Get Mystery Box with random crypto!

ነገረ ፈጅ Negere Fej 📕

የቴሌግራም ቻናል አርማ negerefej — ነገረ ፈጅ Negere Fej 📕
የቴሌግራም ቻናል አርማ negerefej — ነገረ ፈጅ Negere Fej 📕
የሰርጥ አድራሻ: @negerefej
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.91K
የሰርጥ መግለጫ

ሕግን አለማወቅ ይቅርታን ሊያስገኝ አይችልም። የፍታብሔር ሕግ ቁጥር 2035(2)
Ignorance of the law is no excuse.
civil code article 2035(2)
ነገረ ፈጅ ከፈለጉ አለን @NegereFeji_Bot ወይም negerefej@gmail.com ይላኩልን።

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

3

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2022-07-01 09:18:08 Vacancy – Attorney
=============

The Commercial Bank of Ethiopia would like to invite qualified and interested job seekers to apply for the position of Attorney for Head Office and District Offices.

Interested and qualified applicants should apply through CBE career website (https://vacancy.cbe.com.et) from June 29 to July 8, 2022.

For requirements and other detail information, please use the following link:
https://combanketh.et/cbeapi/uploads/ATTORNEY_VACANCY_41ee2c2156.pdf
1.0K views06:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-30 20:25:49 የቀጠለ....
በተያያዘ ሁኔታ በተወሰነው ጊዜ ውስጥ መቀጮው ያልተከፈለ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ ሙሉውን ወይም ያልተከፈለውን ቀሪ መቀጮ ከሚያገኘው ገቢ ተቀናሽ በማድረግ ለመንግስት ገቢ ከማድረግ ጋራ ነፃነትን በሚቀንስ ወይም በማይቀንስ የግዴታ ሥራ እንዲለወጥ በማዘዝ በደንብ መተላለፍ ህጉ ጠቅላላ ድንጋጌዎች መሰረት የግዴታ ስራው የሚቆይበትን ጊዜ ይወስናል፡፡

በሌላ በኩል ከማረፊያ ቤት እስራት፣ ከግዴታ ስራ ወይም ከመቀጮ በተጨማሪ ፍርድ ቤት በቃል ወይም በፅሁፍ ጥፋተኛውን ሊያስጠነቅቀው፣ ሊወቅሰው፣ ሊገስፀው ወይም ተበዳዩን ይቅርታ እንዲጠይቅ ሊያደርገው ይችላል፡፡ እንዲሁም የጥንቃቄ እርምጃዎች ማለትም የመልካም ጠባይ ዋስትና፣ መውረስ እና ለመንግስት ገቢ ማድረግ፣ ድርጅቶችን መከልከል እና የስራ ፍቃድ ማገድ እና የግል ነፃነትን መከልከልና መቀነስ እንደ የጥንቃቄ እርምጃዎች የደንብ መተላለፍ በፈፀሙ ሰዎች ላይ ሊወሰኑ የሚችሉ እርምጃዎች ናቸው፡፡
ይሁንና ከመብት የመሻር ቅጣትን የተመለከቱ ማለትም ከህዝባዊ ወይም ከቤተዘመድ፣ የመንግሥት ሥራ ወይም የሙያ ሥራ ከመሥራት ወይም ከመሳሰሉት መብቶች መሻር እንዲሁም ወታደራዊ ማዕረግን ዝቅ ማድረግ ወይም ከመከላከያ ሰራዊት ባልደረባነት ማስወገድ በደንብ መተላለፍ ላይ ተፈፃሚ አይሆንም፡፡ እንዲሁም በአመክሮ መለቀቅን የሚመለከቱ የወንጀል ህጉ ድንጋጌዎች ለማረፊያ ቤት እስራት ተፈፃሚ የማይሆኑ ሲሆን የደንብ መተላለፍ ቅጣቶች በወንጀል ህጉ ላይ በተደነገጉት ጠቅላላ ሁኔታዎች መሰረት በይቅርታ ወይም በምህረት ቀሪ እንዲሆኑ ማድረግ ይቻላል፡፡

