጠይቅሽለሁ።"

ክፍል አራት ይቀጥላል......

SHARE
ቻናላችንን ሼር በማድረግ ያበረታቱን።
╔════════════╗
JOIN: @SELLU_RESUL
JOIN: @SELLU_RESUL
13 viewssᴇɪᴅ , 08:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-26 07:04:27
@SELLU_RESUL
SHARE

ከወደ #ፓኪስታን ገራሚ ዜና ተሰምቷል

ባለፈው በጣለው ከባድ ዝናብ ምክንያት ብዙ ሰዎች እንደሞቱ እና ብዙ ንብረት እንደወደመ የሚታወቅ ነው።

የፓኪስታን አቃቢ ሕግ እኒህን የመስጅድ ኢማም ለሞቱ ሰዎች እና ንብረት ተጠያቂ ናቸው ብሎ በቁጥጥር ስር አውሏቸዋል ።

ምክንያቱም ለዝናብ ሶላተል #ኢስቲስቃ ማለትም ዝናብ ሲቀር የሚሰገደውን ሶላት አሰግደሀል በሚል ነው።

ምንጭ አቡ ሀሊድ

SHARE
ቻናላችንን ሼር በማድረግ ያበረታቱን።
╔════════════╗
JOIN: @SELLU_RESUL
JOIN: @SELLU_RESUL
129 viewssᴇɪᴅ , edited  04:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-26 07:02:18 ስለ ሰው ልጅ ክህደት የአላህ ፍጥረቶች ምን አሉ?
"
ምድር በየቀኑ እንዲህ በማለት ጌታዋን ትጣራለች፦ «ጌታዬ ሆይ የሰው ልጅን ልዋጠው ፍቀድልኝ እርሱኮ ያንተን ሲሳይ እየበላ አያመሰግንህም»

ተራራም እንዲህ በማለት የጌታዋን ፍቃድ ትጠይቃለች፦ «ጌታዬ ሆይ የሰው ልጅን ላጣብቀው ፍቀድልኝ እርሱኮ ያንተን ሲሳይ እየበላ አያመሰግንህም»

ባህርም በተራዋ «ጌታዬ ሆይ የሰው ልጅን እንዳሠምጠው ፍቀድልኝ ፣እርሱ ያንተን እርዚቅ እየበላ አያመሰግንህም» ትላለች

ሰማይም «ጌታዬ ሆይ የሰው ልጅን አንዳች መቅሰፍት ላውርድበት ፍቀድልኝ እርሱ የአንተን ሲሳይ እየበላ አያመሰግንህም» በማለት ትጣራለች።

#አሏህም « ፍጥረቶቼ ሆይ,,,, የሰው ልጅን የፈጠራችሁት እናንተ ናቹህን»? ይላቸዋል

«#ጌታችን #ሆይ አይደለም» ይላሉ ጥራት የተገባው አሏህም እንዲህ ይላል፦ እናንተ ብትፈጥሯቸው ታዝኑላቸው ነበር።

የነሱን ጉዳይ ተውልኝ እስኪ ከነሱ ወደኔ የተመለሰ (የተፀፀተ) እኔ ወዳጁ ነኝ። እኔኮ እናት ለልጇ ከምታዝነው በላይ ለባሮቼ አዛኝ ነኝ። ከነሱ ወደኔ ተፀፅቶ የተመለሰ «አንተ ተውበት አድራጊ ሆይ
እንኳን ደህና መጣህ ብየ ከርቀት እቀበለዋለሁኝ ።

ወንጀል ሰርቶ ከኔ ለሚሸሸው ደግሞ፦ ወደርሱ ቀርቤ ፦ ባርያዬ ወዴት ነው የምትሄደው ከእኔ ውጭ ሌላ ጌታ አገኘህን፤ ከኔ ውጭስ ሌላ አዛኝ የሆነ ጌታ አገኘህን የምትሸሸኝ »በማለት እጠራዋለሁኝ።

ጌታዬ ሆይ ከርቀት የምትቀበለው ወዳንተ ተመላሽ ባርያ አድርገን።አሚን

SHARE
ቻናላችንን ሼር በማድረግ ያበረታቱን።
╔════════════╗
JOIN: @SELU_RESUL   
JOIN: @SELLU_RESUL
103 viewssᴇɪᴅ , 04:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-26 06:59:21 ይህን ያውቁ ኑሯል

ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ኢስራ ወል ሚዕራጅ ደርሰው ሲመጡ በየሰማያቱ እነማንን እንዳገኙ...

