Get Mystery Box with random crypto!

መንፈሳዊ የህይወት ምክር

የቴሌግራም ቻናል አርማ menfesawimeker — መንፈሳዊ የህይወት ምክር
የቴሌግራም ቻናል አርማ menfesawimeker — መንፈሳዊ የህይወት ምክር
የሰርጥ አድራሻ: @menfesawimeker
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 23.40K
የሰርጥ መግለጫ

መንፈሳዊ የህይወት ምክር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን
ወዳጄ ሆይ ! መንፈሳዊ ተጋድሎን አትፍራ፥ ከእርሱም አትሽሽ፡፡ ተጋድሎ ከሌለ ምግባር ትሩፋትም የለምና፡፡ እምነትና ፍቅርም ካልተፈተኑ በእውን ከአንተ ጋር ስለ መኖራቸው ርግጠኛ መኾን አይቻልምና፡፡
ለ አስተያየት ወይም መንፈሳዊ ጥያቄ ካሎት
@menfesawimekerbot

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2021-03-15 18:22:10 “መልካም ያደረጉ ብዙ ሴቶች አሉ አንቺ ግን ከሁሉ ትበልጫለሽ፡፡” ምሳ. 31፡29

ክርስቶስን ያከበሩ፤ መንገዱን የተከተሉ ብዙ ሴቶች አሉ፤ እውነትን የመሰከሩ፤ ስለ ቃሉ የኖሩ ብዙ ሴቶች አሉ፤ መስዋዕትነትን የከፈሉ በሰማዕትነት ያለፉ ብዙ ሴቶች አሉ፤ ታላላቅ የምድር ነገስታትን፤ ታላላቅ ነቢያትን የወለዱ ብዙ ሴቶች አሉ፤ ከነዚህ ሁሉ ግን አንቺ ትበልጫለሽ፡፡

ቅድስት ድንግል ሆይ አንቺ እኮ፡- ሰማይ ዙፋኑ ምድር መረገጫው የሆነ፤ ድንቅ መካር ኃያል አምላክ የሰላም አለቃ፤ ሁሉ በእርሱ የሆነ ከሆነውም አንዳችም እንኳን ያለርሱ ያልሆነ፤ ዓለምን ሁሉ ከሞት ወደ ሕይወት የመለሰ፤ መንበሩን የሚሸከሙ ኪሩቤልና ሱራፌል የሚንቀጠቀጡለት፤ የሁሉ ፈጣሪ፤ የሁሉ አምላክ እናት ነሽ፡፡ በፊትም አሁንም ወደፊትም ካንቺ በቀር ፈጣሪዋን ልጄ ብላ የምትጠራ ሴት አልነበረችም፤ የለችም፤ አትኖርምም ክርስቶስም እናቴ ብሎ የሚጠራት ብቸኛዋ ሴት አንቺ ነሽ በእውነት ከሁሉ ትበልጫለሽ፡፡

እናት ስትሆኝ ድንግል፤ ድንግል ስትሆኝ እናት በእውነት ከሁሉ ትበልጫለሽ፡፡ ትውልድ ሁሉ ብጽዕት ብሎ የሚጠራሽ ብቸኛዋ ሴት በእውነት ከሁሉ ትበልጫለሽ፡፡ እግዚአብሔር መርጦና ጠብቆ ያስቀረሽ ዘር በእውነት ከሁሉ ትበልጫለሽ፡፡ ለዓለም ሁሉ ድህነት ምልክት የሆንሽ በእውነት ከሁሉ ትበልጫለሽ፡፡

እናቴ ሆይ እንግዲህ እኔ ምን ልናገር? ሺህ ቃላትን ብደረድር ያንቺን ክብር ልገልፀውስ እንደምን እችላለው? አዎ አሁንም እላለሁ “መልካም ያደረጉ ብዙ ሴቶች አሉ አንቺ ግን ከሁሉ ትበልጫለሽ፡፡” ምሳ. 31፡29
የቅድስት ድንግል ማርያም በረከቷ በሁላችን ላይ ይደር፤ ምልጃ ቃል ኪዳኗ ይጠብቀን፡፡ አሜን!!!

