Get Mystery Box with random crypto!

ምን እንጠይቅሎ?

የቴሌግራም ቻናል አርማ mnenteyiklo — ምን እንጠይቅሎ?
የቴሌግራም ቻናል አርማ mnenteyiklo — ምን እንጠይቅሎ?
የሰርጥ አድራሻ: @mnenteyiklo
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 6.20K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ ቻናል የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያንን የተመለከቱ ሃይማኖታዊ ጥያቄዎችን ለመመለስና ለመማማር ታስቦ የተከፈተ መንፈሳዊ ቻናል ነው።
ለሚኖራችሁ ማንኛውም ሀሳብ ጥያቄና አስተያየት

👉 @MenbereM
👉 @teklemaryam19
ልታደርሱን ትችላላችሁ

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2021-02-28 21:02:24 የቀጠለ...

አባ እንጦንስም "እግዚአብሔር መልካም ነው፤ እንደ ሰው ስሜት የሌለውና የማይለወጥም ነው። እግዚአብሔር የማይለወጥ መሆኑን የተቀበለው ሰው እንኳ እንዴት በመልካም ይደሰታል ከክፉው ይርቃል በኃጢአተኞች ይቆጣል ንስሐ ሲገቡም ምህረት ያደርግላቸዋል? በማለት ግራ ይጋባል። ለዚህ መልሱ እግዚአብሔር አይደሰትም አይቆጣም ነው። ደስታም ሆነ ቁጣ ስሜት ናቸውና። አምላክ የሰው ሥራ የሚጠቅመው እና በሰው ሥራም የሚጎዳ ነው ብሎ ማሰብ ሞኝነት ነው። እግዚአብሔር መልካም ነው የሚሰራውም መልካሙን ብቻ ነው።... እኛ ግን መልካም ስንሆን እግዚአብሔርን በመምሰል ወደርሱ ሕብረት እንገባለን ክፉ ስንሆን ደግሞ እርሱን ባለመምሰል ራሳችንን ከእግዚአብሔር ቆርጠን እንለያለን። በምግባር ብንኖር የእግዚአብሔር እንሆናለን። ክፉ ስንሆን ደግሞ ከርሱ ተለይተን እንወድቃለን። ይህ በመሆኑ እርሱ ተቆጥቷል ማለት አይደለም ነገር ግን ኃጢአታችን እግዚአብሔር በኛ ውስጥ እንዳያበራ በማድረግ ከሰይጣናት ጋር እንድንዛመድ ያደርገናል እንጂ። በኋላም በጸሎትና በመልካም ሥራ ከኃጢአታችን መፈታትን ስናገኝ እግዚአብሔርን ከቁጣው አቀዘቀዝነው ለወጥነው ማለት አይደለም ነገር ግን በዚህ ተግባራችንና ወደ እግዚአብሔር በመመለሳችን በኛ ያለውን ክፋት ፈውሰን ዳግመኛ የእግዚአብሔርን መልካምነት ለመሳተፍ ቻልን ማለት ነው። እግዚአብሔር ከክፉዎች ይለያል ሲልም ልክ የዓይን ብርሃን ላጡት (ዓይነ ስውራን) ጸሐይ ራሷን ትሰውርባቸዋለች እንደማለት ነው።" ይላል።
@Orthodoxbiblestudy

ቅዱስ ዳዊት በመዝሙሩ "አቤቱ በቁጣህ አትቅሰፈኝ በመዓትህም አትገሥጸኝ።" መዝ. 6፥1 በማለት የእግዚአብሔር መዓቱ ቁጣው ለትምህርት ለተግሳጽ እንደሆነ ያስተምረናል።
@Orthodoxbiblestudy