:➊. 1ኛ ሰማይ ላይ ያገኙት ነብዩላህ አደም (ዐ.ሰ)

➋. 2ኛ ሰማይ ላይ ያገኙት ነብዩላህ የህያ (ዐ.ሰ) እና ኢሳ(ዐ.ሰ)

➌. 3ኛ ሰማይ ላይ ያገኙት ነብዩላህ ዩሱፍ (ዐ.ሰ)

➍. 4ኛ ሰማይ ላይ ያገኙት ነብዩላህ ኢድሪስ (ዐ.ሰ)

➎. 5ኛ ሰማይ ላይ ያገኙት ነብዩላህ ሃሩን ቢን ኢምራን (ዐ.ሰ)

➏. 6ኛ ሰማይ ላይ ያገኙት ነብዩላህ ሙሳ ቢን ኢምራን (ዐ.ሰ)

➐. 7ኛ ሰማይ ላይ ያገኙት ነብዩላህ ኢብራሂም (ዐ.ሰ)……ናቸው፡፡

   SHARE
ቻናላችንን ሼር በማድረግ ያበረታቱን።
╔════════════╗
JOIN: @SELLU_RESUL  
101 viewssᴇɪᴅ , 03:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-25 14:25:17 ‍ "ሀፍሲ"
ክፍል ሁለት
ፀሀፊ፦ ኑዕማን ኢድሪስ

"... ሀፍሲ ላገባሽ እፈልጋለሁ። ታገቢኛለሽ?" ብሎ ጠየቃት።
በጣም ፈራች። ኡስማን እስካሁን ከምታዉቃቸዉ ወንዶች ሁሉ የተሻለ ነዉ። አላማ ያለዉ፤ ዲኑን የሚኻድም፤ የዱንያ ሪዝቅም የማይጎለዉ ሊወደድ የሚችል ወንድ ነዉ። ነገር ግን ይሄንን ጥያቄ ከዚህ በፊት ይጠይቃት እንጂ ተመሳሳይ ጥያቄዎች በቤተሰቧችና በጓደኟቿ በኩል ስለሚመጡ የኡስማንን ጥያቄ አስታዉሳዉ አታቅም።
"... ኡስሚ" አለች እየፈራች። "እስካሁን ከማዉቃቸዉ ወንዶች አንተ የተሻልክ ነክ ቢሆንም በዚህ አመት ተመራቂ ተማሪ እንደሆንኩ ታዉቃለህ። በዚያ ላይ የጀመዓዉ ስራም ስላለ ጊዜ ከመጣበቡ የተነሳ ያንተ ጥያቄ ትዝ ብሎኝ አያዉቅም። በጣም ይቅርታ ኡስሚ አሁን ግን ልረዳክ እፈልጋለሁ ጊዜ ስጠኝ ልሰብበትና ቀጣይ ወር ስንገናኝ መልሱን እነግረሀለሁ።" ብላዉ ከተቀመጠችበት እየተነሳች "ኡስሚ ሳሪ እየጠበቀችኝ ነዉ ልሂድ"
"እሺ ሂጂ አታስቁሚያት ስንገናኝ ግን መልስሽን እጠብቃለሁ።" ብሏት ተሰነባብተዉ ከቢሮዉ ወጣች።

ኡስማን ሀፍሲን ሲበዛ ይወዳታል። እሷን የማያስብበትና የማይመኝበት አንዲትም ደቂቃ አታልፍም። ነገር ግን ግኑኝነታቸዉ በሀላል እንዲሆን ስለሚፈልግ ለትዳር ከመጠየቅ ዉጭ ለስራ ሲደዋወሉም ሆነ ሲገናኙ በጣም ጥንቃቄ ያደርጋል።

... ለረጅም ሰአት ቢሮ ዉስጥ ተቀምጦ "ቀጣይ ወር ስንገናኝ ምን ትመልስልኝ ይሆን?" እያለ ያስባል። ረጅሙን የሀሳብ ጉዞ ተጉዞ ሀፍሲ እሱን ለማግባት ፍቃደኛ ሁና፤ ሽማግሌ ልኮ፤ አግብቷት፤ በደስታ የፍቅር ህይወት እየኖሩ፤ ሚያማማሩ ልጆች ወልደዉ ከልጆቻቸዉ ጋር አብረዉ እየተጫወቱ፤  የሞቀ ቤት ዉስጥ የሞቀ ፍቅር እየተጎነጩ ....... በመሀል ብንን አለና በራሱ ተገረመ። "ሰዉ ተኝቶ ብቻ ሳይሆን ቆሞም ያልማል" ብሎ በመደነቅ ፈገገ። እንደገና መለስ ብሎ ያለመዉ ሁሉ እዉን እንዲሆንለት አንገቱን ወደ ላይ ቀና በማድረግ "ኢላሂ ምርጫዋ አድርገኝና ምኞቴን አሳካልኝ" ዱዐ አደረገ።

... ቀናቶች እየሄዱ ነዉ። ሀፍሷ ተመራቂ ተማሪ በመሆኗ ጥናቴዊ ፅሁፏ ላይ ሙሉ ቀኗን ታሳልፍለች። ማታ ደግሞ ለጀመዓዉ ገቢ እንዴት ማሰባሰብ እንዳለባት በማሰብ እናትና አባቷን በኸይር ስራዉ ላይ ታሳትፍቸዋለች። ታማክራቸዋለች። የሀፍሲ አባት ነጋዴ ስለሆነ ሀብታም ከሚባሉት ዉስጥ ነዉ። ብዙ አህለል ኸይራቶችንም በአባቷና በአባቷ ጓደኞች በኩል ስለምታገኝ ገቢ በማሰባሰቡ ረገድ ሀፍሲ የጀመዓዉ የጀርባ አጥንት ነች።
በዚህ ወር ብቻ በሷ በኩል እስከ ስድሳ ሺህ ብር መሰብሰብ ስለቻለች በሹራዉ ወቅት የምታቀርበዉን ሪፖርት በማዘጋጀት ላይ ነች።