ለማንኛዉም አስተያየትዎ @menfesawimekerbot ይፆፋልኝ ይደርሰኛል::
@menfesawimeker
@menfesawimeker
98.3K views15:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-09-20 08:32:12 * ሀልወተ እግዚአብሔር *
ሀልወተ እግዚአብሔር ማለት የእግዚአብሔር መኖር ማለት ነው ። እግዚአብሔር የሚባል ነገር የለም የሚሉ አሉና ከሱ እንጀምር ። ታዲያ የእግዚአብሔር መኖር በምን ይታወቃል ? ቢሉ ። 1ኛ.በስነ ፍጥረት ይታወቃል ። ም/ቱም ፍጡር ካለ ፈጣሪ አለና ። ስዕል ካለ ሰዓሊው አለ ፣ ቤት ካለ አናፂ አለ ፣ ሙዚቃ ካለ ሙዚቀኛው አለ ማለት ነው ። ስለዚህ በዚ መሰረት ስናየው ይሄ ሁሉ ስነ ፍጥረት አስገኚ አካል ወይም ፈጣሪ አለው ማለት ነው ። 2ኛ. የሰው ልጆች ዝንባሌ ነው ።ይህም ማለት ግማሹ ሙስሊም ፣ ግማሹ ቡዲስት ፣ ግማሹ ክርስቲያን ፣ ግማሹ ባዕድ አምልኮ አምላኪ የሆነው ነብሱ ከውስጥ የፈጠራት አካል እንዳለ ስለምትጮህ ነው ። ስለዚ ይህም አንዱ የፈጣሪ መኖር ማስረጃ ነው ። 3ኛ.የቀናትና የወቅቶች መፈራረቅ ነው ። ይህም ለምሳሌ መብራት ሲጠፉና ሲመጣ መብራት ሀይል የሚባል አካል እንዳለ እንደምንረዳው ሁሉ ፡ የቀንና የማታ የበጋና የክረምት መፈራረቅም አምላክ እንዳለ ማስረጃ ናቸው ። ፀሀይን በቀን ጨረቃን በማታ ያሰለጠነ ቀኑን ለሰራዊት ሌሊቱን ለአራዊት ያደረገ አምላክ መሆኑን እናውቅበታለን ።የስነ ፍጥረት አይነቱ ብዛቱ ድንቅ ነው ። 1ፀሀይ ሆና ለአለም ሁሉ እንድታበራ ማን አደረጋት ? የዛፎቹ አይነት አንዳንዱ ቅጠሉ ሰፊ አንዳንዱ ቅጠሉ ቀጭን ፣ የአእዋፏቱ አይነት ፣ የአሶችና የሌሎች ባህር ውስጥ ያሉ ነብሳት መኖር ፣ ስናይ ፈጣሪ እንዳለ እንረዳበታለን ። ለውቅያኖሶች ዳርቻዎቻቸውን የወሰነላቸው ሰማይን በከዋክብት ምድርን በአበቦች ያስጌጠ ስራው ድንቅ የሆነ አምላክ የመኖሩ ማስረጃ ናቸው ። ሸክላና ተሽከርካሪ ፣ መርከብና አየር በራሪ ፣ ድልድይና አስፓልት ፣ መኪናና ሌሎችም ሞተር ነክ ነገሮች ፣ ታሪካውያን ህንፆዎች ፣ የሚያስገርሙ ነገሮች ሁሉ ያለ ሰሪ ፣ አትክልትና አዝርዕት ያለ መሬትና ያለ ዘሪ ፣ ልጅ ያለ እናትና አባት እንደማይገኝ ሁሉ ግዑዛንና ግዙፉን ጥቃቅንና ረቂቃን ፍጥረት ሁሉ ያለ ፈጣሪ እንዳልተገኙ እናምናለን ። ቅዱስ ጳውሎስ እንዳለው "የሚታየው ከማይታየው እንደሆነ እናምናለን" እንጂ ዳዊት በመዝሙር 13:1 "ሰነፍ በልቡ አምላክ የለም ይላል" እንዳለው አምላክ የለም አንልም
158.5K views05:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-09-18 14:16:24 † ጋብቻና የሰው ጥንተ ተፈጥሮ - ፩ †