የይርጋ ዘመንን በተመለከተ ማናቸውም ዓይነት የደንብ መተላለፍ ድርጊት ቢሆን ክስ ሳይቀርብበት አንድ ዓመት ካለፈ የተፈረደውም ቅጣት ተፈፃሚ ሳይሆን ሁለት ዓመት ካለፈ በይርጋ ይታገዳል፡፡ በሌላ በኩል ፍርድ ቤቶች የተከሳሹን ያለፈ ታሪክ ጠንቅቀው ማወቅ ይችሉ ዘንድ በደንብ መተላለፍ ረገድ የሚሰጡት የመጨረሻ ቅጣቶች የደንብ መተላለፍ ህግን ጠቅላላ ድንጋጌዎችን በወንጀለኞች መዝገብ ላይ እንዲመዘገብ ፍርድ ቤቱ ይወስናል፡፡

በአጠቃላይ የደንብ መተላለፍ ህግ በወንጀል ህጉ ውስጥ የደንብ መተላለፎችን እና የሚያስከትሉትን ቅጣቶች ያካተተ ቢሆንም በተጨማሪ ሌሎች ባለስልጣናት የሚያወጧቸው የደንብ መተላለፎች ለምሳሌ የትራፊክ ደንብ፣ የከተማ ደንብ ማስከበር( ለምሳሌ ህገ ወጥ ንግድ እና ግንባታ) በተደነገጉት የጥፋት አይነቶች እና ቅጣቶች ኃላፊነትን ያስከትላሉ ወይም ያስቀጣሉ፡፡
በንቃተ ህግ ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክቶሬት
https://t.me/lawsocieties

https://t.me/AleHig
849 views17:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-30 20:25:49 ደንብ መተላለፍ በኢትዮጵያ የወንጀል ህግ
#መግቢያ
በኢትዮጵያ ህግ ቅጣት ሊያስከትሉ የሚችሉ ድርጊቶችን ከክብደታቸው እና ከሚያስከትሉት ሀላፊነት አንፃር በወንጀል ህግ የሚያስቀጡ እና በደንብ መተላለፍ ህግ የሚያስቀጡ ብለን ልንከፍል እንችላለን፡፡ በደንብ መተላለፍ የሚያስቀጡ ድርጊቶች በኢ.ፌ.ድ.ሪ የወንጀል ህግ ሰባተኛ መፅሀፍ እና ስምንተኛ የተደነገጉ ሲሆን ቅጣትን የሚመለከቱ ደንቦች እና የህጉ ተፈጻሚነት ወሰን በወንጀል ህጉ ተካቶ ይገኛል፡፡ በዚህ አጭር ፅሁፍ የደንብ መተላለፍ ምንነት እና ከወንጀል ሀላፊት በምን እንደሚለይ ፣ የደንብ መተላለፎች የሚያስከትሉት ቅጣት እና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ይዳሰሳሉ፡፡
የደንብ መተላለፍ ምንነት
አንድ ሰው ደንብ ተላልፏል የሚባለው ሥልጣን ያለው አካል ባወጣው ህግ የተመለከተውንና አንድ ነገር እንዳይፈፀም የሚያዘውን ወይም የሚከለክለውን ድንጋጌ የተላለፈ ወይም በወንጀል የማያስቀጣ ቀላል ጥፋት የፈፀመ ሲሆንና የዚህ ዓይነቱ ህግ መጣስ ወይም ቀላል ጥፋት በወንጀል ህጉ ከአንቀፅ 746 እስከ 775 በተመለከቱት ድንጋጌዎች የሚያስቀጣ ሲሆን ነው፡፡ በዚሁ መሰረት በወንጀል ህጉ የደንብ መተላለፍ ህግ ላይ በተለየ ሁኔታ ካልተደነገገ በቀር የነገሩን ዓይነት እንዲሁም የህጉን መንፈስና ግብ በመመልከት የወንጀል ህጉ ጠቅላላ ክፍል መሰረታዊ መርሆችና ደንቦች በደንብ መተላለፍ ላይ ተፈፃሚ ይሆናሉ፡፡
የደንብ መተላለፍ አይነቶች
የደንብ መተላለፍ ህጉ በውስጡ የተለያዩ አይነት የደንብ መተላለፎችን የያዘ ሲሆን እነዚህ መተላለፎች በስራቸው ዝርዝር የጥፋት አይነቶችን ከሚያስከትሉት ቅጣት ጋር አካተው ይገኛሉ፡፡ የደንብ መተላለፍ አይነቶቹም በመንግስትና ህዝብ ጥቅም ላይ የሚፈፀሙ የደንብ መተላለፍ ተግባሮች( ለምሳሌ ህጋዊ ገንዘብን አለመቀበል)፤ ወታደራዊ ግዴታዎችን መጣስ እና በመከላከያ ሠራዊት እንዲሁም በፖሊስ ላይ የሚፈፀሙ የደንብ መተላለፍ ጥፋቶች፤ በመንግስት የስራ ግዴታዎች እና በመንግስት መስሪያ ቤት/ባለስልጣን/ ላይ የሚፈፀሙ የደንብ መተላለፍ ጥፋቶች(ለምሳሌ ሀቀኝነትን ማጓደል)፤ በሕዝብ ደኅንነት፣ሰላምና ተረጋግቶ መኖር ላይ የሚፈፀሙ የደንብ መተላለፍ ጥፋቶች(ለምሳሌ ሐሰተኛ የአደጋ ምልክት መስጠት)፤ በሕዝብ ጤና እና በፅዳት ጥበቃ ላይ የሚፈፀሙ የደንብ መተላለፍ ጥፋቶች( ለምሳሌ መርዛማና አደንዛዥ ንጥረ ነገሮችና መድሀኒቶች ለመቆጣጠር የወጣ ደንብ) እና በሰዎችና በንብረቶች ላይ የሚፈፀሙ የደንብ መተላለፍ ጥፋቶች ናቸው፡፡

