Get Mystery Box with random crypto!

شـبـاب السـلـــفــــيــــيــن

የቴሌግራም ቻናል አርማ nuredinal_arebi — شـبـاب السـلـــفــــيــــيــن ش
የቴሌግራም ቻናል አርማ nuredinal_arebi — شـبـاب السـلـــفــــيــــيــن
የሰርጥ አድራሻ: @nuredinal_arebi
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 22.58K
የሰርጥ መግለጫ

#ሰለፍያ_ቀጥተኛ_የሀቅ_መንገድ_ብሎም_አይነኬ_ፅኑ_ተራራ_ነው
ለአስተያዬትና እርማት
@Nuredin_al_arebi_Bot

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-07-24 20:45:26 «ታሪክ ሰሪ ትውልድ»

የእውነት የሚዋደድ፤
ሁሌ እሚተዛዘን፡
በደሊል በሁጃ፤
በሐቅ የሚመዘን፡
ሰባብሮ የሚጥል፤
የኩፍርን ገመና፡
ተጠንቅቆ እሚቆም፤
ከብዶ እንደ ደመና፡
በተውሒድ የፀና፤
በእምነቱ እማይቀልድ፡
ናፈቀኝ ወላሒ፤
ታሪክ ሰሪ ትውልድ፡

«ኑሬ ነኝ ባይተዋሩ»

http://t.me/nuredinal_arebi
http://t.me/nuredinal_arebi
422 views17:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-24 14:32:46 ....ግጥሙን. ታሪክ ደጋሚ ሲመጣ እጨርሰዋለሁ ኢንሻ አሏህ

➺ታሪክ አልባ አይደለህም ቀና በል!!

በጠላቶችህ ድንፋታና ቀረርቶ አትረበሽ አንተው ራስህ ተዳክመህ እንጂ ዛሬ እነሱ ለ❺ ተከፋፍለው የያዟትን ሀገር ያለ አንዳች ኮሽታ ⓱አመት በጥበብ የመራ ጀግና ነበረህ ግን አንተው ተዳከምክና ጠላቶችህ ይፋጁብሀል።

➺...አሁንም ከነቃህ ግን ትደርሳለህ ተናበብ በእምነትህ ፅና ቀና በል!!

«አህመድ የሚባል ስም»

አስራ ሰባት አመት በፍትህ የመራ፡
ሞገሱ አስደማሚ ግርማው የሚያስፈራ፡
ጀግና የጀግና ዘር ተብሎ እሚጠራ፡
ስሙ አህመድ የሚባል ጨለማ አብሪ ኮከብ፡
በፍትህ የናደ የጠላትን መርከብ፡
-------------------------------------
ድንፋታሙን ሁሉ በጦር ያሸነፈ፡
የጠላትን ሴራ ፈጥኖ ያከሸፈ፡
በመሪነት ሚዛን ፕላን የነደፈ፡
ምን ስሙ ቢጠለሽ ክብሩ ያላደፈ፡
ለእምነቱ ታማኝ ሀቅን የገደፈ፡

«ሽንብራ-ኩሬ»ላይ አፄን ያደባዬ፡
አሞተ ቆፍጣና ጀግና ነው አባዬ፡
የአፄውን ስርዐት ገጥሞ የማረከ፡
በሀይማኖቱ ላይ ያልተፍረከረከ፡
ድል ያገኘ ጊዜ ያልሔደ ለበቀል፡
ሞራሉ ጢቅ ያለ የማይንቀለቀል፡
የኢስላም አንበሳ ቀድሞ የዘመነ፡
በእምነቱ ኩሩ በአንድ አሏህ ያመነ፡
በአፄው ስርዐት ላይ ዘንቦ የዳመነ፡

