Get Mystery Box with random crypto!

ምን እንጠይቅሎ?

የቴሌግራም ቻናል አርማ mnenteyiklo — ምን እንጠይቅሎ?
የቴሌግራም ቻናል አርማ mnenteyiklo — ምን እንጠይቅሎ?
የሰርጥ አድራሻ: @mnenteyiklo
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 6.20K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ ቻናል የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያንን የተመለከቱ ሃይማኖታዊ ጥያቄዎችን ለመመለስና ለመማማር ታስቦ የተከፈተ መንፈሳዊ ቻናል ነው።
ለሚኖራችሁ ማንኛውም ሀሳብ ጥያቄና አስተያየት

👉 @MenbereM
👉 @teklemaryam19
ልታደርሱን ትችላላችሁ

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-01-31 10:05:32 #ስለ_ቄደር_ጥምቀት_እና_ለመጠመቅ_የሚያስፈልጉ_መስፈርቶች

#መልስ

ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የልጅነት ጥምቀትን አንድ ጊዜ ትፈጽማለች፡፡ "አንድ ጌታ አንድ ሃይማኖት አንዲት ጥምቀት" ኤፌ. 4:5 ከሌላ ቤተ እምነት የነበሩ ሰዎች ቢመለሱ አስተምራ አሳምና ታጠምቃለች፡፡

ቀድሞ በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን ተጠምቆ ኋላ ግን ወደ ሌላ እምነት ቢገባ ተናዞ (ንስሐ ገብቶ) በማየ ጸሎት (መጽሐፈ ቄደር ተደግሞለት) ይረጫል እንጂ ድጋሚ አይጠመቅም፡፡ ቄደር የንስሐ እጽበት ነው ፡፡ ያደፈ ልብስ እንደሚታጠብ ሁሉ ይህም ሰው ንጽሕት እምነቱን አሳድፏልና ከኃጢአቱ ለመታጠቡ ምልክት ይሆን ዘንድ በማየ ጸሎት ይታጠባል፡፡

በዓረብኛ ቀድር ይባላል፡፡ ትርጉሙም እድፍ ርኩስ ማለት ነው፡፡ መጽሐፉ ወደ ግዕዝ ከተተረጎመ በኋላ ቄድር ተብሏል፡፡

በአሕመድ ግራኝ ወረራ ጊዜ በ16ቱ ዓመታት በተቆጣጠረው ቦታ ሁሉ የሚኖር ትልቅም ይሁን ትንሽ ካልሰለመ ለመኖር አይችልም ነበር፡፡ ከዚህም የተነሳ ብዙ ሕዝብ ሰልሟል፡፡ የሰለመውን ሕዝብ እንደገና ወደ ክርስትና ለመመለስ ገላውዴዎስ መጽሐፈ ቄደርን ከዓረብኛ ወደ ግዕዝ አስተርጉመውታል፡፡ ቄደር የንስሐ ጸሎት ማለት ነው፡፡ አንዳንድ መምህራን ቄደርን ከዮሐንስ ጥምቀት ጋር ያያይዙታል፡፡ የዮሐንስ ጥምቀት የንስሐ እንደሆነ በመጽሐፍ ቅዱስ ተጠቅሷል፡፡ ስለዚህም ነው የቄደር ጥምቀትን ከዮሐንስ ጥምቀት ጋር የሚያያይዙት፡፡

በቤተ ክርስቲያን ስደት ከተጀመረ አንስቶ ስደት ፈርተው ከሃይማኖታቸው የወጡትን ሁሉ ለመመለስ የቤተ ክርስቲያን አባቶች ይህን መጽሐፍ አዘጋጅተዋል፡፡ በመጽሐፉ መጀመርያም "መጽሐፈ ቄደር ሃይማኖቱን ለካደ ወይም ላረከሰ ወንድም ይሁን ሴት የወንድ መነኩሴም ይሁን የሴት መነኩሲት የቤተ ክርስቲያን መምህራን ያዘጋጁት ነው፡፡

የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በዚሁ መጽሐፍ ተጠቅማ የጠፉትን በጎቿን መልሳለች፡፡ በመጽሐፉ የሰፈረው ጸሎት ይደገምና ውሃው በተመለሱት ሰዎች ላይ ይረጫል፡፡ ወይም ይጠመቁታል፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
በወንድም ተክለማርያም
@Mnenteyiklo @Mnenteyiklo
7.5K views07:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-13 22:38:32 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
በክርስቶስ ልጆቼ ሰላም ለእናንተ ይሁን!
አንድ አባት ልጆቹን ሲመክር እንዲህ አለ። "ክፉ ሀሳብና ስለ ጊዜያዊ ስኬቶች ወይም ኃላፊነቶች አብዝቶ የሚጨነቅ ሰው በነፍሱ ለስንፍና ይዳረጋል። ለነፍሱ የሚጠቅመውን ለማድረግ ቸልተኛ ይሆናል። እንዲህ ዓይነት ሰው ካያችሁ በነፍሱ የታመመ መሆኑን አውቃችሁ እዘኑለት። ሥርዓተ አምልኮን በመከታተል ጠንካራ የሆኑ አማኞች ላይም ወደ ክርስቶስ ፍቅር ለመድረስ ወሳኝ በሆኑ የሕይወት ልምምዶች ላይ ሰንፈው ልታዩዋቸው ትችላላችሁ። ስንፍና በእግዚአብሔር ዘንድ እጅግ የተጠላ ነው፤ ኃጢአትም ነው። ከዚያም በላይ "ከዚህ በላይ ከእኔ ምን ይፈለጋል?" የሚል ትዕቢትም ነው::
ለምሳሌ ማታ ወደ መኝታችሁ ስትሄዱ በራችሁን መዝጋትን በቸልተኝነት ልትተውትና ለምን አለዘጋችሁትም? ተብላችሁ ስትጠየቁ ደከመኝ ወይም ረሳሁት ልትሉ አትችሉም። በእውነቱ ሕይወትን አደጋ ላይ ጥሎ ደከመኝ ወይም ረሳሁት ማለት ምን ዓይነት መልስ ነው። ይህን መልስ በሰጡን ሰዎች ላይ ምን ያህል ጊዜ እንደተቆጣን አስቡ። ኃላፊነታቸውን በዘነጉ አገልጋዮቻችን ላይ ወይም የሚጠበቅባቸውን ከማድረግ በጨዋታ ተታለው በረሱ ልጆቻችን ላይ ስንት ጊዜ ተቆጥተን ወይም ቀጥተናቸው ይሆን? የእነርሱን ስንፍና መታገሥ የማንችል ከሆነ እኛስ ለስንፍናችን ከጌታ ዘንድ ርኅራኄን ለምን እንጠብቃለን? እኔኮ ኃጢአት አልሠራሁም ሰነፍሁ እንጂ ብንል ''አንተ ሀኬተኛ ባሪያ ... " ተብሎ ወደ ጨለማ እንዲጣል ከተፈረደበት ባሪያ በምን እንለያለን?
ቸልተኛ፣ ዝንጉና ሰነፍ በሆንን መጠን መከራችን በዚያው ልክ ይሆናል። ጥንቁቅ፣ ትጉህና ለክርስቶስ ፍቅር የምንሳሳ በሆነ መጠን ደግሞ ደስታችንም እንዲሁ ይበዛል። ልጆቼ ከሰነፍ ኃጢአተኛ ይሻላል። ኃጢአተኛ የንስሐ ተስፋ አለው፡፡ ለሰነፍ ተሰፋው ምንድር ነው?"
በክርስቶስ አገልጋያችሁ!
@ktamerat @ktamerat @ktamerat @ktamerat
5.5K views19:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-04-06 20:39:53 የቀጠለ...