ሪፖርቱን በፅሁፍም ጭምር ስለሆነ የሚያቀርቡት ከምሽቱ ሁለት ሰአት አከባቢ አልጋዋ ላይ ተቀምጣ ላፕቶፗን ከፈተች። ነገር ግን ቀኑን ሙሉ ለጥናታዊ ፅሁፏ መረጃ ለማግኘት ቃለ-መጠይቅ ስታደርግ ስለዋለች ድክም ብሏታል። መጻፍ ግዴታ ስለሆነ ብቻ ትንሽ ለመጻፍ እየሞከረች ተንቀሳቃሽ ስልኳ አቃጨለ " ላ ላ  ላ ነህታጁል ማላ ከይነዝዳዱ ጀማላ..." የሚለዉ የሀሙድ ነሽዳ ነበር። ስልኳን ስትመለከተዉ የኡስማን ቁጥር ነበር።
"ሄሎ ኡስሚ"
"አሰላሙዓለይኩም ሀፍሲ"
"ወአለይከሰላም" ... ሰላምታ ከተለዋወጡ በኃላ
"ሀፍሲ እሁድ ጧት 2:30 ሹራ አለ። መቅረት አይቻለም።" ብሎ ቆፍጠን ያለ ትእዛዝ አስተላለፈ።
"እ ዛሬ ቀኑ ማን ነዉ?" ሁኔታዎች ከመደራረባቸዉ የተነሳ ቀኑ ሁሉ ጠፍቶባታል።
"አሁን ጁመዓ ሚረሳ ቀን ነዉ?"
"እ.. እሺ ትንሽ ቢዚ ስለሆንኩ ነዉ ኡስሚ አልቀርም ኢንሻ አላህ!" ብላዉ ተሰነባበቱ። ደክሟትም ስለነበር ብዙም ሳታናግረዉ፤ የጀመረችዉን ፅሁፍ ሳትጨርስ እንቅልፍ ተኛች።
.
.
.
... ዛሬ እሁድ ነዉ። ሀፍሲ ማቅረብ ያሉባት ሁለት ሪፖርቶች አሉ። አንደኛዉን በደንብ አድርጋ ፅፋለች። ሁለተኛዉን ግን ወሩን ሙሉ ረስታዉ ወደ ሹራ ለመሄድ ከቤት ስትነሳ ነዉ ያስታወሰችዉ። በራሷ አፈረች። "በቁም ነገር ጠይቆኝ እንዴት ስለሱ ማሰብ አቃተኝ?" ብላ ራሷን ወቀሰች።  ትንሽ ከተረጋጋች በኃላ እንደገና ስላቀረበላት ጥያቄ ማሰብ ጀመረች። አስር ደቂቃ በማይሞላ ጊዜ ዉስጥ ግን መልሷ "አይሆንም" እንደሆነ ወሰነች!። መግደርደርም ሆነ እሱን ማስጠበቅ አልፈለገችም። "ለሱ  ከወንድምነትና ከጀመዓ አሚርነት የዘለለ አመለካከት የለኝም። ስለዚህ አልሆነዉም!።"

ሸኽ አጃዒቡ፣ ኡስማን፣ ሀፍሲ፣ ሙቤና ነኢማ በሹራ ሰአት ቀጠሯቸዉን አክብረዉ የተገኙ ሲሆን ሳሪና አዲሱ እንግዳ ዴቭ እየተጠበቁ ነዉ። ሁለቱ እስከሚመጡ ብለዉ ሸኽ አጃኢቡ ቀልድና ቁም ነገሩን እያዋዙ ያስቋቸዋል።
"ልጆቼ በስህተት መንገድ ላይ ያለን ሰዉ ስትመልሱ ሂክማን ተጠቀሙ..." ሸኽ አጃኢቡ አብዛኛዉ ሰዉ የሚያዉቃቸዉ ወጣቶችን ለስለስ ባለአንደበት ሲገስፁ፤ አንዳንዴም በቀልድ መልክ ጎንተል እያደረጉ ሲመክሩ ነዉ። ታድያ ሂክማን አብዘተዉ ይወዷታል።
"... አንድዎ ሸኽ ዘንዳ የኔ ቢጤ ደረሳ መፅሀፍ ተወሶ ሲመልስላቸዉ ኪታቡ ወጥ በወጥ አድርጎት ነበር። ታዲያ እኚህ ሸኽ ወጣቱን ክፉ ንግግር አልተናገሩቱም። እሱ እንዳስቀየማቸዉ እሳቸዉ አላስቀየሙትም። ዳግመኛ መፅሀፍ  ለመዋስ ሲመጣ የጠየቃቸዉን መፅሀፍ ሲሰጡት ከመጽሀፉ ጋር አክለዉ የወጥ ማድረጊያ ሰሀን ሰጡት... ማስተማር ማለት እንዲህም አይደል።" ብለዉ ለራሳቸዉ ፈገግ አሉ።

