2022-04-20 23:01:08
"የምትሰብከውን ወንጌል ታምናለህ?" አለኝ
# እውነተኛ_ገጠመኝ_የማንቂያ_ደወል
የዛሬ 19 ዓመት አከባቢ ነው። አቤት ጊዜው እንዴት ይሮጣል?!
ጎዳና ላይ ቆመን የአዋጅ ነጋሪ አገልጋዮች በጀማአ ወንጌል
እያወጅን ነበር በጎዳና ላይ በመቶዎች የሚቆጠሩ ቆመው
አገልግሎታችንን ይሰሙ ነበር።
ሙሉ ፕሮግራሙን ( ሰብከን፣ ዘምረን እና ለሁሉም ጸልየን ) ከጨረስን በኋላ አንድ ሰው ወደ እኔ መጥቶ ጥያቄ አለኝ አለ እኔም እሺ ወንድሜ ይቻላል አልኩት!
ፈጠን ብሎ #የምትሰብከውን_ወንጌል ታምናለህ? አለኝ በልቤ ምን ይጠየቃል ይህማ ግልፅ ነገር አይደለ እንዴ እያልኩ፤ ለመልስ ጊዜ ሳይሰጠኝ ከአንተ ጋር ያሉትስ በወንጌል ያምናሉ? ሁሉም
ጴንጤዎች ያምናሉ ትላለህ? እያለ ተመሳሳይ ጥያቄዉን አከታተለ
የሚገርመው አፉ ውስጥ ጫት እንደሞላ ነበር በጥያቄ
የሚያጣድፈኝ።
እኔም በወንጌል በደንብ አምናለሁ ቤተክርስቲያንም በሚገባ
ታምናለች አልኩት።
አንዳንድ ሰዎች ወሬያችንን ለመስማት ሰብሰብ ማለት ጀመሩ
እርሱም እዉነት ቅድም አንተ እንደምትሰብከው ሲኦል እንደነገርከን መጥፎ ስፍራ ከሆነና መንግስተ ሰማይ የከበረ ስፍራ ከሆነ፤ ኃጢአተኞችም ሁሉ በኢየሱሱ ክርስቶስ ስራ አምነው መዳን የሚችሉ ከሆነና የማያምኑ ሁሉ ደግሞ ሲኦል የሚገቡ ከሆነ ዛሬ ምድርን የሞሉ በኢየሱስ የማያምኑ ሰዎች ወደ ሲኦል ሲሄዱ እያያችሁ እንዴት አስችሎአችሁ ዝም ብላችሁ ቤተክርስቲያን ብቻ ተሰብስባችሁ ትለያያላችሁ?
እኔ ግን የምታምኑ አይመስለኝ?! ታዲያ እንዴት ጴንጤ ሁሉ
በየመንገዱ ወጥቶ ከሲኦል አምልጡ እያለ አይጮኽም?
እስቲ አስብ አንድ ህፃን እሳት ውሰጥ እየገባ እያየ ዝም ብሎ
የሚያይ ሰው ይኖራል? ሁሉም ሰው ህፃኑን ከእሳት ለማዳን
አይሮጥም? አለ።
እኔም እውነት ነው ለማዳን ይሮጣል አልኩት።
እርሱም እኔ ግን ትናገራላችሁ እንጂ ሲኦል እንዳለ የምታምኑ
አይመስለኝም አለኝ።
እውነቱን ለመናገር ደነገጥኩ የዚህ ሰው ጥያቄ ሳላስበው የእኔም
ጥያቄ ሆነ እውነት ትክክል ነን? የዘላለም ሞትና ሕይወት እንዳለ
ከተረዳን ለምን ሁሉም ሰው ወጥቶ አይጮህም? አልኩ።
ውስጤ በአማኞች (በእኛ ሁኔታ) በጥያቄ እንደተሞላሁ ብቻ ግን
ይህ ሰው ወደ ጌታ እንዲመጣ በማሰብ ለራሴም ጥያቄ
እንደፈጠረብኝ ስለዚህ እኮ ነው ይኸው እንደምታየኝ ጎሮሮዬ
እስኪዘጋ ስጮህ የነበረው ቅድም አላየኽኝም? አልኩት።
ብዙም አልተዋጠለትም እርሱ አማኝ ቢሆን ኖሮ ወንጌል ለመስበክ ያለ ዕረፍት እንደ እብድ እንደምጮህ እየታየው መሰለኝ እናንተ እንደምታምኑ እኔ ባምን... ብሎ ዝም አለ።
ይህ ሰው እንዴት አይነት እንቅልፍ ውስጥ (አግባብ ባልሆነ ዝምታ
ውስጥ) እንዳለን አሳይቶኝ ተለየኝ።
ወገኖቼ እኔም የሰውዬውን ጥያቄ እደግማለሁ በወንጌል
እናምናለን? የማያምኑ ሰዎች እንደማይድኑ የምናምን ከሆነ ለሰው ዘር ሁሉ ወጥተን በጌታ በኢየሱስ እመኑ ከዘላለም ሞት ዳኑ ብለን ለምን አንጮህም?
ወንጌል ለሁሉም ሁሉም ለወንጌል እንወጣለን እንወርሳለን
164 views20:01