ሌላው 'ጸለለ' ለሚለው ግዕዙ በራሱ ሁለት አይነት ፍቺ (ትርጉም) አለው ጠብቆና ሲላላ "ጸለለ" ላልቶ ሲነበብ "መጥለል፣ መጥራት፣ በአየር ወይም በውኃ ላይ ተዘርግቶ መሄድ... አጽለለ ደግሞ አጠራ፣አጠለለ፣አሰፈፈ ፣ አንጓለለ" ተብሎ ይፈታል፡፡ ላልቶ ሲነበብ በግዕዝ አረባብ "ጸለለ፣ ይጸልል፣ ይጽልል፣ ጸሊል ሲሆን ግሱን በቅርብ የሴት አንቀጽ ሲረባ "ጸለለኪ፣ ይ'ጸ'ልለኪ፣ይጽልልኪ..." ይሆናል፡፡ በሉቃ. 1:35 ላይ ግን የተጠቀሰው ቃል በግዕዙ "መንፈስ ቅዱስ ይመጽዕ ላዕሌኪ ወኃይለ ልዑል ይ'ጼ'ልለኪ" ነው የሚለው፡፡ ከላይ እንደተመለከተው ግን ቃሉ ሲላላ ያለው የአረባብ መንገድ በሉቃስ ወንጌል ላይ ያለውን "ይ'ጼ'ልለኪ" አያስገኝም፡፡

"ጸለለ" ሲጠብቅ ደግሞ ትርጓሜው "መጽለል፣ በላይ ሆኖ ማጥላት፣ ጥላ መሆን፣ ማልበስ፣ መክደን፣ መሸፈን፤ መከለል፤ መጋረድ" ተብሎ ይፈታል፡፡ ጠብቆ ሲነበብ ባለው የአረባብ መንገድ ነው በሉቃስ ወንጌል ላይ የተጻፈውን ይ'ጼ'ልለኪ የሚለውን የሚያስገኘው፡፡

ስለዚህ ጠብቆ ሲነበብ ካለው ትርጉም ጋር የሚሄድ መሆኑን ማወቅ ያስፈልጋል፡፡ ይህንም በሉቃ 1:35 ተክተን ስናነበው "የልዑል ኃይል ይጋርድሻል፣ በላይ ሆኖ ያጠላልሻል፣ ጥላ ይሆንሻል፣ ያለብስሻል፣ ይከድንሻል፣ ይሸፍንሻል፣ ይከልልሻል" የሚል ትርጉም ይሰጣል፡፡ "ማንጓለል፣ ማጥራት፣ ማጥለል፣ የሚል ግስ እና በሁለተኛ አንቀጽ ለእመቤታችን አልተነገረም፡፡

በእንግሊዘኛው መጽሐፍ ቅዱስም "The Holy Ghost Shall come up on thee, and the power of the highest shall 'overshadow' thee" luke 1:35 ገልጾታል፡፡ ይጸልልሻል የሚለውን "Overshadow" በማለት ነው የሚያስቀምጠው፡፡ ይህም ቃል "To shelter, to protect " ጥላ መሆን (አስቀድሞ) መጋረድ ተብሎ ይፈታል፡፡

ስለዚህም ቃሉ በኃይለ ልዑል መጋረድ መጠበቋን ፣ መሸፈኗን ከኃጢአት መከልከሏን ነው፡፡" የሚያሳየው:: በማር. 9:7፣ ሉቃ 9:34፣ ማቴ 17:5 ላይም Overshadow የሚለው መጋረድ ወይም መከለል በሚል የተፈታ ነው፡፡ ጸለለ የሚለውም ይህን የተከተለ ነው፡፡

ዋቢ፦ ሐውልተ ስምዕ (መምህር ኃይለ ማርያም ላቀው)
- ወልታ ጽድቅ (በአማን ነጸረ)
23.3K views17:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-04-06 20:32:43 ጥያቄ