በመሃል ሳሪ "አሰላሙዓለይኩም" ብላ ወደ ቢሮ ገባች። ሁሉም አንድ ላይ "ወአለይኩም ሰላም" ብለዉ መለሱ። ሳሪ ከኃላዋ አስከትላዉ የገባችዉ ዴቭ ገና ሲገባ ነበር ትንሿን ቢሮ በተቀባዉ ሽቶ ያወዳት። ሁሉም አይናቸዉ እሱ ላይ አረፈ። በተለይ ሀፍሲ ፈዛ ቀረች። ክፍት ወደሆነዉ ወንበር ሂዶ እስከሚቀመጥ ድረስ አይኖቿን መንቀል አልቻለችም።

ክፍል ሶስት ይቀጥላል.....

 @SELLU_RESUL
@SELLU_RESUL
SHARE
142 viewssᴇɪᴅ , 11:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-25 10:33:06 ┏─━─━─━∞◆∞━─━─━─┓
                 ". #ሀፍሲ ".
   ✎ፀሐፊ፦ መግፊራ ቢንት ፉላን
┗─━─━─━∞◆∞━─━─━─┛
              #እውነተኛ_ታሪክ
┎━─━─━─━─━─━─━─━─━┒

        . ልብ አንጠልጣይ ታሪክ.
┖━─━─━─━─━─━─━─━─━┚
@SELLU_RESUL
┯━━━━━▧▣▧━━━━━┯
        #ክፍል_አንድ ʕ❶ʔ
┷━━━━━▧▣▧━━━━━┷

ፒፕፕፕፕፕፕፕፕፕፕፕ......................የታክሲው ጩሀት ከገባችበት ሀሳብ አባነናት ፤ወዴት መሄድ እንዳለባት እንኳን በቅጡ ሳትወስን ነበር ከቤቷ ብድግ ብላ የወጣችው። ለካንስ በሀሳብ ባህር ውስጥ ሰምጣ፤ አስፋልት መሀል ገብታለች፤ ምን ልትሰራ እዚህ መጣች? እሷም አታውቀውም እግሯን ተከትላ ለጊዜው አስፋልት መሀል ተገኝታለች፤ ልቧ እና አእምሮዋ ተጣልተውባት በእግሯ መመራት ከጀመረች ይሀው እንደቀልድ 5 ወር ሆናት። ከመኪና አደጋ ስታመልጥ ይህ የመጀመርያዋ አደለም፤ ጀሊሉ በቁድራዉ ይሸፍናታል እንጂ እንደሷማ ቢሆን ይሄኔ ቤተሰቦቿ እሷን በማስታመም እየማቀቁ ወይ ሰደቃ ሊያወጡላት ደረታቸው እየደቁ ነበር።
አይ ሀፍሲ ምን ይሆን እንደዚ ከጥንካሬሽ ማማ አውርዶ ዘጭ ያደረገሽ??
...............................................................................
ሀፍሳ ትባላለች በሰፈር ስሟ (ፈንዲሻዬ)  በጣም ሳቂታ ስለነበረች የሰፈር ሰው ሁላ ተስማምተው ያፀደቁት ሁለተኛ ስሟ ነው ከልጅነቷ ጀምሮ ጠንካራ ጥሩ ፀባይ ያላት ሰው አክባሪ ታዛዥ......... በቃ ጥሩ የተባሉ ነገሮች ሁላ እሷ ላይ አሉ ለቤተሰቦቿ የመጨረሻ ልጅ ለዚያውም ብቸኛ ሴት ናት እናቷ እድሌ ብለው ይጠሯታል አባቷ ደግሞ መድመቂያዬ ይሏታል ወንድሞቿ ለሰከንድ ተከፍታ አይደለም ደብሯት ማየት አይፈልጉም አለም ትገልበጥልኝ ካለች አለምን ለመገልበጥ ማይፈነቅሉት ድንጋይ የለም ልጅቷ ሀፍሲ ናታ የቤቱ እንቁ የቤቱ ድመቀት......................................
እሷ ግን እንደዚ አልነበረችም ቤተሰቦቿ እንዳቀበጧት ቀበጥ አይደለችም ጠንካራ ሴት መሆን የልጅነት ህልሟ ስለነበር አሁን እስካለችበት የአምስተኛ አመት የህክምና ትምህርቷ ድረስ ውጤቷን ለማንም ያላስደፈረች በት/ት ቤትም በኮሌጅ ቆይታዋም የተመሰገነች ጎበዝ ተማሪ ነበረች እናት እና አባቷ ዩኒቨርስቲ ገብታ እንድትመረቅ ቢፈልጉም የወንድ ልጆቻቸው ሀሳብ አሸንፎ ከፍተኛ ውጤት ብታመጣም እዚው አ.አ ቀርታለች የእድሜ እኩዮቿ በቤተሰቦቻቸው ሲመከሩ የሀጂ መሀመድን ልጅ አታይም እስቲ እንደሷ ሁኚ እየተባሉ ነበር።
..........................................................................