ይሔ ነው አባቴ ሁሌ ደስ የሚለኝ፡
አፄ ነኝ ለሚል በግ አብሪ ታሪክ አለኝ፡
ዘመናት ተሻግሮ ዛሬም የሚፈራ፡
ከታሪክ ድርሳን ላይ አብቦ ያፈራ፡
ለካሀዲያን ብዛት ለህዝብ ቆጠራ፡
ስልቱን አዘጋጅቶ አሏህን የጠራ፡
ጀግናው ኢማም አህመድ ተብሎ እሚጠራ፡

ዛሬም ነግሶ ያለ ይሔ ነው የኔ አባት፡
በሀረር በደቡብ በወሎ በዳባት፡
የካፊርን ደውላ ግራ የሚያጋባት፡
ከላይ ከታች ብሎ ፈጥኖ እሚያዋክባት፡
ስሙ አህመድ ይባላል እሱ ነው የኔ አባት፡

በፍቱን መዳኒት በሽታን የሚያክም፡
አዛኝና ትሁት ለሀገር የሚደክም፡
ያለ ምንም አድሎ ፍትህ ፈራጅ ዳኛ፡
የጦር ሜዳ አንበሳ ወታደር አርበኛ፡
የመሪነት ብቃት ያለው ጥበበኛ፡

ጣዖታትን ሁሉ አፍርሶ እሚያከስም፡
የሁሉ እኩል መሪ ጠላት የማይጎስም፡
ሀበሻን የመራ አህመድ የሚባል ስም፡

«ልጅ ሲተካ እጨርሰዋለሁ ኢንሻ አሏህ»

➺በኑረዲን አል አረቢ1444

http://t.me/nuredinal_arebi
http://t.me/nuredinal_arebi
1.6K viewsedited  11:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-24 13:47:41
1.7K views10:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-24 13:04:09ቆፍጠን በል አትልፈስፈስ!!

" الحياة مواقف .. وليست عشرة عمر."

ሕይወት ማለት አቋም እንጂ አሥር አመት እድሜ አይደለም።

http://t.me/nuredinal_arebi
1.8K views10:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-24 11:51:39 «ወዳጅ!!?

ቀን እስከሚያልፍ ወዳጅ ጥቅም ያገናኘው..
አንዱን ውሻ በላው አንዱን ጅብ ተመኘው።
በማስመሰል ብቻ ተጣምረው በግዳጅ፡
ካደረ አያመሽም የአሁን ጊዜ ወዳጅ፡

    ኑሬ ነኝ 

http://t.me/nuredinal_arebi
1.9K viewsedited  08:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-23 22:49:21ስሙማ ወዳጆቼ..!!

➙ማስተዋል የጎደለው ሰው ተናግሮት የነበረው ላይ ሲያተኩር....... አስተዋይ ሰው ግን በሚናገረ ነገር ላይ ያነጣጥራል፡፡

➙ሰፊ አስተሳሰብ ያለው ሰው ደግሞ ይቅርታው ላይ ያተኩራል፡፡

  ❝ይቅር ባይነት የጥሩነት መገለጫ ነው

➺አሏህ ይቅር የሚል ልብ እና ማስተዋል የሚችል አዕምሮ ያድለን አሚን፡፡


http://t.me/nuredinal_arebi
http://t.me/nuredinal_arebi
2.7K views19:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-23 21:25:28 السلام عليكم ورحمة الله وبركاته

ሰሞኑን የሸይኽ ሙሐመድ ገዛልን መታመም ተከትሎ ለህክምና የሚሆን ድጋፍ የተጠየቀ መሆኑ የሚታወስ ነው። አሁን ላይ - ምስጋና ለአላህ ይሁንና - ሸይኹ ጤናቸው እንደተመለሰ እያስታወስን ጉዳዩ አሳስቧችሁ በምትችሉት መንገድ ሁሉ ከጎናቸው የቆማችሁ ሁሉ አላህ እጥፍ ድርብ አድርጎ ይመንዳችሁ፣ ከፈተና ይጠብቃችሁ እንላለን።
1.8K views18:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-23 18:05:11 ኩሉ ዕወት ሰብ መሪሪ ታሪኽጉዕዞ አለዎ
ኩሉ መሪር ጉዕዞ ድማ አወት መፈፃምታ አለዎ
«ይላሉ ትግሬወች»እውነት ነው።
2.9K views15:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-23 17:28:57 ለሁላችንም ጥቆማ.....
ቆም ብለን እንየውማ!!