በሉቃስ ወንጌል "መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል፡፡ የልዑልም ኃይል ይጸልልሻል ስለዚህ ከአንቺ የሚወለደው ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል" ሉቃ 1:35 ላይ ይጸልልሻል የተባለው ""መንፈስቅዱስ በማርያም ላይ አስቀድሞ መምጣት ያስፈለገበት ምክንያት ለመጽለል ( ለመጋረድ፣ ለማጥለል) ሲሆን ቀጥሎም ከተጋረደው ወይም ከተጠለለው ማንነቷ ውስጥ የሚወለደው ክርስቶስ " ቅዱሱ" የእግዚአብሄር ልጅ እንዲሆንና እንዲባል ነው።"" በማለት እመቤታችን ኃጢአት ነበረባት በማለት ተቃዋሚ መናፍቃን ያስተምራሉ::

መልስ

ቃሉን አስተውለን ከተመለከትነው እመቤታችን "ወንድ ስለማላውቅ ይህ እንዴት ይሆናል" ሉቃ. 1:34 በማለት ለጠየቀችው ጥያቄ ነው መልአኩ "መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል፡፡ የልዑልም ኃይል ይጸልልሻል ስለዚህ ከአንቺ የሚወለደው ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል" ሉቃ 1:35 በማለት የመለሰው በደል ኖሮባት ከዚያ ሊያነጻት አይደለም፡፡ ኃጢአት እንደሌለባትማ ከፍ ብሎ በሉቃ. 1:28 ላይ "ጸጋን የሞላብሽ ሆይ ጌታ ከአንቺ ጋር ነው፡፡ አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ አላት፡፡" በማለት መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል በረከት ሳይሆን መርገም በነበረበት ዘመን ብሩክት ብሎ አመስግኗታል፡፡ ጸጋ በጎደለበት ዘመን ጸጋን የተሞላሽ በማለት ኃጢአትና መርገም ያላገኛት እንደሆነች ተናግሯል፡፡

እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያምስ "ከሴቶች ተለይታ ጸጋን የተመላችና ከሴቶች ተለይታ የተባረከች" ናት፡፡ ሊቃውንትም ይህን ክፍል "ያንቺማ ጽንስ መቼ እንደሌሎች ሴቶች ጽንስ ነዋ መንፈስ ቅዱስ ያድርብሻል ኃይለ ልዑል ወልድ ሥጋሽን ይለብሳል፡፡" በማለት ተርጉመውታል፡፡

ሁለተኛው ተቃዋሚዎች "ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ የሆነው መንፈስ ቅዱስ ወዳንቺ ይመጣል" የሚለው ቃል ከተነገረ በኋላ ነው በማለት ይህ ግን በባህሪይው ቅዱስ የሆነ ጌታ ቅድስናን ስጋ ከለበሰ በኋላ ነው ያገኘው የሚለው የክህደት ትምህርት ነው፡፡ "በመጀመርያ ቃል ነበር ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበር፡፡ ቃልም እግዚአብሔር ነበር፡፡" ዮሐ 1:1 በማለት ቅድመ አለም ቃል (ወልድ) እግዚአብሔር እንደሆነ ተናግሯል፡፡ ቅድስናው የባህሪይው ከእመቤታችን ሲወለድ ያገኘው አልነበረም፡፡
11.8K views17:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-29 21:53:14 ጥያቄ

"ነገር ግን፥መልካምንና ክፉን ከሚያስታውቀው ዛፍ አትብላ ከርሱ በበላኽ ቀን ሞትን ትሞታለኽና።" ኦሪት ዘፍጥረት 3፥17 ላይ እግዚአብሔር አምላክ አዳምን ዕጸ በለስን በበላኽ ቀን ትሞታለህ ብሎታል። አዳም ግን የሞተው 930 ዓመት ከኖረ በኋላ እንደሆነ ነው መጽሐፍ ቅዱስ የሚነግረን። ታዲያ ምን ማለት ነው?