ሀፍሲ ለመጀመርያ ጊዜ ትጎዳለች፤ ከትምህርቷ ያዘናጋታል፤ አረ እንደውም ፀባይ ሁላ ልትቀይር ትችላለች፤ ተብሎ በቤተሰብም፤ በዘመድ አዝማድ፤ በሰፈርሰ ው፤ አጠቃላይ በሚያውቃት ሁሉ ተፈርቶ የነበረው የ1ኛ አመት ተማሪ ሆና አባቷ ጋሽ መሀመድ ሲሞቱ ነበር። ሀፍሲ ግን ሰው እንደጠበቃት አልነበረችም እንደውም ወንድሞቿን ተቆጪ እናቷን "ሰብር አድርጊ" ብላ ስታፅናና ነበር። "ለአባቴ ዱዐ እንጂ ለቅሶ አያስፈልገውም፤የሚወደው ይቅራለት፤ ዱዐ ያድርግለት" ብላ ሚያለቅሱትን ሁላ እያስቆመች በምትኩ ቁርዐን ትሰጣቸው ነበር።  "ሀዘኗን በውስጧ ይዛ ቤተሰቡን ለማፅናናት ነው እንጂ ሀፍሳማ ያባቷ ነገር እንዲ በቀላሉ አይወጣላትም" እያሉ ብዙዎቹ በግርምትም በማዘንም አምተዋታል። አንዳንዶቹ እናቷ ጋ እየመጡ "ዋ ይቺ ልጅሽን ተይ በያት ሀዘን በውስጧ አምቃ ቡሀላ የሆነ ነገር እንዳትሆንብሽ፤ አልቅሳ ቢወጣላት ነው ሚሻለው!" ብለው ስሞታ አቅርበዋል ሀፍሲ ግን ወይ ፍንክች ሀዘን ማመቅ የለ፤ መጎዳት የለ፤ ጠንክራ ቤተሰቡን ያጠነከረች ጀግና ሆነች፤ ቆይታ ሀዘኗን ይዛ እንዳትባል ይሀው አባቷ ከሞቱ 3 አመት አለፋቸው። ሀፍሲ ግን የድሮዋ ሀፍሲ ነበረች።
እና ዛሬስ ሀፍሲን ሚሰብር በሀሳብ የሚያዋዥቅ ከራሷ ሚያጣላ ምን ገጥሞት ይሆን .............
╬╬═════════════╬╬
   #ክፍል_ሁለት ʕ❷ʔ ይቀጥላል
╬╬═════════════╬╬

ቻናላችንን ለውዳጅ ዘመድዎ ሼር በማድረግ ስራዎቻችንን ያበረታቱ።
               . ↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴

@SELLU_RESUL
SHARE
          
142 viewssᴇɪᴅ , 07:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-24 21:32:59 ★#የነብዩ_ሙሐመድ_ﷺ_የሚስቶቻቸው_ስም

★زوجات الرسول ﷺ ﺇﻧّﻬﻦ ﺍﺛﻨﺘﺎ ﻋﺸﺮﺓ ﺯﻭﺟﺔً،
(١) ☜السيدة خديجة بنت خوليد
(٢)☜السيدة السودة بنت زمعة
(٣)☜السيدة عائشة بنت ابي بكر
(٤)☜السيدة حفصة بنت عمران
(٥)☜السيدة زينب بنت خزيمة
(٦)☜السيدة هند بنت أمية
(٧)☜السيدة زينب بنت جحش
(٨)☜السيدة جورية بنت الحارث
(٩)☜ السيدة ﻣﺎﺭﻳﺔ ﺍﻟﻘﺒﻄﻴﺔ  ﺑﻨﺖ ﺷﻤﻌﻮﻥ
(١٠)☜السيدة رملة بنت ابي سفيان
(١١)☜ السيدة صفية حيي بن اخطب
(١٢)☜السيدة ميمونة بنت الحارث

#የነብዩ_ሙሐመድ_ﷺ_ሚስቶቻቸው_12_ነው እነሱም፦

①☞ ሰይደቲ #ኸዲጃ    ቢንቲ ኹይሊድ
②☞ ሰይደቲ #ሰውዳእ  ቢንቲ ዘመዐህ
③☞ ሰይደቲ #አዒሻ      ቢንቲ አቡበክር
④☞ ሰይደቲ #ሓፍሷ     ቢንቲ ዒምራን ልጅ
⑤☞ ሰይደቲ #ዘይነብ    ቢንቲ ኹዘይማህ
⑥☞ ሰይደቲ #ሂንድ       ቢንቲ  አሚያህ
⑦☞ ሰይደቲ #ዘይነብ     ቢንቲ ጀሕሽ
⑧☞ ሰይደቲ #ጁወይሪያ ቢንቲ ሓሪስ
⑨☞ሰይደቲ #ማሪያ_አልቂብጢያ ቢንቲ ሸምዑን
10☞ ሰይደቲ #ረምላ       ቢንቲ አቡ ሱፍያን
11☞ ሰይደቲ #ሶፍያ       ቢንቲ ሓይይ
12☞ ሰይደቲ #መይሙና ቢንቲ ሓሪስ

