2022-07-01 09:29:26
ለዶሮ አርቢዎች እና አቀናባሪዎች በሙሉ
በቅርቡ በአንዳንድ አከባቢዎች በተከሰተው የዶሮ ወረርሽኝ በሽታ ምክንያት የዶሮ እና የዶሮ ውጤቶች እንቅስቃሴ ተገድቦ ( Restrict ) ተደርጎ የቆየ መሆኑ ይታወቃል። ይህ እገዳ የበሽታውን ስርጭት በመግታት ረገድ ከፍተኛ ሚና ቢኖረውም፣ የእገዳ ጊዜው መራዘሙ በአርቢዎች እና አቀናባሪዎች ላይ ከፍተኛ ጫና ፈጥሮ የቆየ መሆኑ ይታወቃል። በሽታውን በመግታት ሂደት እና በእገዳው ምክኒያት አርቢዎች እና አቀናባሪዎች ላይ እየደረሰ የነበረውን ኪሳራ የማህበራችን አመራር ቦርድ ከግበርና ሚኒስቴር አመራሮች እና ይህ ጉዳይ ከሚመለከታቸው ባለሙያዎች ጋር በየሳምንቱ በአካል በመገኘት እየተወያየን የቆየን ሲሆን በዛሬው እለት በግብርና ሚኒስቴር በኩል የተዘጋጀውን በሽታን ለመቆጣጠር እና የተጣለውን እገዳ በጥንቃቄ ማኔጅ ለማድረግ የወጣውን የትግበራ መመርያ( operational guideline) ላይ የኢትዮጵያ ዶሮ አርቢዎች እና አቀነባሪዎች ማህበር ቦርድ አባላት እና የግብርና ሚኒስቴር አመራሮች እና ባለሙያዎች ውይይት አደርገናል። በዚህ በተዘጋጀው የትግበራ መመሪያ መሰረት ፣
፩ኛ• ወረርሽኙ ያልተከሰተባቸው አካባቢዎች ( free zone) ያሉ ፋርሞች የምያመርቱትን እንቁላል እና ሥጋ ግብይት ማድረግ የሚቻል መሆኑ
፪ኛ• ወረርሽኙ በተከሰተ አከባቢ ያሉት ፋርሞች የምያመርቱትን እንቁላል እና ሥጋ በግብርና ሚናስቴር እውቅና በተሰጠው አካል እና ባለሙያ አማካኝነት የላብራቶሪ ምርመራ ( lab.Test) አድርጎ ከበሽታ ነፃ መሆኑ ከተረጋገጠ የእንቁላል እና የሥጋ ምርቶች ግብይት መፈፀም የሚቻል መሆኑ
፫ኛ• የላብራቶር ምርመራ በተመለከተ የተቋቋመ taskforce ስላለ በፍጥነት አገልግሎት እንደሚሰጡ ተገልፀዋል። አርቢዎችም ይህንን አውቃችሁ ትብብር እንድታደርጉ ማህበሩ ያሳስባል።
፬ኛ• ጫጩት፣ ቄቦች እና የለማ እንቁላል በተመለከተ ወረርሽኙ የተከሰተባቸው አከባቢዎች (Controlled Zone) ላይ ግብርና ሚ/ር መግለጫ እስከሚሰጥ ድረስ ግብይት እና ስርጭት ማደርግ የተከለከለ መሆኑ።
፭ኛ/ ይህ በሽታ ዳግም እንዳይከሰት በእንቁላል እና ሥጋ ሽያጭ ወቅት መከተል የሚገባን ቅድመ ሁኔታዎች
እንቁላልን በተመለከተ
1- ፋርሞችን ማስመርመር እና ነፃ መሆናቸውን ማረጋገጥ
2-የካርቶን ትሪዎችን አንድ ጊዜ ቢቻ መጠቀም(use and then Burn/bury)
3-ፕላስቲክ ትሪዎችን Disinfect በማድረግ መጠቀም
የዶሮ ሥጋን ሽያጭን በተመለከተ
1-ምርመራ ተካሄዶ ነፃ ከሆኑ ፋርሞች የተገኘ የስጋ ውጤት
2-ከመታረዳቸው በፊት በየሳምንቱ ከበሽታ ነፃ ለመሆናቸው Sample Test የተደረጉ እና ከበሽታ ነፃ የሆኑ
3-በንፅህና ታርደው የተዘጋጁ ዶሮዎች
ባጠቃላይ በግብርና ሚኒስቴር በኩል በደረሰን እና በተወያየንበት መመሪያ መሰረት ከላይ የተጠቀሱትን ቅድመ ሁኔታዎችን በማሟላት በግብይት መመሪያው የተፈቀዱ የእንቁላል እና የሥጋ ምርቶችን ከነገ ዓርብ ቀን 24/10/2014 ጀምሮ ለገበያ ማቅረብ የሚቻል መሆኑን እየገለፅን፣ በሽታው ባለባቸው ቦታዎች (Controlled Zone) ያሉት የጫጩት፣ የቄብ ዶሮ እና የለማ ዶሮን በተመለከተ፣ የግብርና ሚኒስቴር ተጨማሪ መግለጫ እስኪያወጣ ተገድቦ የሚቆይ መሆኑን እንገልፃለን።
ለመመሪያው ተግባራዊነት እና በሽታው ዳግም እንዳይስፋፋ ሁላችንም የየድርሻችንን እንወጣ።
ከሠላምታ ጋር!
የEPPPA Board
1.1K views06:29