1ኛ. ሞት ማለት ከእግዚአብሔር መለየት ነው። ቅዱስ ጳውሎስ ለኤፌሶን ክርስቲያኖች በላከው መልዕክቱ "በበደላችኹና በኀጢአታችኹ ሙታን ነበራችኹ በእነርሱም፥በዚህ ዓለም እንዳለው ኑሮ፥" ኤፌ. 2፥1::

አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስም አንተን ከመከተሌ በፊት አባቴን እቀብር ዘንድ ፍቀድልኝ ብሎ ለጠየቀው ሰው "ኢየሱስም፦ተከተለኝ፥ሙታናቸውንም እንዲቀብሩ ሙታንን ተዋቸው አለው።" ማቴ. 8:22 ብሎታል። የሞተ ሰው የሞተን ሰው የሚቀብር ሆኖ ሳይሆን የሞቱ ያለቸው ከእግዚአብሔር የተለዩ በኃጢአት የሚኖሩ ለማለት ነው። ስለዚህም አዳም የእግዚአብሔርን ትዕዛዝ ተላልፎ ኃጢአትን በማድረጉ ሞተ ተብሎ የነፍስ ሞቷ ከእግዚአብሔር መለየቷ ነውና።

2ኛ. በርግጥም አዳም ዕጸ በለስን በበላበት ቀን ሞቷል። "እናንተ ግን ወዳጆች ሆይ፥በጌታ ዘንድ አንድ ቀን እንደ ሺሕ ዓመት፥ሺሕ ዓመትም እንደ አንድ ቀን እንደ ኾነ ይህን አንድ ነገር አትርሱ።" 2ኛ ጴጥ.3:8። እንደተባለው በእግዚአብሔር አንድ ቀን የሰው 1000 ዓመት ተብሎ ተነግሯል። ከ አምስት ቀን ተኩል በኋላ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ ብሎ የገባለት ቃል ኪዳንም ምስጢሩ ከ 5500 ዓመት በኋላ ሰው ሆኖ እንደሚያድነው የሚናገር ነው።

ስለዚህ አዳምም ሆነ የአዳም ልጆች 1000 ዓመትን መኖር አልቻሉም። አዳም በ930 ዓመቱ ነው የሞተው። በዕድሜ ትልቁ የሚባለው ማቱሳላም 969 ዓመት ነው የኖረው። "ማቱሳላም የኖረበት ዘመን ዅሉ ዘጠኝ መቶ ስድሳ ዘጠኝ ዓመት ኾነ ሞተም።" ኦሪት ዘፍጥረት 5:27:: ስለዚህ 1000 ዓመትን ሰው መኖር አልቻለም። በበላበት ቀን ሞቷል የተባለው በዚህ ይተረጎማል። በእግዚአብሔር ዘንድ አንድ ቀን አንድ ሺህ ዓመት ነው ተብሏልና።

" 2 በአሥራ ዘጠኝኛው ኢዮቤልዩ መጨረሻ በሰባተኛው ሱባዔ በስድስተኛው ዓመት አዳም ሞተ ልጆቹም ሁሉ በተፈጠረበት ምድር ቀበሩት።

3 እርሱም ኣስቀድሞ በምድር ተቀበረ።ከሺህ ዓመትም ሰባ ዓመትን አጐደለ ይህችውም በሰማይ ጽላት እንደ አንዲት ቀን ነበረች።

4 እርሱም ኣስቀድሞ በምድር ተቀበረ።ከሺህ ዓመትም ሰባ ዓመትን አጐደለ ይህችውም በሰማይ ጽላት እንደ አንዲት ቀን ነበረች።" መጽሐፈ ኩፋሌ 6:2-4 በማለት በበላበት ቀን መሞቱን ያስረዳል።
10.7K views18:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-27 18:46:32 ጥያቄዎቻችሁን በ
@MenbereM
@EYOAB14

በኩል ልታደርሱን ትችላላችሁ።
6.8K views15:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-27 16:37:12 እንደምን ሰነበታችሁ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች!

