2023-07-03 12:46:33
በክቡር ሸይኽ ሀጅ ኢብራሂም ቱፋ የሚመራዉ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠ/ም/ቤ በ1444ኛው የሐጅ መስተንግዶ ባሳየዉ የተሻለ አፈጻጸም በሳዉዲ ኮሚዩኒቲ የዕውቅና ሽልማት ተበረከተለት።
••••••••••••••••••••••••••••••
በክቡር ሸይኽ ሀጅ ኢብራሂም ቱፋ የሚመራዉ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠ/ም/ቤ ያስመዘገውን ውጤታማ ስራ በሳዉዲ አረቢያ በመካና በጂዳ በሚገኙ የኢትዮጵያን ኮሚዩኒቲ ፅ/ቤቶች፡ በቢላል፡ በሰዑዲ አረቢያ የኢትዮጵያን ሙስሊሞች ማህበር እና በመካ ተወላጅ ኢትዮጵያዊያን ወጣቶች(መዋሊድ መካ) አዘጋጅነት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በ1444ኛ የሐጅ ጉዞ መስተንግዶ ዉጤታማ ስራ የምስጋናና የትውውቅ መርሀ ግብር በመካ ተካሂዷል።
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሸይኽ ሀጅ ኢብራሂም ቱፋ የዘንድሮ የሐጅ ስራችን ውጣታማ የሆነው በተወኩል ስራውን በመጀመራችን ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ ባሳለፍነው የስራ ቆይታ ስህተቶች ሲገጥሙን ፈጥነን ማረም በመቻላችን የዛሬውን ውጤት ምክር ቤቱ እንዲያይ አድርጓታል። ለዚህም ፈጣሪያችንን አሏህ እናመሰግናለን። ብለዋል
የዘንድሮውን የሐጅ መስተንግዶ በተቋቋመው የሐጅ ግብረ ኃይል እየተመራ ሲሆን ሰራተኞችንን በማስተባበር ውጤታማ ስራዎችን ማስመዝገቡን ገልፀዋል።
ጠቅላይ ምክር ቤቱ በአዋጅ ከተቋቋመ በኋላ ለሲቪል ማህበራትና ድርጅቶች የሕጋዊ ዕውቅና ሰርተፊኬት እየሰጠ መሆኑን አስታውሰው ቢላል በሳዉዲ የኢትዮጵያዊያን ማህበር ጥያቄም በአሠራሩ መሠረት ምላሽ እንደሚያገኝ ገልፀዋል።ወደፊትም ጥናት ላይ በተመሰረተ የመካ ተወላጅ ወጣቶችን በመካ የሐጅ ስራ መስተንግዶ ላይ ተሳታፊ እንዲሆኑ እንደሚሰራ ገልፀዋል።
በዘንድሮ የውጪ ምንዛሪ ችግርን ለመቅረፍ የመንግስትና የግል ባንኮችን ትብብር ያስታወሱት ፕሬዝዳንቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዘንድው ሐጅ መስተንግዶ ያደረገው አስተዋፅዖ የሚበረታታ ነዉ ሲሉ ምስጋና አቅርበዋል::
1.3K viewsMujib Amino Z Islam, 09:46