ደንብ መተላለፍ ተፈፃሚ የሚሆንባቸው ጥፋቶች
በህጋዊነት መርህ እንደተመለከተው በደንብ መተላለፍ ህግ ወይም በሌላ ህግ የተደነገጉ ጥፋቶች ብቻ የሚያስቀጡ ሲሆን የሚያስቀጡትም በህጉ የተቀመጡትን ቅጣቶች ብቻ ይሆናል፡፡ በተጨማሪም የደንብ መተላለፍ ድንጋጌዎች ተፈፃሚ የሚሆኑት ለተፈፀመው ድርጊት የበለጠ ቅጣት የሚደነግጉ አንቀፆች በሌሉ ጊዜ ብቻ ነው፡፡ ስለሆነም አንድ ድርጊት የሚያስቀጣው በወንጀል ህግ ወይም በደንብ መተላለፍ ህግ በአንደኛው እንጂ በሁለቱም ሊሆን አይችልም፡፡ እንዲሁም የወንጀል ህግ ወደ ኋላ ተመልሶ የማይሰራ መሆኑ መርህ በተመሳሳይ ለደንብ መተላለፍ ይሰራል፡፡ በመሆኑም የደንብ መተላለፍ ተግባሮች የሚያስቀጡት በተፈፀመበት ጊዜ ፀንተው ባሉት ድንገጌዎች መሰረት እንጂ ከድርጊቱ በኋላ የወጣን ህግ ወደ ኋላ ተመልሶ እንዲፈፀም በማድረግ አይሆንም፡፡
በሌላ በኩል የደንብ መተላለፍ ተግባርን ለመፈፀም የሚደረጉ የመዘጋጀትና የሙከራ ድርጊቶች የማያስቀጡ ሲሆን ለደንብ መተላለፍ የሚደረግ ማነሳሳት፣አባሪነት እና ወንጀል ከፈፀመ በኋላ ወንጀል አድራጊውን መርዳት አያስቀጣም፡፡ ይህ ማለት የሚቀጣው ደንብ ተላላፊው ብቻ ነው ማለት ነው፡፡ እንዲሁም የህግ ሰውነት የተሰጠውን ሰው በአነሳሽነት ወይም በአባሪነት የማይቀጣ ሲሆን የድርጅቱ ሀላፊ ወይም ሰራተኛ የሚቀጣው በወንጀል ህጉ መሰረት በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን ደንብን ወይም መመሪያን በዋና ደንብ ተላላፊነት በሚጥስበት ጊዜ ብቻ ነው፡፡