ኦርቶዶክሳዊ ሆነው ሳይሆን መስለው ለማሳሳት የተነሱ ብዙዎች በመካከላችን አሉ። ሰይጣን ራሱ የሐሰት አባት የበጎ ነገር ሁሉ ጠላት ሆኖ ሳለ ሰውን ለማሳሳት ግን "ራሱን የብርሃን መልአክ አስመስሎ እንኳ ይገለጣል" እንዲህ በመገለጡ ግን የብርሃን መልአክ አይሆንም። ቅዱስ ጳውሎስ በዘመኑ የተነሱትን አሳሳቾች እንዲህ ይገልጻቸዋል።

2ኛ ቆሮ 11:13-15

" 13 እንደ እነዚህ ያሉ ሰዎች የክርስቶስን ሐዋርያት እንዲመስሉ ራሳቸውን እየለወጡ፥ውሸተኛዎች ሐዋርያትና ተንኰለኛዎች ሠራተኛዎች ናቸውና።

14 ይህም ድንቅ አይደለም ሰይጣን ራሱ የብርሃንን መልአክ እንዲመስል ራሱን ይለውጣልና።

15 እንግዲህ አገልጋዮቹ ደግሞ የጽድቅን አገልጋዮች እንዲመስሉ ራሳቸውን ቢለውጡ ታላቅ ነገር አይደለም ፍጻሜያቸውም እንደ ሥራቸው ይኾናል።"


በቴሌግራም መማማርያ መድረኮች ውስጥም እኛን ሳይሆኑ መስለው ለማሳሳት የገቡ ብዙዎች አሉ። እንደምሳሌም ከቅዱሳን ሕብረት የሌለው ራሱን '"ጉባኤ ቅዱሳን'" ብሎ የሚጠራው የቴሌ ግራም ቻነልም የተሃድሶ መናፍቃን (Heretics) ትምህርቶችን እያሰራጨ ይገኛል። ባለማወቅ የገባችሁ የኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ልሳን አለመሆኑን ተገንዝባችሁ እንድትወጡ ስል እናሳስባለን! ከዚህና ይህን በመሰሉ አስመሳይ (በሐሰት ካልሆነ ራሳቸውን ችለው መቆም የማይችሉ) ስማቸው ኦርቶዶክሳዊ የሚመስል ሥራቸው ግን ፕሮቴስታንታዊ ከሆኑ ቻነሎች ራሳችሁንና ሌሎች ወንድም እህቶቻችሁም ወደ ነዚህ ቻነሎች ባለማወቅ ተቀላቅለው ከሆነ እንዲለዩ ያድርጉ!

ቤተ ክርስቲያን ስንዱ እመቤት ናትና ማወቅ የምንፈልገውን በመጠየቅ እንመላለስ!

ተጠበቁ ተጠንቀቁ! ዛፍ ከፍሬው እንዲታወቅ ኦርቶዶክሳዊ ያልሆኑ ትምህርቶችንም ከትምህርታቸው እየለየን ይሁን!
7.4K viewsedited  13:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-13 15:53:10 የመስቀል ዓይነቶችና ስያሜያቸው