አሁን የምናውቀው ዓይነት የመዋትያን ጋብቻ በገነት ውስጥ በነበረው የሰው ልጅ ሕይወት አስፈላጊ አልነበረም፡፡ ምንም እንኳን ለወደቀው የሰው ልጅ ድጋፍ እንዲኾን እግዚአብሔር የመሠረተው ቢኾንም፥ ከውድቀት በፊት ግን አልነበረም፡፡ እንዲህም ማለታችን በገነት ውስጥ የነበረው ድንግልና አሁን ከምናውቀው ዓይነት ድንግልና እንደሚለይና እጅግ እንደሚልቅ ኹሉ፥ በገነት ውስጥ የነበረው የአዳምና የሔዋን አንድነትም አሁን ከምናውቀው የባልና የሚስት አንድነት የሚለይና እጅግ የሚልቅ ነበር፡፡ በገነት ውስጥ የነበረው የአዳምና የሔዋን አንድነት ምሥጢራዊ አንድነት ነው፡፡ ሔዋን ለአዳም ረዳት ኾና ስትሰ’ጠው፥ አሁን በጋብቻ ውስጥ የምናውቀውን ዓይነት ረዳትነት እንድትሰጠው አልነበረም፡፡ አሁን በምናውቀው ዓይነት ጋብቻ ውስጥ ሚስት ለባሏ ረዳት ከምትኾንባቸው ነገሮች ዋናው ነገር፥ ፍትወት ሲበረታበት በዝሙት እንዳይወድቅ ሸክሙን ማቅለል ነው፡፡ ባልም እንደዚሁ ለሚስቱ! በገነት ውስጥ ከውድቀት በፊት የነበረው የሔዋን ረዳትነት ግን እንደዚህ አልነበረም፡፡ የተሰጠችው እንድታወራው፣ እንድታጽናናው፣ እኩል ክብሩን እንድትጋራ፣ በኹለንተናዋ እርሱን እንድትመስል ነበር፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ “በእንተ ድንግልና” በተባለ ተወዳጅ መጽሐፉ ይህን ሲያብራራውም እንዲህ ይላል፡-

“እግዚአብሔር ይህን ዓለም ለጥቅማችን ፈጥሮ ከፈጸመና ዝግጁ ካደረገ በኋላ፥ በመጨረሻ ይህ ዓለም ለእርሱ የተፈጠረለትን ሰውን ፈጠረ፡፡ ከተፈጠረ በኋላም የሰው ልጅ በገነት ኖረ፤ ለጋብቻ የሚኾን ምክንያትም አልነበረም፡፡ ሰው ረዳት ያስፈልገው ነበር፤ ወደ መኖርም መጣች (ተፈጠረች)፡፡ ያን ጊዜም ቢኾን [አሁን የምናውቀው ዓይነት የመዋትያን] ጋብቻ አልነበረም፡፡ ገና [አሁን በምናውቀው መንገድ] አልተገለጠም ነበር፤ ከዚህ ይልቅ ጋብቻ እንደማያስፈልጋቸው ኾነው ይኖሩ ነበር፡፡ የሩካቤ ፍላጎት፣ ፅንስ፣ ምጥ፣ ልጅ መውለድና ኹሉም ዓይነት ሙስና ከነፍሶቻቸው ውስጥ አልነበሩም፡፡ ከንጹህ ምንጭ ጽሩይ ወንዝ እንደሚፈልቅ፥ እነርሱም (አዳምና ሔዋንም) በገነት በድንግልና ውበት ተጽደልድለው ይኖሩ ነበር፡፡”