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅም ስለዚህ ነገር ሲያስተምር " ... የእግዚአብሔር ቁጣ እንደ ሰው ስሜት ቢሆን ኖሮ በብዙ የክፋት ስራዎች ያቀጣጠለውን እሳት (ቁጣ) ማጥፋት ባለመቻሉ ሰው ተስፋ ይቆርጥ ነበር። የአምላክ ባህሪይ ግን ከስሜት ነጻ ስለሆነ ቢቀጣንም ቢበቀልም ይህን ሁሉ የሚያደርገው በቁጣ ያይደለ እንክብካቤ ባለው ፍቅርና በርህራሄ ነው... እግዚአብሔር በፊቱ ኃጢአትን ያደረጉትን እንኳ ስለ ራሱ ሲል በቅጣት አይጎበኝም። መለኮታዊ ባሕርይን የሚጎዳ አንዳች ድርጊት የለምና ነገር ግን ይህን ስለ ጥቅማችን ያደርጋል እርሱን በመተውና ቸል በማለት የበለጠ ከመጥመም ይከለክለን ዘንድ ነው። ራሱን ከብርሃን ውጪ ያደረገ ሰው በብርሃኑ ላይ የሚያደርሰው አደጋ የለም ይልቅ ትልቁን ጉዳት በራሱ ላይ በጨለማ ውስጥ መዘጋትን (መቀመጥን) ያመጣል። እንዲሁ ኃያሉን አምላክ ቸል የሚለውም ኃያሉ አምላክን አይጎዳውም። ይልቅ ትልቁን ጉዳት በራሱ ላይ የሚያመጣ ይሆናል። ስለዚህም ምክንያት እግዚአብሔር ቅጣትን እንደሚያመጣ በመንገር ያስፈራናል ብዙ ጊዜም ቅጣትን ያመጣል ይህም [ኃጢዓት በማድረግ ስለበደልነው] ለራሱ በመበቀል ሳይሆን እኛን ወደ ርሱ በመሳብ ነው። አንድ ሐኪም አዕምሮዋቸው በተነካ ሰዎች (በአዕምሮ ሕሙማን) ስድብ የሚበሳጭና የሚያዝን አይደለም። ይልቁኑ ይህን ተገቢ ያልሆነ ድርጊትን የሚፈጽሙትን እንዲተዉ ለማድረግ ሁሉንም አማራጮች ይሞክራል። ይህን የሚያደርገው ስለራሱ ጥቅም ሳይሆን ስለ ታማሚዎቹ ሲል ነው። ጥቂትም ቢሆን ራስን ወደ መግዛትና ወደ ትክክለኛ አዕምሮዋቸው ሲመለሱ ይደሰታል። ስለ ቀደመው ባሕርያቸው [ስለ ስድባቸው] ስለመበቀል በሚል ሳይሆን ወደ ቀደመው ጤናቸው ይመለሱ ዘንድም ስለነርሱ ጥቅም በቅንነት መድኃኒቱን መስጠቱን ይቀጥላል። እግዚአብሔርም በተመሳሳይ መልኩ [ኃጢአትን ክፋትን በማድረግ ] ጥልቅ ዕብደት ውስጥ ስንገባ ስለ ክፋት ስራችን በመበቀል ያይደለ ከዚህ በሽታችን ነጻ ሊያደርገን ነው። " ይላል። ስለዚህም የእግዚአብሔርን ቁጣ እንደ ጨካኝና ስለ ራሱ እንደሚበቀል አድርጎ ማሰብ ልክ አንድ በሽተኛ የሐኪሙን ትዕዛዝና ሕክምና እንደ ማስፈራርያ አድርጎ የመውሰድ ያህል ነው።
@Orthodoxbiblestudy
6.5K views18:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-28 21:00:34 እግዚአብሔር እንደ ሰው ይቆጣልን? የእግዚአብሔር ቁጣ ሲልስ ምን ማለት ነው?
@Orthodoxbiblestudy