<=============>

❶]> ስማ ጀግናው ....ደጋፊዎች ተከታዮች አይደሉም ። ሰዎች ስለደገፉህም የያዝኩት እውነት ነው ብለህ መንቻካ አትሁን ፤ ምናልባት ዛሬ የሚጮሁልህ ዛሬን ሊረሱብህ ሊሆን ይችላልና አስተውል ተጠንቀቅ አትዝረክረክ ።
ሲያለቅሱልህም ቃልህ ማርኳቸው ሳይሆን የሞተ ዘመዳቸው ትዝ ብሏቸው ሊሆን ይችላልና አለቀሱ ብለህ ንግግርህን ድንበር አታሳጣው በመረጃ ተመጠን ቆፍጠን በል ። እውነትንም በደጋፊ ብዛት እንዳትመዝናት ተጠንቀቅ!!


❷]>ለእውነታ እንጂ ለይሉኝታ አትኑር ፤ ያን ስልህ የምትኖርበት ሕዝብና ባሕል ከእውነት ጋር እስካልተጋጨ መጋፋት የለብህም። ሠዎች የሚቀበሉህ ባሕላቸውን ስታውቅና ስታከብርላቸው ነው ።

❸]>ልጅነት የለሰለሰ መሬት ፣
ወጣትነት የአዝመራ ዘመን ፣
ሽምግልና ደግሞ የአጨዳ ዘመን መሆኑን አስተውል ።

በየ ሔድክበት ፊትና የማያጣህ መርህ አልባ አቋመ-ተልባ አትሁን ወንድ ወንድ ሽተት ....
........ሰለፍይነት ማለት ወንድነት እንጅ ወዳገረድነት አይደለም።

ወላሒ ልብ በል

በሽምግልናህ የምታጭደው የወጣትነትህን አዝመራ ነውና ዛሬ ለምትዘራው ተጠንቀቅ ።

http://t.me/nuredinal_arebi
http://t.me/nuredinal_arebi
2.9K viewsedited  14:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-23 16:46:36 ➙ወላሒ ከልቤ አመሰግናቸዋለሁ

«ክብር ይገባቸው»

"ባጭር ቀረን" ስንል፤
አይዟችሁ ብለው ተስፋ ላበደሩን፡
መንሀጅ አስተምረው፤
በቀደምቶች ፈለግ ቀርፀው ላሳመሩን፡
በሽርክ ስንጨልም፤
የተውሒድ ነፀብራቅ ለኩሰው ላበሩን፡
ከቢዲዐ አርቀው፤
በሱናውን መንገድ ላይ ለፍተው ላስከበሩን፡
---------------------------------------------
ፊታችንን ዐይተው፤
እንደተቸገርን ካይናችን ላወቁ፡
በአሏህ ስም ብለን፤
እስክንለምናቸው ቆመው ላልጠበቁ፡
ወቀሳውን ፈርተው፤
በየሸለቆው ዳር ስንቶች ሲደበቁ፡
ብዙ እየተባሉ፤
ሁሉን ነገር ችለው ለለውጥ ለበቁ፡
በተውሒድ ምክንያት፤
በጨቋኝ ስርዐት ግፍ ተፈርዶባቸው፡
እንባ እያፈሰሱ፤
ጀግንነት ላሳዩን ለሀይማኖታቸው፡
አቋም ላልቀየሩት፤
ለነዚህ አንበሶች ክብር ይገባቸው፡