ቅዱስ ዮሐንስ ዘደማስቆም እንዲህ ይላል፡-
“ያን ጊዜ [አሁን የምናውቀው ዓይነት] ጋብቻ አልነበረም፡፡ ገና [አሁን በምናውቀው መንገድ] አልተገለጠም ነበር፤ ከዚህ ይልቅ ጋብቻ እንደማያስፈልጋቸው ኾነው ይኖሩ ነበር፡፡ የሩካቤ ፍላጎት፣ ፅንስ፣ ምጥ፣ ልጅ መውለድና ኹሉም ዓይነት ሙስና ከነፍሶቻቸው ውስጥ አልነበሩም፡፡”
113.6K views11:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-09-16 21:54:48 “የቃልህ ፍቺ ያበራል፥ ሕፃናትንም አስተዋዮች ያደርጋል።”
— መዝሙር 118(119)፥130
ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ምንነት እንዲሁም በመጽሐፍ ቅዱስ ላሉት ምንባባት አንድምታቸው ትንታኔና ማብራርያ የሚያገኙበት ቻናል ይቀላቀሉ

“መጽሐፍ” ለሚለው ምንጭ በግሪክ ቋንቋ ቢብሎስ (byblos) ከደንገል በተሠራ ወረቀት ወይም በብራና ከተጻፈ በኋላ በሁለት በትሮች...read more

መጽሐፍ ቅዱስ መቼ በአንድ ጥራዝ ተጠቀለለ? ከክ.ል.በ ይሁን በኋላ የተጻፉት ሁሉንም መጻሕፍቶች ለየብቻቸው ነበሩ፡፡ከ500ዎቹ ዓ.ዓ....read more

ኦሪት "ኦራይታ" ከሚል የሶርያ(አራማይክ) ቃል የተገኘ ሲሆን ትርጓሜውም "ሕግ" ወይም "ትምህርት" ማለት ነው።የመጠሪያ ምንጩም....read more
86.2K views18:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-09-16 14:00:03 ስለ ሰባቱ ሰማያት !
♡ጽርሐ አርያም ፦
ሰማየ ሰማያት ፣ ከሰማያት ሁሉ በላይ ያለች ሰማይ ናት ፤ ዳር ድንበሯ ከእግዚአብሔር
በቀር ማንም አያውቀውም፡፡
♡መንበረ ስብሐት ፦
አራት ቅርጽ ያላት ሲሆን ድንኳን ትመስላለች ፤ የምንኖርባትን ዓለም ታክላለች ። ሥላሴ
በፈለጉት መጠንና መልክ ለቅዱሳን ይገለጡባታል ። ሰባት የእሳት መጋረጃም አላት ።
ዘፍ ፳፰፡፲፪-፲፯
ኢሳ ፮፡፩-፪
♡ሰማይ ውዱድ ፦
ኪሩቤል የሚሸከሙት የሥላሴ ዙፋን ነው ።
ሕዝ ፲፡፲፱-፳
♡ኢዮር ፣ ራማ ፣ ኤረር ፦
እነዚህ ሦስቱ የመላእክት ከተሞች ሲሆኑ ከአድማስ እስከ አድማስ የተዘረጉ ናቸው ። ከላይ
ወደ ታች ፣ መጀመርያ ሰማይ ውዱድ ፤ ቀጥሎ ኢዮር ፣ ቀጥሎ ራማ፣ ቀጥሎ ኤረር የተያያዙ
ናቸው ። ስፋታቸውም እኩል ነው ።
♡ኢየሩሳሌም ሰማያዊት ፦
አራት መዓዘን ፣ 12 በሮች አሏት ፡፡ በውስጧ የብርሃን ሳጥን የተቀረጸ ከሥላሴ ፀዳል
የተሣለባት ታቦት ዘዶር አለች ፡፡ ይህቺም የእመቤታችን ምሳሌ ናት ፡፡
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ፦
ዓይን ያላየው ፤ ጆሮ ያልሰማው ፣ በሰውም ልብ ያልታሰበ ፣ እግዚአብሔር ለሚወዱት
ያዘጋጃት ያላት ይህቺው ናት
፩ኛ ቆሮ ፪፡፱-፲ ። መጠኗም የተወሰነ ነው ።
ባለ ራእዩ ዮሐንስ አዲሲቱ ሰማይ ያላትም ይህቺው ናት
ራእ ፳፩፡፪-፫ በጕበኖቿ የ12ቱ ሐዋርያት ስም ፤ በመድረኮቿ የ12ቱ ነገደ እስራኤል ስም ፤
በአዕማዶቿ የጻድቃን የሰማዕታት ስም ተጽፎባታል
ራእ ፳፩፡፲፩-፲፭ ።
(ስነ ፍጥረት)
87.5K views11:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-09-16 08:13:52 ኦሪት ዘፍጥረት 2፥1-3
1.“ሰማይና ምድር ሠራዊታቸውም ሁሉ ተፈጸሙ።”
#ሠራዊቶቻቸውም : - በውስጣቸው ያሉት ፍጥረታትንም ሁሉ ፈጥሮ ጨረሰ።
@yemetshaf_qdus_tinat
2.“እግዚአብሔርም የሠራውን ሥራ በሰባተኛው ቀን ፈጸመ፤ በሰባተኛውም ቀን ከሠራው ሥራ ሁሉ ዐረፈ።”
#ሰባተኛው_ቀን : - ብርሃንና ጨለማ የተለያዩበት ከስነ ፍጥረት የመጀመርያው ቀን(እሁድ) አንስተን አዳም እስከ ተፈጠረበት(አርብ) ያለውን የብርሃንና የጨለማ ዑደት(ዙር፣መፈራረቅ) ብንቆጥር 6ቀን ይሆናል ስለዚህ ሰባተኛዋ ቀን ቀዳሚት ሰንበት (የመጀመርያዋ ሰንበት) በአይሁድ "sabbath" የምትባለዋ ናት።የመጀመርያዋ ሰንበት ወይም ቀዳሚት ሰንበት (በተለምዷዊ አጠራር ቅዳሜ) የመባልዋ ምክንያት #እሁድም ሁለተኛዋ ሰንበት(የክርስቲያን ሰንበት፣ሰንበት ዓባይ፣የጌታ ቀን) ተብላ ስለምትጠራ ነው።ስለዚህ እግዚአብሔር ከመፍጠር ያረፈው በሰባተኛይቱ ቀን ቀዳሚት ሰንበት ላይ ነው።
@yemetshaf_qdus_tinat