አንዱ ሊቅ "እግዚአብሔር ጅማሬ የሌለው ዘላለማዊ አንዳችገ የማይጎድልበት እንደ ቁጣ መዘንጋት አለማወቅ ከመሰሉት ስሜቶችና ጉድለቶች ሁሉ በላይ ነው።" በማለት እንደ ሰው ያለ ስሜት የሌለው እንደሆነ ይነግረናል። መጽሐፍ ቅዱስ ለሰው የተጻፈ የተሰጠ የእግዚአብሔር ቃል ነው። የተጻፈውም በሰው ቋንቋ ነው። እኛ እንረዳ ዘንድ በሰው ቃል ማይገለጠውን እግዚአብሔር ለመግለጽ በምናውቀው ቃል አገላለጽ ተጠቅሞ መልዕክትን የሚያስተላልፍ ነው። የእግዚአብሔር ቁጣ እንደ ሰው ንዴት ቁጣ ያለ የስሜት መግለጫ አይደለም። መጽሐፍ ቅዱስ ለሰው ነውና የተጻፈው በሰውኛ የተገለጹ ቃላትን ስንመለከት እግዚአብሔርን እንደ ሰው አድርገን ልንመለከት አይገባም።
ስለ እግዚአብሔር ያለው አብዛኛው ነገር በድንግዝግዝ የምናቀው የምንረዳው ስለሆነ መግለጽ በሚችሉ ቃላት ማስቀመጥ አንችልም። ከኛ በላይ የሆነውን ለመግለጽም በውሱን ችሎታችን ከመጠቀም ውጪ አቅም የለንም። እኛ ከህጻናትና ከልጆች ጋር ስናወራ አንደበተ ርቱእነታችንን እያሳየን ሳይሆን ራሳችንን ለነርሱ ደካማነት በሚመጥን መልኩ ነው ምናወራው እግዚአብሔርም ከጊዜና ከቦታ ከስሜቶች ሁሉ በላይ የሆነው አምላክ ሲናገረን ለኛ አዕምሮ በሚረዳው በሚመጥን መልኩ እንደሆነ መረዳት ያስፈልጋል።
@Orthodoxbiblestudy

ቅዱስ ዮሐንስ ካዝያን ስለ እግዚአብሔር በሰውኛ ስለተገለጹት ሲናገር "...ስለ አምላክ ቁጣ ስናነብ ለሰው ስሜት በሚሆን በማይገባ መንገድ ሳይሆን ከስሜት ነጻ ለሆነው ለእግዚአብሔር በሚገባ መልኩ አድርገን ልንረዳ ይገባል።" ይላል።

ቅዱስ አምብሮስ የተባለውም ሊቅ ".... የእግዚአብሔር ሐሳብ እንደሰው አይደለም። በርሱ ዘንድ የሐሳብ ለውጥ የለም። [እንደ ሰው] የሚቆጣና ቀጥሎም የሚረጋጋ አይደለም። እኚህ ሁሉ የተጻፉት የአምላክን ቁጣ እንድናገኝ ያደረገውን የኃጢአታችንን ምሬት እናውቅ ዘንድ ነው። ኃጢአት በዚህ ደረጃ አድጎ በባሕሪይው ለቁጣ ጥላቻና ሌላ የሰው ስሜት የማይነሳሳው እግዚአብሔር ለቁጣ እንደተነሳሳ ተደርጎ እስኪጻፍ ድረስ መበደላችንን የሚያሳይ ነው።" በማለት ይናገራል። በተመሳሳይ እግዚአብሔር አዘነ ተጸጸተ ሲልም በተመሳሳይ እንደ ሰው የሚያዝን የሚጸጸት ስሜት ያለው ሳይሆን የኃጢአታችን ብዛት የሚያሳዝን የሚያጸጽት መሆኑን ለመግለጽ ነው።
@Orthodoxbiblestudy