የነብዩን ህይወት፤
የሶሀባን ታሪክ ለኛ ላስታወሱን፡
ምቀኞችን ንቀው፤
በሐቅ ላይ ፀንተው ፅናትን ላዋሱን፡
ታግለው ላታገሉን፤
ከጥመት አውጥተው ስኬት ላንተራሱን፡
የመንሀጅ መዐዛን፤
የሰለፍያን ወዝ ቀምሰው ላቀመሱን፡
ጥመት ላይ ስንተኛ፤
ኑ ብለው ወደኛ ሱናን ላስዳሰሱን፡
-----------------------------------------
በመንሀጅ ላይ ፀንተው፤
በአዳዲስ ፊትናወች ላልተቀያየሩ፡
ወደ ነፈሰበት፤
ጩኸት በበዛበት ላልሆኑ እንዳየሩ፡
ጠላት ሲዘምትበት፤
ዲናቸው ሲደፈር ቀድመው ለሚነሱ፡
በደዕዋ መንገድ ላይ፤
አይዟችሁ ለሚሉን ፊት ሆነው እነሱ፡
ሌት ከቀን ሳያርፉ፤
ለሚገሰግሱ ታሪክን ለመድገም፡
ውድቀትም ሲመጣ፤
ፈጥነው የሚነሱ ቶሎ ለማገገም፡

ለእምነት ዋጋ ከፍለው፤
በአሏህ እገዛ ዘወትር ወደ ፊት ለሚገሰግሱ፡
ለአንዷ ሐቅ ሲባል፤
ወድቀው ለማይጥሉ ነግሰው ለሚያነግሱ፡
ነውራችንን ዐይተው፤
በማራኪ ተግሳፅ ስህተት ለሚያፈርሱ፡
ነገር ከማራገብ፤
ችግርም ሲፈጠር ቶሎ ለሚደርሱ፡
ክብር ይገባቸው፤
አርቆ አስተዋዮች ሰው ናቸው እነርሱ፡

ለነዚህ ኮከቦች ይገባቸው ክብር፡
የአሏህን አደራ ያልቀየሩት በብር፡
በዱንያ ቆይታ ኢማንን ጨምረው፡
ሐቅ ላይ ለሞቱት በሐቅ ላይ ኖረው፡
በትንሹም ቢሆን ለቀራንባቸው፡
ለነዚህ ፅኑወች ክብር ይገባቸው፡

ውሸት በመሰከክ ሰው ለሚያጫርሱ፡
የጠራውን መንገድ ለሚያደፈርሱ፡
የኢስላምን ጠላት የሚገረስሱ፡
ህይወትን ለመክፈል ፈፅሞ እማይሳሱ፡
ለሒዝብያ መንጋ ለሽርክ ጠበቆች፡
ለኢስላም ነቀርሳ ለእውር ሙናፊቆች፡
የነዚህ መዳኒት ናቸው የኔ ሊቆች፡

በበሳል አካሔድ፤
ላባ ላረጉልን የመከራ ሸክሙን
ቀልደው ላሳቁን፤
በሚገርም ጥበብ ተጫውተው ላከሙን፡
በቸከ ዘመን ላይ...
ስጋ-ለበስ ትንግርት ሆነው ላስደመሙን፡
የአርሹ ባለቤት፤
እውቀት ከልቀት ጋር የሰጣቸው አቅሙን፡
በቁርዐን በሀዲስ፤
በሰለፎች ፈለግ የነብያት ወራሽ፡
አስደማሚ ዶክተር፤
በመረጃ ውበት ሁሌ ፈጥነው ደራሽ፡
ሰለፍያን እንዳውቅ፤
ከአሏህ በመቀጠል«ጉልህ»ነው ድርሻቸው፡
የኢስላም ሙህራን፤
ሊቀ-ጠበብቶቹ ክብር ይገባቸው፡
።።።።።።።።።።።፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
በኑረዲን አል-አረቢ 1444

https://t.me/nuredinal_arebi
https://t.me/nuredinal_arebi
2.7K viewsedited  13:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