#ዐረፈ : -በስድስቱ ቀናት ከፈጠራቸው ፍጥረታት ተጨማሪ መፍጠርን #አቆመ #ተወ ማለት ነው እንጂ ፈጣሪ ውጣ ውረድ ድካም የለበትም!!።ይህ ቃል እግዚአብሔር ከፍጥረቱ ጋር ያለው ግንኙነት መገለጫም ነው። እንዴት? በሰባተኛይቱ ቀን ከስራው ሁሉ ዐረፈ ካለ በኋላ ማታም ሆነ ጠዋትም ሆነ አይልም አንድ የዕረፍት ቀን ላይ ነው።ፍጥረቱ የሆነው የሰው ልጅ ደግሞ ወደእርሱ እንዲመጣ(እርሱን እንዲያውቅ) በቃሉም እየኖረ እንዲያመልከው ከፈጣሪው ጋር ህብረት እንዲያደርግ ይፈልጋል።
@yemetshaf_qdus_tinat
እስራኤል ከግብፅ ሲወጡ ለአብርሃም ወደ ማለለት ምድር ይገቡና እርሱን እያመለኩ በመንፈሳዊ ሐሳብ ከእግዚአብሔር ጋር ህብረት እንዲኖራቸው ነበረ ዓላማው ይህም ለዘለአለማዊው ከእግዚአብሔር ጋር የመኖርን ምሳሌ ነው።በእምነት ቃሉን ሰምተው እየታዘዙት መኖር በመንፈስ ዕረፍቱን መውረስ መካፈል ነው።ነገር ግን ከግብፅ የወጡት ቃሉን ሰምተው አላመኑም ባለመታዘዝ አሳዘኑት ፈጣሪም ከኔ ጋር አንድነት ዕድል ፈንታ የላቸውም አለ።
@yemetshaf_qdus_tinat
“ነገሬንም ስላልሰሙ፥ በእውነት ለአባቶቻቸው የማልሁላቸውን ምድር አያዩም፤ ከእነርሱም የናቀኝ ሰው ሁሉ አያያትም፤”— ዘኍልቁ 14፥23