ይቀጥላል...
5.6K views18:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-24 21:44:21 ይህን ሊንክ ለኦርቶዶክሳዊያን ቤተሰቦቻችሁና ጓደኞቻችሁ በስልክ መልዕክት በመላክ አስገቧቸው። https://t.me/defend_orthodoxy_EOTC_Followers
5.4K views18:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-23 00:33:12 ለቀራንብትኪ:- እመቤቴ ኪዳነ ምሕረት ሆይ የዓይኖችን እይታና አገላለጥ ለመጠበቅና ለመንከባከብ ለተፈጠሩ ቀራንብቶችሽ ሰላምታ ይገባል።

የቃል ኪዳኗ እመቤት ሆይ ያለ ዘርዓ ብእሲ የወለድሽውን ልጅሽን ኃጥአን እንኳን ቢሆኑ ስምሽን ከጠሩ እምርልሻለሁ ስትል የገባህልኝ ቃል ኪዳን ወዴት አለ ብለሽ አሳስቢው።

ለቃልኪ፦ እመቤቴ ኪዳነ ምሕረት ሆይ የተጎናጸፈ በብሥራተ መልዓክ በገብርኤል ቃል ቃልን ለተቀበለ ቃልሽ ሰላምታ ይገባል።

የቃልኪዳኗ እመቤት ሆይ የእግዚአብሔር የልዑል ኃይሉ ማደርያው ሆነሻልና ኃጥአን መዳን ወይም መጽደቅ በሚችሉበት ገንዘብ የይቅርታዋ የቸርነቱን ቃል ኪዳን እንኳን ሰጠሽ እሰይ እሰይ እያልን እናመሰግንሻለን።

ለጉርዔኪ:-እመቤቴ ኪዳነ ምሕረት ሆይ መራራውን ከጣፋጭ በየወገኑ ለሚለይ ንዑድ ክቡር ለሚሆን ጒረሮሽ ሰላምታ ይገባል።

የቃል ኪዳኗ እመቤት ሆይ እመቤቴ ሆይ እንግዲህ ስለ ቸርነትሽ ምን ውለታ እከፍላለሁ። ኃይሌ ደካማ በመሆኑና በሁለት አቅጣጫ የተደቀነውን ልዩ ፈተና ልወጣው ባለመቻሌ ዓለም ጠባኛለችና። ነገር ግን እናት ሆይ በቀላል ኪዳንሽ አረጋጊኝ።

ለእራኅኪ ፦ እመቤቴ ኪዳነ ምሕረት ሆይ በታላቋ መቅደሰ ኦሪት ሳለሽ ሰማያውያን መላዕክት ያመጡልሽን ሰማያዊ ሕብስትና ሰማያዊ መጠጥ ለተቀበሉ ለእጆችሽ መዳፍ ሰላምታ ይገባል።

የቃልኪዳኗ እመቤት ሆይ እንደዚህም ሁሉ ጥርኝ ውሃ ለተጠማ አጠጥቼ ብገኝ ጥቂቷን ስጦታዬን እንደተመረጠ የሠርክ መስዋዕት አድርጎ ቃል ኪዳንሽ ይቀበልልኝ።

[ መልክአ ኪዳነ ምሕረት]

እንኳን አደረሳችሁ!
5.9K views21:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-13 13:35:58 በድጋሚ በመጠየቁ ለሁለተኛ ጊዜ የተለቀቀ
ጥያቄ#
ይህን ጥቅስ ብታብራሩልን?

"ስለ እነርሱም ሊያማልድ ዘወትር በህይወት ይኖራል።" ዕብ 7:25

ስሁታን ይህን በመጥቀስ ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ እኛ ያማልዳል በማለት ይናገራሉ:: ክርሰቶስ ግን ከትንሳኤው በኋላ በስጋዉ ወራት (በምድር ሳለ) እንደምናውቀው እንዳይደለ ቅዱስ ጳውሎስ አስተምሮናል፡፡ 2ኛ ቆሮ 5:19-21ን አንብቡ!

