2022-07-16 16:18:18
#አስገራሚ_እውነት_ግን_ከጠላት.....
.........#ሙስሊም_ተማሪወች_ሆይ_አደራ...!!
➽እናንተ ተምራችሁ ቢሆን ኖሮ ዛሬ እኔ እዚህ ቦታ ባልተገኘሁ ነበር አለች።
(#ክርስቲያኗ_የህግ_ባለሙያ!!)
....ሙስሊም ወንድም እህቶቼ!!
ታውቃላችሁ ሁሌም ስኬታችሁ ስኬቴ እንደሆነ አስባለሁ የትም ቦታ በምንም ጉዳይ ሆነ በምንም ነገር ላይ እናንተ የበላይ ሆናችሁ ማየት ከልቤ ያስደስተኛል።
ወደ ጉዳዬ ስገባ አላውቅም ብቻ ግን በዚህች አለም ስትኖር ህይወት በራሷ ዛቢያ እያሽከረከረችህ ራሷው ጥያቄ አዘጋጅታ ትፈትንሀለች የሚገርመው ፈታኟም ራሷ ነች ፈተናውን በትዕግስት ካለፍክ ስኬት በምታቀርብልህ ሲሆን ፈተናውን በስርአት ካልተወጣህ ግን የበታችነትና የጭቆና ገፈት ቀማሽ መሆንህ አይቀሬ እንደሆነ በተግባር ታሳይሀለች።
ይገርማል ብቻ የአሏህን ውሳኔና ፈቃድ ሆኖ በተለያዩ ጊዜ ብዙ አይነት ገጠመኞች አሉኝ ....
....እናላችሁ በቅርቡ ከሁለት ቀን በፊት ወደ #ሐይቅ_ለሆነ ጉዳይ ጎራ ብዬ ነበር እና በዚያ አጋጣሚ የሔድኩበት የስራ ጉዳይ ሆነና ወደ በአካባቢው ወደ ሚገኝ #አስተዳደር ፅህፈት ቤት ጎራ አልኩኝ አብረውኝ #ሁለት_የዋህና_ገራገር ወጣቶች አሉ......!!
ከዚያም ሶስታችንም ተያይዘን ጉዳያችንን ለማስፈፀም ዘልቀን ወደ ውስጥ ገባንና በመስኮት የሆነችን #ክርስቲያን ሴት ማናገር ጀመርን ስለጉዳዩ አስረዳኋት ቀሚስ ለብሸ ስታይ ይሁን አላውቅም በጣም አመናጨቀችኝ ለመታገስ ሞከርኩ እንደምንም ወደ ሌላ ቦታ አመላከተችንና ተመለስን .....ስንመለስ ሁለቱ ወንድሞቼ የዛው የሀይቅ ልጅ ነበሩና አሁን የአንተን ቀሚስ አይታ እንጅ ስናውቃት እንድህ አልነበረችም አሉኝ ገረመኝና ጉዳያችንን እስክንፈፅም እንታገስ ብዬ ነግሬያቸው ከሔድንበት ቦታ የሆነ ወረቀት ይዘን ተመልሰን መጣን...።
#አሁን_ልብ_በሉ___
#ቁልፉ_እዚህ_አካባቢ_ነው።
ያዘዘችንን መረጃ አሟልተን ቀረብን ከባለፈው በተሻለ ሁኔታ ማናገርና ማስተናገድ ጀመረች...ከዚያም የሰጠናትን መረጃወች እያገላበጠች ሁለቱን ልጆች ስትጠይቃቸው የምትላቸውን ነገር ፈጥነው አልተረዱም እና እኔ ጉዳዩ ስለማይመለከተኝ ወደ ኋላ ነኝ ንግግሯ መሞቅ ሲጀምር ተጠጋሁ ማድመጥ ጀመርኩኝ ...
➽#አልተማራችሁምን!?
አለቻቸው አንገታቸውን ደፍተው ዝም አሏት.
እንዳልተማሩ ተረዳችና...ተናደደች..
ስሙኝ አለች በትኩረት ማድመጥ ጀመርኩ
እናንተ በዚህ እድሜያችሁ በጣም ፈጣን መሆን ሲኖርባችሁ..ግን አልተማራችሁም።
እስካልተማራችሁ ድረስ የማንም ታዛዥና አሽከር ትሆናላችሁ አሽከር የሆነ ሰው ደግሞ ከጭቆና ነፃ መሆን አይችልም።
የሰው ልጅ የመጀመሪያው ነፃነት ስለራሱ ራሱ መወሰን መቻል ሲጀምር ነው።
በዚህ እድሜያችሁ ጫት እየቃማችሁ ጊዜ ከማጥፋት እውቀት ብትሰበስቡ ለናንተ የተሻለ ነው።
ነገር ግን እጅህን ከስራ አዕምሮህን ከዕውቀት የፀዳ ካደረከው ሁሌም ከጭቆና ቀንበር ነፃ መውጣት አትችሉም።
እናንተ ተምራችሁ ቢሆን ኖሮ ዛሬ እኔ እዚህ ቦታ ባልተገኘሁ ነበር አለች።
....ቀጠለችና አውቃለሁ እናንተ ሙስሊሞች በስራ አትታሙም ጥሩ ሰራተኞች ናችሁ ሰርታችሁ ገንዘብ መያዝ ትችላላችሁ ግን ደግሞ በጣም ኋላ ቀር ናችሁ...
#ይህ_ቦታ_እናንተን_አይመለከትምን!?
#የሀገሪቱ_ሁኔታ_አይመለከታችሁምን!?
ከትምህርት ገበታ ርቃችሁ ሙስሊሙ ተጨቆነ ብትሉ በወሬ የሚቀየር ነገር የለም ምንም አይነት ፈተናና ጭቆና ቢደርስባችሁም እንኳን ስኬት ከጭቆና በኋላ ነውና የሚደርስባችሁን ነገር ሁሉ ችላችሁ መማር አለባችሁ።
........ያኔ እንደ ሌላው እኩል ቦታ ይኖራችኋል።
አልያ ግን በየ ሰፈሩ ጫት በመቃም የሚመጣ መብትም ሆነ እኩልነት የለም።
ገንዘብ ለማግኘት እንደምትሰሩ ሁሉ በሁሉም#የመንግስት ሴክተሮች ላይ ለሠሳተፍ ፀንታችሁ መማር አለባችሁ በማለት በምሬት ነግራናለች።
እናም እኔ ምንም አልጨምርም የኔን ሀሳብ እርሷ ተናግራለች ስለዚህ ወገኖቼ ሆይ እባካችሁ ጠንክረን እንማር አደራ...!!
አውቃለሁ ለሙስሊሞች ሁሉም ነገር አልጋ ባልጋ አይደለም ግን ቢሆንም መከራውን ጭቆነረውን በጥሰን እንሒድና ለተተኪው ትውልድ የሆነ ፈር ቀደንለት እንሔድ እላለሁ።
አደራ ጠንክረን እንማር አካዳሚክ እውቀትን የሚከለክሉ ሰወችን ፈፅሞ አትስሟቸው..ግን ደግሞ እምነታችሁን ተውሒድ ሱናችሁን ጠብቁ ለማለት እወዳለሁ።
የሴትዮዋ ንግግር ግን ወላሒ...
በጣም በጣም በጣም ነው የተሰማኝ !!
ኑር.......
http://t.me/nuredinal_arebi
3.3K viewsedited 13:18