መዝ94(95)፥10-11 “ያችን ትውልድ አርባ ዓመት ተቈጥቻት ነበር፦ ሁልጊዜ ልባቸው ይስታል፥ እነርሱም መንገዴን አላወቁም አልሁ።ወደ #ዕረፍቴም እንዳይገቡ በቁጣዬ ማልሁ።”

ቅዱስ ጳውሎስም ይህን ዕረፍት በዕብራውያን መልእክቱ ሲያብራራው እንዲህ ይላል
“ለእነዚያ ደግሞ እንደ ተነገረ ለእኛ የምስራች ተሰብኮልናልና፤ ዳሩ ግን የሰሙት ቃል ከሰሚዎቹ ጋር #በእምነት_ስላልተዋሐደ አልጠቀማቸውም።ሥራው ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ ምንም እንኳ ቢፈጸም፦ እንዲህ፦ ወደ #ዕረፍቴ አይገቡም ብዬ በቁጣዬ ማልሁ እንዳለ፥ እኛስ ያመንን ወደ ዕረፍቱ እንገባለን።ስለ #ሰባተኛው_ቀን በአንድ ስፍራ፦ እግዚአብሔርም በሰባተኛው ቀን ከሥራው ሁሉ ዐረፈ ብሎአልና፤በዚህ ስፍራም ደግሞ፦ ወደ #ዕረፍቴ አይገቡም።እንግዲህ አንዳንዶች በዚያ እንዲገቡ ስለ ቀሩ፥ ቀድሞም የምስራች የተሰበከላቸው ባለመታዘዝ ጠንቅ ስላልገቡ፦ #ዛሬ_ድምፁን ብትሰሙት ልባችሁን እልከኛ አታድርጉ በፊት እንደ ተባለ፥ ይህን ከሚያህል ዘመን በኋላ #በዳዊት ሲናገር፦ ዛሬ ብሎ #አንድ_ቀን እንደ ገና ይቀጥራል(ይወስናል)።” ዕብ4፥1-7
@yemetshaf_qdus_tinat

3.“እግዚአብሔርም ሰባተኛውን ቀን ባረከው ቀደሰውም እግዚአብሔር ሊያደርገው ከፈጠረው ሥራ ሁሉ በእርሱ ዐርፎአልና።”
#ባረከው_ቀደሰውም : - መልካም ነገር እንዲያስገኝ መልካም እንዲሆን መረቀው ለራሱም ለየው።
#በረከቱም እስራኤላውያን በነቢዩ ሙሴ መሪነት ከባርነት ወጥተው አምላካቸውን አውቀው ህግም በተሰጣቸው ጊዜ ከባርነት ወጥተው ብቻ ሳይሆን ከስጋ ስራም በእግዚአብሔር ስራና ዕረፍት ምሳሌ 6 ቀን ሰርተው በሰባተኛይቱ ቀን እንዲያርፉ ሲታዘዙ፤ከሰማይ ይዘንብላቸው የነበረው መና ለነገው ማሳደር አልተፈቀደላቸውም ለቀኑ በቅቷቸው ካደረ መናው ይበላሻል ለየቀኑም አዲስ የዘነበ ይበሉ ነበር በስድስተኛይቱ ቀን ግን ከዘነበው መና የሁለት ቀን ይሰበስቡና በሰባተኛይቱ ቀን መናም አይዘንብም ያደረውም አይበላሽም አርፈው ይመገቡት ነበር (ዘጸ16)።