በሐዋ 7 ፡55 ላይ ቀዳሜ ሰማዐት ቅዱስ እስጢፋኖስ "ክርስቶስን በአብ ቀኝ ቆሞ አየዋለሁ" ካለ በኋላ በ ቁጥር 60 ላይ በድንጋይ ለወገሩት "ኃጢአታቸውን አትቁጠርባቸው" አለ እንጂ "አማልዳቸው አላለም" ምክንያቱም እርሱ አማላጅ ሳይሆን ይቅር ባይ: መሐሪ ነውና ነው፡፡ ወደ ጥቅሱ ትርጉም ስንሄድ ከዕብ 7፦25 በፊት ስታነቡ የሌዊ ክህነትንና የክርስቶስን ሊቀ
ካህንነት እያነፃፀረ ነው የመጣው። የሌዊ ክህነት ፍፅምነት ያለውን ዕርቅ ማምጣት እንዳልቻለ ክርስቶስ ግን እርሱ
ሊቀ ካህን ነውና መስዋዕት አቅራቢ መስዋዕት ተቀባይ ራሱ መስዋዕት ራሱ
ሆኖ ፍፁምነት ያለው እርቅን እንዳደረገ ይገልፃል፡፡

ዕብ 7፦25ን ላይ "ስለ እነርሱም ሊያማልድ ዘወትር ይኖራል" የተባለው፦

አንዴ የፈፀማት የእርቅ ስራ ለዘላለም ከጥንተ በደልና ከእርግማን የምታድን መሆኗን ሲገልፅ ነው። አምላክ ቀንና ሌሊት ይሁኑ ብሎ አንድ ጊዜ
የተናገራት ቃል ዛሬም ቢሆን ቀንና ሌሊት ሁኑ በተባሉበት ሆነው ፀንተው እንደሚኖሩ ሁሉ ክርስቶስም በመስቀል ላየ የፈፀማት
የእርቅ ስራ ዘላለማዊነቷን ከጥንተ በደልና ከእርግማን የምታድን መሆኗን ሲገልፅ ነው።

በብሉይ ኪዳን የኦሪት ሊቀ ካህናቱ የእንስሳት ደምን ይዘው በየአመቱ
ለሃጢአት ስርየት ወደ መቅደስ ይገቡ ነበር። ክርስቶስ ግን እንደ ኦሪት ካህናት
ያይደለ ራሱ መስዋዕት አቅራቢ፣ራሱ መስዋዕት ተቀባይ እና ራሱ መስዋዕት ሆኖ
አንዴ መፈፀሙን የሚያስረዳና። በቤተ መቅደስ የምንቀበለው ስጋ እና ደሙ ከእለተ አርቡ ጋር የማትለይ በመሆኗ ዘወትር ሲያስታርቀን
እንደሚኖር ሲገልጥ ነው። ይህ ሁልጊዜ የሚፈተት ስጋ እና ደም አንድ ጊዜ የቀረበ የእግዚአብሔር ስጋና ደም ነውና በመለኮት ህያው ሆኖ በየጊዜው በወልደ እግዚአብሔር አምነው የሚመጡትን ሁሉ ህይወት እየሰጠ ሲያስታርቅ የሚኖር በመሆኑ ነው፡፡ ይህም በንስሐ ተመልሰን ከእግዚአብሔር ጋር የምንታረቀው በስጋ ወደሙ ነው፡፡ "ወደርሱ የሚመጡትን ፈፅሞ ሊያድናቸው ይችላል" ተብሏልና:: በራሱ ይቅር ባይ፣ መሐሪ ሐጥያት የሚያነፃ እንጂ ምህረት የሚለምን ( አማላጅ) አይደለም፡፡ ለዚህም ነው ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ "የልጁ የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ከኃጢአት ሁሉ ያነፃል፡፡" 1ኛ ዮሐ 1:7 ያለው፡፡

ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅም ይህን በተረጎመበት ድርሳኑ እነዲህ ብሏል፡፡