★#የነብዩ_ሙሐመድ_ﷺ_ሚስቶች_መቼ_ሞቱ

ነብዩ ﷺ ሙሐመድ በህይወት እያሉ የሞቱት ሚስታቸ
( ١)☜خديجة بنت خويلد
(٢)☜زينب بنت خزيمة
①☞ #ኸዲጃ_ቢንቲ_ኹወይሊድ
②☞ #ዘይነብ_ቢንቲ_ኹዘይማ ፦ እነዚህ ሁለቶች ረሱል በህይት እያሉ ነው የሞተ ። ሌሎች #10ኞቹ ነብዩ ﷺ ሙሐመድ ህይወታቸው ካለፈች ቡኃላ ነው የሞቱት።

★ #ነብዩ_ሙሐመድ #ሰባት ልጆችአሏቸው።
#6ቱን ልጆች የወለዱት  ከሰይደቲ ኸዲጃ ነው። እነሱም፦
① #ቃሲም
② #ዐብዱሏ
③ #ዘይብ
④ #ሩቅያ
⑤ #ኡሙ_ኩልሱም
⑥ #ፋጡማ ናቸው።

★ #ነብዩ_ሙሐመድ #አንዱን ልጃቸውን የወለዱት ከማሪያ አል ቂብጢያ ነው።
እሱም፦
☞ #ኢብራሒም ነው።


★#የነብዩ_ሙሐመድ_ﷺ_ወንድ_ልጆቻቸው

★ﺃﻭﻻﺩ ﺍﻟﺮﺳﻮﻝ ﻋﻠﻴﻪ ﺍﻟﺼﻼﺓ ﻭﺍﻟﺴﻼﻡ
٢. ١ ﺍﻟﻘﺎﺳﻢ
٢. ٢ ﻋﺒﺪ ﺍﻟﻠﻪ
٢ . ٣ ﺇﺑﺮﺍﻫﻴﻢ
①☞ #ቃሲም
②☞ #ዐብዱሏህ
③☞ #ኢብራሒም

★#የነብዩ_ﷺ_ሙሐመድ_ﷺ_ሴት_ልጆቻቸው

ﺑﻨﺎﺕ ﺍﻟﺮﺳﻮﻝ ﻋﻠﻴﻪ ﺍﻟﺼﻼﺓ ﻭﺍﻟﺴﻼﻡ
٣. ١ ﺯﻳﻨﺐ
٣. ٢ ﺭﻗﻴﺔ
٣ . ٣ ﺃﻡّ ﻛﻠﺜﻮﻡ
٣. ٤ ﻓﺎﻃﻤﺔ
①☞ #ዘይነብ
②☞ #ሩቅያ
③☞ #ኡሙ_ኩልሱም
④☞ #ፋጡማ

★#የነብዩ_ሙሐመድ_ﷺ_ወንድ_ልጆቻቸው_መቼ_ሞቱ

ﻓﺈﻥ ﺃﻭﻻﺩﻩ ﺻﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻠﻴﻪ ﻭﺳﻠﻢ ﺍﻟﺬﻛﻮﺭ ﻭﻫﻢ  ﻟﻘﺎﺳﻢ ﻭﻋﺒﺪ ﺍﻟﻠﻪ ﻭﺇﺑﺮﺍﻫﻴﻢ ﺭﺿﻲ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻨﻬﻢ ﺟﻤﻴﻌﺎ، ﻛﻠﻬﻢ ﻣﺎﺗﻮﺍ ﺻﻐﺎﺭﺍ ﻓﻲ ﺣﻴﺎﺗﻪ ﺻﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻠﻴﻪ ﻭﺳﻠﻢ،

የነብዩ ﷺ ሙሐመድ ወንድ ልጆቻቸው
☞ #ቃሲም
☞ #ዐብዱሏህ
☞ #ኢብራሒም ሁሎችም  ነብዩ ﷺ ሙሐመድ በህይወት እያሉ ነው የሞቱት።

★ #የነብዩ_ሙሐመድ_ﷺ_ሴት_ልጆቻቸው_መቼ_ሞቱ

ﻭﺃﻣﺎ ﺑﻨﺎﺗﻪ ﺻﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻠﻴﻪ ﻭﺳﻠﻢ ﻓﺜﻼﺛﺔ ﻣﻨﻬﻦ ﺗﻮﻓﻴﻦ ﻓﻲ ﺣﻴﺎﺗﻪ ﺻﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻠﻴﻪ ﻭﺳﻠﻢ، ﻭﻫﻦ : ﺯﻳﻨﺖ ﻭﺭﻗﻴﺔ ﻭﺃﻡ ﻛﻠﺜﻮﻡ ﺭﺿﻲ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻨﻬﻦ، ﻭﺃﻣﺎ ﻓﺎﻃﻤﺔ ﺭﺿﻲ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻨﻬﺎ ﻓﻘﺪ ﺭﻭﻯ ﺍﻟﺒﺨﺎﺭﻱ ﻭﻣﺴﻠﻢ ﻋﻦ ﻋﺎﺋﺸﺔ ﺭﺿﻲ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻨﻬﺎ ﺃﻧﻬﺎ ﺗﻮﻓﻴﺖ ﺑﻌﺪ ﺃﺑﻴﻬﺎ ﺻﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻠﻴﻪ ﻭﺳﻠﻢ ﺑﺴﺘﺔ ﺃﺷﻬﺮ،