በተጨማሪም በወንጀል ህጉ አንቀጽ 743 እንደተደነገገው የማያስቀጡና ይቅርታ የሚሰጡ ሁኔታዎች የሚከተሉት ናቸው፡፡ እነዚህም በህግ የታዘዙ ወይም የተፈቀዱ ድርጊቶች፣ የሞያ ስራ ግዴታ፣ የተጎጂው ፍቃድ ፣ ፍፁም የሆነ መገደድ፣አስፈላጊ ሁኔታ እና ህጋዊ መከላከልን የሚመለከቱ የወንጀል ህግ ድንጋጌዎች ለደንብ መተላለፍም ተፈፃሚ ይሆናሉ፡፡ ይሁንና ደንብ የተላለፈ ማንም ሰው ህግ አለማወቅን ወይም የማድረግ መብት አለ ብሎ መሳሳትን እንደመከላከያ ምክንያት አድርጎ ሊያቀርብ አይችልም፡፡

ለደንብ መተላለፍ ተፈፃሚነት ያላቸው ቅጣቶችና የጥንቃቄ እርምጃዎች

ለደንብ መተላለፍ መደበኛ የሆኑ የወንጀል ቅጣቶች ተፈፃሚ የማይሆኑ ስለሆነ ምንጊዜም ቢሆን ለወንጀሎቹ በተወሰኑት ፅኑ እስራት ወይም በቀላል እስራት አይቀጡም፡፡ ይህም የሚያመለክተው ደንብ መተላለፍ ከወንጀል የሚለየው በሚያስከትለው የተለየ ቅጣት እንደሆነ ነው፡፡ ስለሆነም የደንብ መተላለፍ ድርጊቶች በተፈፀሙ ጊዜ የሚወሰነው ነፃነትን የሚያሳጣ ቅጣት የማረፊያ ቤት እስራት እንጂ የማረሚያ ቤት እስራት አይሆንም፡፡ መደበኛ የማረፊያ ቤት እስራት የሚፈፀመው ከፍርድ ቤቶች ወይም ከፖሊስ ጣቢያዎች ጋር በተያያዙ ልዩ የመቆያ ቦታዎች ይሆናል ማለት ነው፡፡ እንዲሁም በማረፊያ ቤት እስራት ፈንታ የግዴታ ስራን ፍርድ ቤት ሊወስን የሚችልባቸውን ሁኔታዎች የደንብ መተላለፍ ህጉ ደንግጎ ይገኛል፡፡ በተጨማሪም በማናቸውም ጊዜ ቢሆን በማረፊያ ቤት እስራት እንዲቀጣ የተፈረደበት ሰው ወደ ጠባይ ማሻሻያ ወይም ማረሚያ ቤት እንዲላክ ፣በወንጀል ምክንያት ከተቀጡት እስረኞች ጋርም እንዲቀላቀል ማድረግ አይቻልም፡፡

በወንጀል ህጉ አንቀጽ 747 እና 768 እንደተደነገገው የደንብ መተላለፍ ድርጊቶች በተፈፀሙ ጊዜ የሚወሰነው ቅጣት እና የህጉ ልዩ ድንጋጌዎች የሚያስቀምጡት ከፍተኛ ቅጣት የማረፊያ ቤት እስራቱ የሚቆይበት ጊዜ ከአንድ ቀን እስከ ሶስት ወር ይሆናል( በደጋጋሚነት እና በመደራረብ ጊዜ ከሁለት ዓመት የማረፊያ ቤት እስራት አይበልጥም) ፡፡ በተጨማሪም ደንብ ተላላፊዎች ወታደሮች ወይም ወጣት ጥፋተኞች ሲሆኑ የሚፈፀመው የተለየ ቅጣት እንደተጠበቀ ሆኖ በደንብ መተላለፍ ረገድ የሚፈፀሙ ቅጣቶች በደንብ መተላለፍ ህግ በተደነገገው መሰረት ይሆናል፡፡ እንዲሁም ለህብረተሰቡ ሲባል የጥበቃ ወይም የሕክምና እርምጃዎች መወሰድ ሲኖርባቸው በተለየ ኃላፊ ሊሆኑ የማይችሉ ሰዎችን በሚመለከት ፍርድ ቤት አግባብነት ላለው የአስተዳደር ባለስልጣን ያሳውቃል፡፡