"የቀደሙት ሊቃነ ካህናት መዋትያን (የሚሞቱ) ስለነበሩ ብዙ ናቸው።እርሱ ግን የማይሞት ሕያው ስለኾነ አንድ ነው። የማይሞትም ስለኾነ እርሱን አምነው የሚመጡትን ኹሉ ሊያድናቸው ይቻለዋል።እንደምንስ ያድናቸዋል? የሚል ሰው ካለም በቅዱስ ሥጋውና በክቡር ደሙ ብለን እንመልስለታለን።በሃይማኖት በንስሐ ወደ እርሱ የሚቀርቡትን የሚያድናቸው በዕለተ ዓርብ ብቻ አይደለም። ከዚያ በኃላም ጭምር እንጂ። በወደደበትም ጊዜ ለመነላቸው። ኹልአንድ ጊዜ ይለምናል ብሎ የሚያስብ ከቶ እንደምን ይኖራል? ጻድቃንስ እንኳ ጊዜ በለመኑት ልመና የሚሹትን የሚያገኙ አይደለምን?...ሐዋርያውም ኹል ጊዜ ቁሞ የሚያገለግል እንዳያስመስሉት በማሰብ በመትጋት መሥዋዕት አንድ ጊዜ እንደሠዋ አስረዳ።አንድ ጊዜ ሰው እንደኾነ አንድ ጊዜ ተሾመ፤ አንድ ጊዜ እንደተሾመ አንድ ጊዜ አገለገለ። ሰው በኾነ ጊዜ የሰውነትን ሥራ በመሥራት ጸንቶ እንዳልኖረ ኹሉ ባገለገለ ጊዜም በማገልገልም ጸንቶ አልኖረም።አኹን ቢያገለግል ኖሮ ቆመ እንጂ ተቀመጠ ባላለ ነበር። መሥዋዕቱ ቁርጥ ልመናውን አንድ ጊዜ ወደ እዝነ አብ (በአብ ጆሮ) ወደ ገጸ አብ (በአብ ፊት) የደረሰች ሰለኾነች እንደቀደሙት ሊቃነ ካህናት ኹል ጊዜ ሊያገለግል አያስፈልገውም::"

በተክለ ማርያም

ወስብሀት ለእግዚአብሔር!
@mnenteyiklo
8.4K views10:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-10-28 20:53:51
24.3K views17:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-10-28 20:53:03 እንደምን ቆያችሁ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች?

በቴሌግራም የሚተላለፉ አንዳንድ ቻነሎች ላይ በቅዱስ ሲኖዶስ ተወግዘው የተለዩ ግለሰቦችን ዲያቆን መሪጌታ መጋቤ ሐዲስ በሚል ስም ትምህርታቸውን እየለቀቁ ይገኛሉ። እንዲህ የሚያደርጉ ቻነሎች አውቀውም ይሁን ሳያውቁ በየዋሕነት ሊሆን ይችላልና ከዚህ እንድትጠበቁ ልናሳስባችሁ እንወዳለን። ዲ/ን አሸናፊ መኮንን በቅዱስ ሲኖዶስ ተወግዞ የተለየ እንደነበር ይታወቃል። የርሱን ስብከት ኦርቶዶክሳዊ አድርገው (አስመስለው) የሚያቀርቡ ቻነሎችን ታዝበናል። ከነዚህም መካከል "መልካም እረኛ" ፤ "ፍኖተ ቅዱሳን" የተሰኘና ሌሎች የቴሌግራም ቻነሎች ይገኙበታል። እናም ቤተ ክርስቲያን ከማታውቃቸው አስተማሪዎች እንድትጠበቁ አደራ እንላለን። "አእመረ አሸብር" የተባለ ግለሰብም ራሱን መጋቤ ብሉይ ብሎ የሚጠራ ከቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ የተለየ ትምህርት የሚያስተምርና የተለየ ሆኖ ሳለ ለማደናገር በቤተ ክርስቲያን ስም ሲጠቀም ነበር። ምንም እንኳ ክፉውን ዛፍ ከፍሬው ማወቅ ቢቻልም አንዳንዴ ግን በረቀቀ መንገድ ምንፍቅናቸውን እውትን ከሐሰት ቀላቅለው ያማረ አስመስለው ስለሚያስተምሩ መጠንቀቅ ያሻል!