የነብዩ ﷺ ሙሐመድ ﷺ #ሶስቱ ሴት ልጆቻቸው
☞ #ዘይነብ
☞ #ሩቅያ
☞ #ኡሙ_ኩልሱም፦ እሳቸው በህይወት እያሉ ነው የሞቱት ።

ነገር ግን #ፋጡማ [ረዲየሏሃ ዐንሃ ] #ቡኻርይ_እና_ሙስሊም እንደዘገቡት የሞተችው #ነብዩ_ሙሐመድ ከ ሞቱ በ6 ስድስት ወሯ ነው።

نحبك يا رسول الله نحبك ياحبيب الله
@SELLU_RESUL
@SELU_RESUL
147 viewssᴇɪᴅ , 18:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-24 20:52:41 @SELLU_RESUL
@SELLU_RESUL


* كلام اعجبني ................../ካስገረሙኝ ንግግሮች/ *

عندما تولد لا تعلم
من الذي أخرجك من بطن أمك
ስትወለድ ከእናትህ ሆድ ያወጣህን ፈፅሞ አታውቅም።

وعندما تموت لا تعلم
من الذي أدخلك إلى قبرك
ስትሞት ማን ወደ ቀብርህ እንዳስገባህ ፈፅሞ አታውቅም።

* عجبا لك ياابن آدم*
* የአደም ልጅ ሆይ! ትገርማለህ።*

عندما ولدت تغسل وتنظف
ስትወለድ ትታጠባለህ፣ ትፀዳለህ።

وعندما تموت تغسل وتنظف
ስትሞት ትታጠባለህ፣ ትፀዳለህ።
* عجبا لك ياابن آدم*
* የአደም ልጅ ሆይ! ትገርማለህ።*

   عندما تولد لاتعلم من فرح واستبشر بك
ስትወለድ ማን በልደትህ እንደተደሰተ አታውቅም።

وعندما تموت لاتعلم من بكى عليك وحزن
ስትሞት ማን እንዳዘነና እንዳለቀሰ አታውቅም።

*    عجبا لك ياابن آدم*
* የአደም ልጅ ሆይ! ትገርማለህ*

في بطن أمك كنت في مكان ضيق ومظلم
በእናትህ ሆድ ውስጥ በጠባብ ቦታና በጨለማ ውስጥ ነበርክ።

وعندما تموت تكون في مكان ضيق ومظلم
ስትሞት ጊዜ በጠባብ ቦታና በጨለማ ውስጥ ትሆናለህ።

* عجبا لك ياابن آدم*
* የአደም ልጅ ሆይ! ትገርማለህ*

عندما ولدت تغطى بالقماش ليستروك
ስትወለድ በጨርቅ ትጠቀለላህ ሊሸፍኑህ!

وعندما تموت تكفن بالقماش ليستروك
ስትሞት በከፈን ይጠቀልሉሃል ሊሸፍኑህ!

عجبا لك ياابن آدم
የአደም ልጅ ሆይ! ትገርማለህ

عندما ولدت وكبرت يسألك الناس
عن شهادتك وخبراتك
በተወለድክና በአደግክ ጊዜ ሰዎች ምስክር ወረቀት ስለሙያህ ይጠይቁሃል።

وعندما تموت تسألك الملائكة عن عملك الصالح
በሞትክም ጊዜ መልዐኮች ስለመልካም ስራህ ይጠይቁሃል።

* فماذا أعددت لآخرتك  ؟*
*   ለመጨረሻው ሃገርህ ምን አዘጋጀህ?*

جرب تقولها من قلب :
آشهد آن لآ آله آلآ آلله
واشهد آن محمد رسول آلله
   ከልብህ ይህችን (ቃል) ለመናገር ሞክር! ከአላህ ሌላ በፍፁም የሚመለክ አምላክ እንደሌለ መስክር። እንዲሁም ሙሃመድ የአላህ መልክተኛ መሆናቸውን መስክር።

مستحيل تقرآها بدون ما ترسلها
ይህችን መልእክት ፍፁም ሳታነባት እንዳትልካት!

                    & & &
‏        بسم الله الرحمن الرحیم
*{ قل هو الله أحد * الله الصمد * لم يلد ولم يولد * ولم يكن له كفواً أحد }*

*ﺑﺴﻢ ﺍﻟﻠﻪ ﺍﻟﺮﺣﻤﻦ ﺍﻟﺮﺣﻴﻢ*
*{ በል! እርሱ አላህ አንድ ነው። አላህ (የሁሉ) መጠጊያ ነው። አልወለደም፤ አልተወለደምም። ለእርሱ አንድም ብጤ የለውም።}*

إرسل وتخيل في هالساعه
መልዕክቱን ላክ! ሰአትህን አስተውል

كم شخص يقرأ ثلث القرآن  بسببك لاتحرم نفسك مٍن الاجر
  በአንተ ሰበብ የቁርዓን አንድ ሶስተኛን ይቀራሉ (ያነባሉ)
ነፍስህን አጅር አትከልክላት!!!