ሌላው በደንብ መተላለፍ ህጉ ለደንብ መተላለፍ ጥፋት የተቀመጠው ቅጣት የገንዘብ መቀጮ ቅጣት ነው፡፡ ይኸውም ጥፋተኛው ደጋጋሚ ካልሆነ ወይም የህጉ ልዩ ድንጋጌ የበለጠ ካልወሰነ በቀር በደንብ ተላላፊ ላይ የሚጣል መቀጮ ከአንድ ብር እስከ ሶስት መቶ ብር ለመድረስ የሚችል ሲሆን ጥፋቱ በተደጋገመ ጊዜ የሚደረገው የቅጣት ማክበጃ እንደተጠበቀ ሆኖ ተላላፊው ጣፋቱን የፈፀመው በአፍቅሮ ንዋይ እንደሆነ መቀጮው እስከ አምስት መቶ ብር ሊደርስ ይችላል፡፡ እንዲሁም ለተፈረደበት ሰው ቢያስፈልግም ከፋፍሎ በየጊዜው ዕዳውን እንዲከፍል በመፍቀድ ፍርድ ቤቱ እስከ ሶስት ወር ለመድረስ በሚችል የመክፈያ ጊዜ ሊወስንለት የሚችል ሲሆን ሁኔታዎች በቂ ምክንያት ያስገኙ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ የመከፈያ ጊዜውን እስከ አንድ አመት ሊያራዝመው ይችላል፡፡... ይቀጥላል
649 views17:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-26 20:52:15
883 views17:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-26 09:31:56
3.2K views06:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-26 09:00:42 የስሚ ስሚ ማስረጃ (Hearsay Evidence)

የስሚ ስሚ ማስረጃ ስንል ስለ አንድ ኩነት እውነትነት ችሎት ያልቀረበ ሰው የገለፀውን ሌላው ሰው ችሎት በመቅረብ የሚሰጠው የምስክርነት ማስረጃ ነው። የስሚ ስሚ ማስረጃ በ'common law' እና በ'civil law' ምን ያህል ቅቡልነት እንዳለው ይህ ጽሁፍ ይመረምራል። የስሚ ስሚ ማስረጃ በኢትዮጵያ ተቀባይነት ሊኖረው ይገባል ወይስ አይገባም የሚለው ጥያቄ የዚህ ጽሁፍ ጭብጥ ነው።
: ተስፋዬ አባተ እንደ ፃፈው
735 views06:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-25 19:22:19 " ህግ ይከበር ፤ ፍትህ ይሰጠን "

ለማስፋፊያ ስራ ተብሎ #ህግን_ባልተከተለ መልኩ ቤታችን ፈረሰብን ያሉ በአዲስ አበባ ከተማ ፤ ገርጂ ኮርያ ሆስፒታል አካባቢ የሚገኙ ነዋሪዎች ቅሬታ አቅርበዋል።

ያሉበት ቦታ ለማስፋፊያ ስራ ይፈለጋል የተባሉ ዜጎች ለማስፋፊያ አንደሚፈለግ ያወቁት ሰኔ 29/2013 ዓ/ም አንደሆነ ከዛ በፊት ስለጉዳዩ ምንም እንደማያቁ / እንዳልተነገራቸው ፤ ጉዳዩን የሚያውቁት ከወረዳው ጀምሮ እስከ መሬት ማናጅመት ድረስ ያሉ አካላቶች እንደነበሩ አስረድተዋል።

አሁን ላይ ህግን ሳይከተል መኖሪያቸው የፈረሰባቸው ወገኖች ፍትህ እንዲሰጣቸው እየጠየቁ የሚገኙ ሲሆን በዚህ ክረምት ወቅት ዝናብ እየወረደባቸው ውጭ መሆናቸውን አስረድተዋል።