ከዚህ በፊት ቤተ ክርስቲያን አውግዛ ለይታቸው የነበሩት ሰዎች በፎቶ ከታች ተያይዟል። ለሌሎችም ሼር በማድረግ ከስሕተት አካሄድ ሌሎችን ይጠብቁ!
16.2K viewsedited  17:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-10-15 16:47:52
12.0K views13:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-10-15 16:46:48 ዳሰሳ መጽሐፍ (book review )

(ዲ/ን ዘአማኑኤል ገዛኸኝ)

የመጽሐፉ ርዕስ :- ትምህርተ ጽድቅ

የመጽሐፉ አዘጋጅ :- ዲ/ን ዮሐንስ ጌታቸው

የገጽ ብዛት :- 351

መቼተ ኅትመት :- አዲስ አበባ ፡ 2013

የመጽሐፉ ዋጋ :- 200 ብር
መግቢያ

ይህ የዲያቆን ዮሐንስ መጽሐፍ ዕቅበተ እምነታዊ (APOLOGETIC) ይዘት ሲኖረው በዋናነትም በነገረ ማርያምና በነገረ ክርስቶስ ዙርያ ከቀደሙት ዘመናት አንስቶ አሁን ድረስ ሲያከራክሩ ሲያወያዩ የነበሩ ጉዳዮችን እያነሳ የብዙ ቀደምት አበውን (Early Church fathers) አስተምህሮና ምስክርነትን በመግለጥ ጥሬውን አብስሎ ፣ አንኳሩን አድቅቆ ፣ የተበተነውን ሰብስቦ፣ የረቀቀውን አጉልቶ ፣ የተቋጠረውን ፈትቶ የሚያብራራ "ማለፊያ ነው" የሚያሰኝ መጽሐፍ ነው።

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ " ቅዱሳት መጽሕፍትን ስታነቡ ገጸ ንባቡን ማንበብ ሳይኾን የጽሑፉን ሐሳብመፈለግ ይገባችኋል። ማንኛውም ሰው ምሥጢሩን መሠረት ሳያደርግቃላቶችንና የተጻፉትን ጽሑፎች ብቻ የሚመለከት ከኾነ ብዙ ስሕተቶችን ይፈጽማል” እንዲል ሁሉም የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች በጥሬው የሚበሉ እየመሰላቸው ግራ ለሚጋቡ ምዕመናን ንባባቸውን ከቤተክርስቲያን ጋር
( ecclesiastical reading) እንዲሆን በማድረግ ከስህተት
የሚጠብቅ መጽሐፍ ነው ።

ምክንያተ- ጽሒፍ

አጽራረ ሃይማኖት የሆኑ ትምህርቶች ዛሬ እንደ አሸን ቢፈሉም መነሻቸው ግን ከፍጥረተ መላእክት ጀምሮ ነበር ። በኋላም
በዘመነ አበው ፣ ዘመነ ነቢያት፣ በዘመነ ሐዋርያት፣ በሐዋርያነ
አበው ዛሬም ድረስ ቤተ ክርስቲያንን ሲፈትን የኖረ ነው ።
ምንም እንኳ አርዮስ በስጋ ቢሞት በመንፈስ የወለዳቸው ብዙ
አርዮሳውያን አሉ ፤ መቅዶንዮስ በአካል ባይኖርም በመንፈስ
ያደረባቸው ነፍስን የሚገድሉ ትምህርቶችን የሚነዙ ሐሳውያን
አሉና ዛሬም እነ ቅዱስ አትናቴዎስ ፣ ጎርጎርዮስ እነ ሳዊሮስ
በመምህራነ ቤ/ክ አድረው ያስተምራሉ ፤ መጽሐፍትን ያጽፋሉ
፤ ሕይወትን ይሰጣሉ ።