የመስቀል ዓይነቶች

1. የመጾር መስቀል

በቅዳሴ እና በማዕጠንት ጊዜ ሠራዒው ዲያቆን የሚይዘው ነው።

2. የእጅ መስቀል

ካህናት ምእመናንን የሚባርኩበት በእጅ የምትያዝ የመስቀል ዓይነት ናት።

3. የአንገት መስቀል

ምእመናን ለአምላካቸው ያላቸውን ፍቅር ለመግለጽ ከማዕተባቸው ጋር በአንገታቸው የሚያደርጉት ነው።

4. እርፈ መስቀል

በማንኪያ ቅርጽ ተሠርቶ በእጅታው ላይ የመስቀል ምልክት ያለበት ነው፤ ሠራዒው ዲያቆን በቅዳሴ ጊዜ የአምላካችንን ክቡር ደሙን ለምእመናን የሚያቀብልበት ነው፤እንዲሁም ጌታችን በእለተ አርብ የተወጋበት ጦር ምሳሌ ነው።

መስቀል ከተለያዩ ማዕድናት ይሰራል። ከተሰራበትም አንጻር የተለያዩ ምሳሌ ሰጥተውታል።

1. የእንጨት መስቀል

ጌታችን የተሰቀለው በዕጽ በእንጨት ላይ መሆኑን ለማመልከት ነው።
አዳም ዕጽ/ እንጨትን በልቶ ሞትን በማምጣቱ ክርስቶስም በእንጨት ተሰቀሎ ህይወትን ሊሰጠን በእንጨት መስቀል ተሰቀለ።

2. የብረት መስቀል

ጌታችን በአምስቱ ቅንዋተ ለመቸንከሩ ምሳሌ ነው።

3. የብር መስቀል

ይሁዳም በሠላሳ ብር አሳልፎ ስለመስጠቱ፤ በተጨማሪም ከብር ቢሰራ ተስፋን ዕድልን ያመለክታል።
ይኸውም እርሱ ለሰው ልጆች ሁሉ ቤዛ ሊሆን በደሙ ዋጋ ከፍሏልና ከእርሱ ተስፋ እንድናደርግ ያመለክተናል።

4. የወርቅ መስቀል

ከወርቅ ቢሰራ ወርቅ ንጹህ እንደሆነ ንጹሀ ባህርይ እድፈት የሌለው ጽኑ አንተ ነህ ብሎ ለመመስከር ነው።

5. የመዳብ መስቀል

መዳብ ቀለሙ ቀይ ይመስላል ጌታችን ለእኛ ብሎ ያፈሰሰው ደም ምሳሌ ነው።
ብዙዎች የመስቀል ጣላት ሆነው መስቀልን ጣኦት ነው ይላሉ ጣኦት ማለት ግን የሠይጣን ስም የሚጠራበት ፣የሚመለክበት ነው።

ከማዕዶት ዘተዋሕዶ ቻነል የተወሰደ
@mnenteyiklo @mnenteyiklo
12.2K views12:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-09 15:31:32 selam………
catolic ke ortodox yemileyebetn astemehero
betenegerugni?

1ኛ. የኦሬንታል (የተዋሕዶ) ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት ኢየሱስ ክርስቶስ በተዋሕዶ አንድ ባሕርይ ነው ሲሉ የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ደግሞ ኢየሱስ ክርስቶስ ሁለት ባህርያት አሉት ይላሉ።

2ኛ. የኦሬንታል (ተዋሕዶ) አብያተ ክርስቲያናት መንፈስ ቅዱስ ከአብ ብቻ የሰረጸ ሲሉ የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን መንፈስ ቅዱስ ከአብና ከወልድም ሰረጸ ትላለች።

3ኛ. የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ብዙ ሰዎች ለሰሩት ኃጢአት በመጸጸት ንስሐ ገብተው ሳይፈጽሙት በድንገት ሲሞቱ በመንግስተ ሰማያትና በገሃነመ እሳት መካከል ልዩ የሆነ ቦታ (መካነ ንስሐ-purgatory) ስላለ ነፍሶቻቸው ወደዚያ ሄደው ከኃጢአታቸው እስኪነጹ ድረስ መከራ እየተቀበሉ ቆይተው ኋላ ወደ መንግሥተ ሰማያት ይገባሉ በማለት ስታስተምር የኦርየንታል ኦርቶዶክስ (ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ) ይህን ትምሕርት አትቀበለውም።

