2022-07-09 09:51:06
1443ኛው የኢድ አል አድሃ አረፋ በዓል የሶላት ስነ-ስርዓት በሰላም መጠናቀቁን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡
***
1443ኛው የኢድ አል አድሃ አረፋ በዓል በላም እንዲከበር የፀጥታና የደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል ወቅታዊውን የፀጥታ ሁኔታ ያገናዘበ ዕቅድ በማውጣት ዝግጅት አድርጎ ወደ ስራ መግባቱ የሚታወቅ ነው፡፡ ህብረተሰቡንና የዕምነቱ ተከታይ በጎ ፈቃደኞችን በማስተባበር በተሰራው ሥራ በአዲስ አበባ ስታዲዮም ዙሪያ የተከናወነው የሶላት ስነ- ስርዓት በሰላም መጠናቀቁን የአ/አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡
ሥነ-ሥርዓቱ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ የበዓሉ ታዳሚዎች ላሳዩት ቀና ተባባሪነት እና ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ተግባራቸውን በብቃት ለተወጡ የፀጥታ አካላት የአዲስ አበባ ፖሊስ በፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይሉ ስም ምስጋናውን አቅርቧል፡፡
ቀሪው የበዓል አከባበር ሰላማዊ ሆኖ እንዲቀጥል በየአካባቢው በቂ የፀጥታ ኃይል ተመድቦ ተግባሩን እየተወጣ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቆ ህብረተሰቡ ከፀጥታ ጉዳይ ጋር ተያያዥ መረጃ ወይም ጥቆማ ለመስጠት በ991 ወይም 816 ነፃ የስልክ መስመሮች እና 01- 11 -11- 01 -11፣ 01- 11- 26- 43- 59፣ 01- 11- 01- 02- 97፣ መጠቀም እንደሚቻል ተገልጿል፡፡
9.7K viewsAllah Is Great, 06:51