ይህም መጽሕፍ ትኩረት የሚያደርገው በተአምረ ማርያምና
በነገረ ክርስቶስትምህርት ላይ በሚነሡ ጥያቄዎች መልስ ላይ
ነው። የተአምረ ማርያምንሥራቸው አድርገው ምእመናንን
ስለሚያደናግሩበት ምእመናንን ለመጠበቅ በጉዳዩ ላይ
የጥብቅና ጽሑፍ ማዘጋጀት አስፈላጊ ስለ ነበር ጸሐፊው
እነዚህን ችግሮች ከግምት ውስጥ በማስገባት ይህን መጽሐፍ አዘጋጅቷል ።

ሐተታ

በዚህ "ትምህርተ ጽድቅ" በተሰኘው መጽሐፍ አዘጋጁን
ሊያስመሰግነው የሚችሉ ብዙ አዳዲስ ነገሮች ይዞ የመጣ
ቢሆንም በተለይ ግን ከምንጭ አንጻርም ሊሆን ይችላል
በብዙ የነገረ ማርያም መጻሕፍት ያልተዳሰሱ አንዳንድ የነገረ
ማርያም ትምህርቶችን ሰፊ ዳሰሳ (broad overview) በማድረግና ሀገርኛና የባሕር ማዶ ተጨባጭ ምንጮችን (concrete sources ) በመጠቀም " ይበል " የሚያስብል ማብራርያ ሰጥቷል ።

ባጠቃላይም መጽሐፉ ሁለት ክፍል ፣ አራት ምዕራፎች
ሲኖሩት በክፍል አንድ ተአምረ ማርያምን መነሻ በማድረግ
የተአምር ምንነት ፣ ጥቅምና መገለጫዎችን ከብዙ ነቅዐ
መጻሕፍት ትንታኔ ጋር ማብራርያ ይሰጣል ። በተለይም ነገረ
ማርያምን(mariology) በተመለከተ የዘመኑ አሳቾች
ለራሳቸው እንዲመቻቸው በማድረግ ተአምረ ማርያምን
በማጣመምና የዋሀንን በማሳት ያሉትን የሚረታና በእምነት ያሉትንም የሚያጸና ገለጻ የቀረበበት ክፍል ነው። አንዳንዶች በመንፈሰ ንስጥሮስ ሆነው የአውሬው አፍ ተሰጥቷቸው ስለምን ለድንግል ማርያም ይህን ያህል ክብር ሰጣችኋት? ከክርስቶስ አስበለጣችኋት ! እያሉ የስድብን ነገር ለሚያነሱት አፋቸውን የሚያዘጋና ማክሲሚልያን የተባለው ሊቅ እንደተናገረው" ቅድስት ድንግል ማርያምን መውደድ ከሚገባኝ መጠን በላይ አልፌ ወድጄያት ይሆን? ብለህ ሥጋት አይግባህ። ኢየሱስ ክርስቶስ ከወደዳት በላይ
ልትወዳት አትችልምና" እንዳለው ገና ከዚህ በላይ እንወዳት
ዘንድ ፍቅሯን የሚያሳድርብን የመጽሐፉ ክፍል ነው ።

በክፍል ሁለትም በነገረ ክርስቶስ(christology) ዙርያ
ለሚነሱ የነገረ ድኅነት (soteriology) ይዘት ያላቸውን
የመናፍቃን ጥያቄዎች የመጽሐፍ ቅዱሱን ነገረ መለኮታዊ
ዐውድ( biblical Theology) ጠብቆ " መንክር "
በሚያስብል በአበው ትምህርት ተቀምሞ የተዘጋጀ መጽሐፍ ነው።
11.8K viewsedited  13:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