2023-04-30 21:26:01
ዘመድኩን ና በኀይማኖት ተቋማት ስር የተሰገሰጉ ጽንፈኛ ሽብርተኞች!
የፀጥታ ግብረ ኅይሉ በተለይም ዘመድኩም በቀለን
ጨምሮ በኃይማኖት ተቋማት ስር የተሰገሰጉ ሽብርተኛና ጽንፈኛ ግብረ አበሮቹን በቁጥጥር ስር እንዲያዉል ስለመጠየቅ።
▬▬▬▬▬▬▬▬▬
Mujib Amino
የሽብር ኃይሎቹ ከሚኖሩባቸው ሀገራት በአለም አቀፍ የፖሊስ ድርጅት (ኢንተርፖል) እንዲሁም እነሱ ከሚኖሩባቸው ሀገራት መንግሥት የፀጥታ እና የደኅንነት ተቋማት ጋር በተመሠረቱ የትብብር ማዕቀፎች አማካኝነት ወደ ሀገር ቤት ተላልፈው እንዲሰጡ በህግም እንዲጠየቁ እየተሰራ ይገኛል።
እነዚህ ጽንፈኛ ኃይሎች የሀሰት ወሬዎችን በመፍጠር እና ከፍተኛ የሽብር ፕሮፓጋንዳ በመንዛት ህዝቡን በብሄር እና በሀይማኖት በመከፋፈልና በማጋጨት የክልል እና የፌደራል መንግሥትን በኃይል ለመጣል እንዲሁም ሀገሪቱ ከጀመረችው የለውጥና የልማት መንገድ ወጥታ ወደ ለየለት ሁከትና ትርምስ እንድትገባ በህቡዕ ተደራጅተው እየሠሩ መሆናቸውን የገለፀው የጋራ ግብረ ኃይሉ፤ በሀገር ውስጥና በውጭ ሆነው በሀሰት ሀገር ለማፍረስ የሚሰሩ እነዚህን ጨምሮ ሌሎችም በህቡዕ አደረጃጀቱ ውስጥ ያሉ ግለሰቦችም ጭምር በሽብርተኝነት ምርመራ እየተጣራባቸው መሆኑን መግለጫው አመልክቷል።
የፀጥታ ግብረ ኅይሉ በተለይም ዘመድኩም በቀለን ጨምሮ በአዲስ አበባና በክልል ከተሞች ሐይማኖትን ሽፋን በማድረግ ሁከት እንዲንሰራፋ፣ ብጥብጥ እንዲነሳ፣ ሽብርና ጥፋትን በማቀጣጠል ዜጎች በጥርጣሪ እንዲተያዩና ሃገሪቷ የደም መሬት እንድትሆን ጭካኔየዊ፣ ኢ ሰብዓዊ ፣ ኢ ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ ሲንቀሳቀሱ እንደነበር የሚታወቅ ነዉ።
በመሆኑም ህግና ስርዓትን በተከተለ መንገድ የኃይማኖት ተቋማትን ጨምሮ በስራቸዉ የሚገኙ መጋዘኖችና ሱቆች ላይ ትኩረት በማድረግ ፍተሻ እንዲያደርግ እንገልጻለን።
በተለይም በአዲስ አበባ ና አከባቢዋ ከዘመድኩን በቀለ ጋር ግንኙነት ያላቸዉ አካላት በግልጽ የሚታወቁ በመሆኑ መረጃና ማስረጃዎች ሳይሸሹ ኣፋጣኝ የምርመራ ሂደት እንዲዘረጋ እናሳስባለን።
በዚህ የምርመራ ሒደት ዉስጥ ቀጥተኛ ተሳትፎ እያደረገ ለሚገኘዉ የጸጥታና የደህንነት ግብረ ኀይል
በማህበረሰባችን፣ በሕዝባችን ስም የላቀ ምስጋናችንን እናቀርባለን።
5.6K viewsAllah Is Great, 18:26