ـ.                              
*ሼር በማድረግ አጅሩን ይካፈሉ*
174 viewssᴇɪᴅ , 17:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-24 20:22:51 ፈገግታ ሱና ነዉ፡፡

#ዛሬ የምነግራችሁ ስለ አንድ የዋህና ብልጥ ሸህ ታሪክ ነዉ፡፡ ሁለቱም የሚኖሩት በገጠሩ ክልል ሲሆን #ሸህየዉ አላገቡም ነበር፡፡ የዋሁ ሰዉየ ምንም ቁርአንም ኪታብም አልቀራም ጃሂል ነዉ፡፡

ሰዉየዉም በሰላም ሚስቱ ጋር እየኖረ ህልም ያያል ህልሙም ሚስቱን ሶስቴ ሲፈታት በህልሙ ያያል ....ሶስቴ መፍታት ከትዳር እንደተፋቱ ነዉ ሲሉ ሰምቶ እስኪ ለማንኛውም ልጠይቅ ይልና የሰፈሩን ሸህ ይጠይቃቸዋል፡፡

#ሰዉየዉ :- ሸሀችን በህልሜ ሚስቴን ሶስቴ ፈትቻት ነበር ፡፡ ምንድን ትሉኛለሁ ሲለቸዉ

#ሸህየዉም:- ያማ በህልምህ ስለፈታህ ግድ መፍታት አለብህ ይሉታል፡፡ከዛ ሰዉየዉም እያዘነ እነሸህ ካሉማ ምን ይደረጋል ይልና ይፈታታል፡፡

ከ ሁለት ወር ቡሀላ ያልታሰበ ነገር ተፈጠረ..የተፈታችዉን ልጅ ሸህየዉ ለራሳቸዉ የትዳር አጋር እንድትሆናቸዉ አገቧት፡፡

ጃሂሉም ሰዉየ ሰምቶ ተሸወድኩ ብሎ ነገሩን ተወዉ፡፡

አንድ በጣም የሚቀርበዉ ጓደኛዉ አልሰማም ነበር ,..ምንድን ነዉ የአንተን ሚስት #እነሸህ ጋር አየሇት እሳ ሲለዉ ...እሱም እኔማ በህልሜ ሶስቴ ስፈታት አይቼ እነሸህን ፈትዋ ጠይቂያቸዉ ፍቹ ግድ ነዉ ሲሉኝ ፈትቼ ኢሄዉ እሳቸዉ አገቧት ይለዋል፡፡

ጓደኛዉ  በሰማዉ ነገር ተናደደ ጓደኛዉ በጣም በሳልና ብልጥ ነበር..ና እኔን ጥልቆ ይዘህ ተከተለኝ ይለዋል ሁለቱም ጥልቆ ይዘዉ ሸህየዉ ቤት ይሄዳሉ ፡፡

ከዛ የሰዉየዉን ቤት ግርግዳ በጥልቆዉ መምታት ጀምሩ ..ከዛ ሸህየዉ ምንድን ነዉ ተዉ እንጂ ሲሏቸዉ ..ጓደኛዉ እነ ሸህ ዝም በሉማ...የሆነ ነገር ታይቶናል ይላቸዋል..,ከዛም ቤቱን ዝም ብለዉ በጥልቆ መምታቸዉን ቀጠሉ ..ከዛ

#ሸህየዉም አረ እባካችሁ ተዉ ቤቴን በጥልቆ መምታታችሁን ሲሉ .. የሰዉየዉ ጓደኛ ሸሀችን ወድጄ አይደለም ቤትሁን በጥልቆ የምመታዉ በህልሜ የአንቱን ቤት በጥልቆ ስመታዉ አይቼ ነዉ ይላቸዋል፡፡

ሸህየዉም በፍጥነት ህልም እኮ ዉሸት ነዉ ይሏቸዋል፡፡ የሰዉየዉ ጓደኛም ምን ቢል ጥሩ ነዉ
ህልም ዉሸት ከሆነ የጓደኛየን ሚስት መልሱ ፡፡ ብሏቸዉ እርፍ

መመለሷን አለመመለሷን አጣርተን እንነግራችሇለን፡፡

ምን ለማለት ፈልጌ ነዉ ፈትዋ የምንጠይቀዉ የምናማክረዉ የምናወያየዉ እና ሀሳብ የምናጋራዉን ሰዉ ለይተን ማወቅ አለብን።

ጨረስኩ

SHARE SHARE
╔════════════╗
JOIN:       
JOIN: @SELLU_RESUL    ╚════════════╝
161 viewssᴇɪᴅ , edited  17:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-23 21:55:23 Watch "መልካምነትኡስታዝ ያሲን ኑሩMELKAMINETUSTAZ YASIN NURU#HARIS_TUBE" on YouTube


1.2K viewsedited  18:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