ያንብቡ
https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-06-25
740 views16:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-25 15:35:45 የኢትዮጵያ ብር እና የውጭ ሀገር ገንዘብን ይዞ መገኘት/ማዘዋወር ያለው የሕግ ተጠያቂነት

በ:-ገመቺስ ደምሴ

ሀገራችን የኢኮኖሚዋ መሠረት ሆኖ የሚያገለግልና ውስን የሀገር ሀብት በተገቢው መንገድ ጥቅም ላይ ለማዋል አስፈላጊ የሆኑ የቁጥጥር እርምጃዎችን ለመውሰድ ገንዘብ የሚያዝበትና የሚተዳደርበትን አግባብ በተመለከተ የተለያዩ ሕጎች ተደንግገው እናገኛለን፡፡ ይህንን ዓላማ ለማሳካት አስተዳደራዊና የወንጀል ተጠያቂነትን እንደማስፈፀሚያ መሳሪያ አድርጋ በተለያዩ የሕግ ማዕቀፎች ውስጥ አካታ እየተገበረች በመሆኑ በቀጥታ ከወንጀል ጋር ያለውን ቁርኝት ጽሑፉ ለመዳሰስ ይሞክራል፡፡

ጽሑፉ በቅድሚያ አጠቃላይ መንደርደሪያ ሀሳቦችን ለማንሳት የሚሞክር ሲሆን የገንዘብ ትርጉምን፣ የውጭ ምንዛሬ ምንነትንና ሊታዩ የሚገባቸውን የሕግ ማዕቀፎችን መነሻ አድርጎ ያትታል፡፡ በመቀጠልም የኢትዮጵያ እና የውጭ ሀገር ገንዘብን በጥሬ ገንዘብ ለመያዝና ለማዘዋወር የሚፈቀድባቸው አግባቦች ከተለያዩ የሕግ ማዕቀፎች አንፃር ለማንሳት ይሞክሯል፡፡

የተለየ ትኩረትም ከውጭ ምንዛሪ ጋር በተያያዘ ሊታዩ የሚገቡ ነጥቦችን አንስቶ የሚሞግትና የሚያስገነዝብ አፃፃፍን ተከትሏል፡፡ ጽሑፉ በሕግ ከተቀመጠው አግባብ ውጭ ገንዘብ መያዝና ማስተላለፍ የሚያስከትለውን የወንጀል ተጠያቂነትን አጉልቶ በማንሳት የሚስተዋሉ የአረዳድና የአተረጓጎም ክፍተቶችን ሽፋን ሰጥቶ ካነሳ በኋላ ሊያዝ የሚገባውን ተገቢ አረዳድና አተረጓጎማቸውን አንስቶ ይሞግታል፡፡ በመጨረሻም ጽሑፉ ማጠቃለያ ሃሳቦችን ጨምቆ ለማስቀመጥ ሞክሯል፡፡

Enjoy reading!

https://www.abyssinialaw.com/blog-posts/item/2032-money-holding-limit-in-ethiopian-law
701 views12:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-24 12:18:03
10 ከፍተኛ የዋጋ ግሽበት ያለባቸው አገራት

የዋጋ ግሽበት ከናጣቸው አገራት መካል ቬንዝዌላ ቀዳሚ ተጠቃሽ ናት። ባላት ከፍተኛ የነዳጅ ምርት ላይ የኢኮኖሚዋን ሐሳብ የጣለችው ቬንዙዌላ፣ በቀላሉ በነዳጅ ዋጋ ላይ በሚኖሩ ለውጦች ተጽእኖ ያርፍባታል።

ይህም ነው በ2022 ለታየው የዋጋ ግሽበት መንስኤ የሆነው። በቬንዝዌላ የታየው እንዲህ ያለው ግሽበት ታድያ በኢንግሊዘኛው ‹ሀይፐር ኢንፍሌሽን› ተብሎ እንደሚጠራ ወርልድ ፖፑሌሽን በገጹ ባነበበው የአገራቱ ዝርዝር ስር ያስረዳል።
#EthiopianBusinessDaily
667 viewsedited  09:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-24 06:39:58
645 views03:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