4ኛ. የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የሮም ፖፕ የክርስቶስ እንደራሴና የአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ የበላይ ስለሆነ በመንበሩ ተቀምጦ (ተሠይሞ) በሚወስነው ሁሉ አይሳሳትም ብላ በ 1870 ዓ.ም በቫቲካን አንድ ጉባኤ የወሰነችውን የኦርየንታል ኦርቶዶክስ (ኦርዶክስ ተዋሕዶ) ቤተ ክርስቲያን ግን የቤተ ክርስቲያን መሪዎች በጉባኤ ተሰብስበው በተገኙበት በመንፈስ ቅዱስ መሪነት የተወሰነውና ለወደፊትም የሚወሰነው ውሳኔ (ድንጋጌ) ነው የማይሳሳት በማለት የአንድን ሰው የፖፑን አለመሳሳት አይቀበሉም። ፖፑ የሁሉ የበላይ ነው በማለት የአንድ ሰው የፖፑን አለመሳሳት አይቀበሉም።ፖፑ የሁሉ የበላይ ነው በማለት የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የምታስተምረውንም ይቃወማሉ።

5ኛ. የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ሕጻናትን አጥምቃ ሜሮን የየምትቀባቸው ነፍስ ካወቁ በኋላ ነው። የኦርየንታል ኦርትዶክስ ግን ሕጻናትን አጥምቀው ወዲያው ሜሮን ይቀቧቸዋል።

6ኛ. የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ለቀዳስያን ካህናት ስጋ ወደሙን ስትሰጥ ለምዕመናን ብቻ አቀብላ ደሙን አታቀብልም ነበር። ነገር ግን በቫቲካን ሁለት ጉባኤ ለምዕናንም ሥጋ ወደሙ እንዲሰጣቸው ተፈቅዷል። የኦርየንታል ኦርቶዶክስ ግን ለካህናትና ለምዕመናን ሥጋ ወደሙን ይሰጣሉ። ከዚህም ጋር ኦርቶዶክሳውያን የምንቀበለው የክርስቶስ ሥጋና ደም ነፍስ የተለየው መለኮት የተዋሐደው ነው ስንል ካቶሊካውያን ግን ነፍስ ያለው መለኮት የተዋሐደው ነው ይላሉ።

7ኛ.በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ሕጻናት ቅዱስ ቁርባን የሚቀበሉት ነፍስ ዐውቀው ሜሮን ከተቀቡ በኋላ ሲሆን በኦርየንታል ኦርቶዶክስ ግን ሕጻናት ከተጠመቁና ሜሮን ከተቀቡ በኋላ ወዲያው ይቆርባሉ።

8ኛ. እስፓኝ ውስጥ በተደረገችው በኤልቪራ ሲኖዶስ መሠረት የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ካህናት በመላ ሚስት አያገቡም። የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ (ኦርየንታል ኦርቶዶክስ) ካህናት ግን ከጳጳሳት በስተቀር ቀሳውስትና ዲያቆናት ከፈለጉ አንዳንድ ሚስት አግብተው ሥልጣነ ክህነት ተቀብለው ሊያገለግሉ ይችላሉ።

9ኛ. የካቶሊክ ካሕናት ጽሕማቸውን ሲላጩ የኦርየንታል ኦርቶዶክስ ካህናት ግን ያሳድጉታል።

10ኛ. የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን አብዛኛውን ጊዜ ከሥዕል በተጨማሪ ለጌታ ለእመቤታችን ለጻድቃንና ለሰማዕታት መታሰቢያ የድንጋይ ሐውልት ሲቀረጽላቸው በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ደግሞ አብዛኛውን ጊዜ በሥዕል ይሳላሉ።

(የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ሉሌ መልአኩ፤ ገጽ. 56-58)

@mnenteyiklo @mnenteyiklo
7.4K views12:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