ዕብራውያን 4
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁹ እንግዲያስ የሰንበት ዕረፍት ለእግዚአብሔር ሕዝብ ቀርቶላቸዋል።
¹⁰ ወደ ዕረፍቱ የገባ፥ እግዚአብሔር ከሥራው እንዳረፈ፥ እርሱ ደግሞ ከሥራው አርፎአልና።
¹¹ እንግዲህ እንደዚያ እንደ አለመታዘዝ ምሳሌ ማንም እንዳይወድቅ ወደዚያ ዕረፍት ለመግባት እንትጋ።
76.5K views05:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-09-13 08:06:42 እውነተኛ ወዳጅ፥ ወዳጅ መኾኑ የሚታወቀው ጓደኛውን መገሠጽ ሲችል ነው፡፡ ኹላችንም በየጊዜው ኃጢአት እንሠራለን፡፡ አብዛኞቻችን ደግሞ ኃጢአታችንን እንዳላየነው ኾነን ለማለፍ እንጥራለን፡፡ ለራሳችን ይቅርታ እንቸራለን፡፡ ወይም ምንም እንዳላጠፋ ሰው ለመምሰል እንሞክራለን፡፡ በእንደዚህ ዓይነት ሰዓት እውነታውን በትክክል እናይ ዘንድ ዓይናችንን የሚከፍት እውነተኛ ወዳጅ ያስፈልገናል፡፡

አንተ ሆይ! እስኪ ራስህን መርምር፡፡ ጓደኛህ እውነታውን እንዲያይ ታደርጋለህ? ጓደኛህ ኃጢአት ሠርቶ ሲያበቃ ለራሱ ይቅርታ ሲያደርግ ይቅርታው ያደረገው ይቅርታ ትክክለኛ እንዳልኾነ እንዲያውቅ ታደርጓለህን? እንዲህ እውነታውን ስትነግረው ምናልባት ጓደኛህ አለአግባብ ሊቈጣህ ይችላል፡፡ ታዲያ ሲቈጣህ ለመታገሥ ዝግጁ ነህን? ወይስ ከዚህ በተቃራኒ የጓደኛህን ኃጢአት አይተህ እንዳላየህ ነው የምትኾነው?

ጓደኛ ስንመርጥ ከእኛ ጋር እውነተኛ ወዳጅ ሊኾን የሚገባውን መኾን አለበት፤ ስንቈጣው እንኳን ቁጣችንን ታግሦ ስናጠፋ የሚያርመን ሊኾን ይገባል፡፡ እንደዚህ ካልኾነ ጓደኝነት ጥልቀት አይኖረውምና፤ ጓደኞች ነን መባባላችን ጥቅም የለውምና፡፡

ልናውቀው የሚገባን ነገር ግን አለ፡፡ ጓደኛችን በሚያጠፋበት ሰዓት ተግሣጽ አስመስለን እንዲሁ ክብሩን በሚነካ መልኩ ልንናገረው አይገባንም፡፡ ተግሣጻችን ኹልጊዜ እውነቱን ብቻ እንጂ የተጋነነና ሌላውን መልካምነቱን የሚክድ መኾን የለበትም፡፡ ጥፋቱን ስንነግረው ኹልጊዜ በቀና ልብ እንደምንነግረው እርግጠኛ እንዲኾን ማድረግ አለብን፡፡ ይህን የምናደርገው ከፍቅራችን የተነሣ እንጂ ከቅናት ወይም ከንቀት እንዳልኾነ እንዲያውቅ ማድረግ አለብን፡፡ እውነተኛ ወዳጅነት ማለት ይህ ነውና፡፡

#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
79.7K views05:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-09-08 08:00:46 “እግዚአብሔር የሚወዳችሁ አንድም እግዚአብሔርን የምትወዱት ወንድም እህቶቼ ሆይ! እግዚአብሔር በሥጋ ከባረከን በላይ በነፍስ የባረከን ይበልጣልና ስለዚሁ ልናመሰግነው ይገባናል፤ ምድራዊ መጠጥን አንድም ምድራዊ መብልን ከመስጠት መንፈሳዊ መጠጥንና መብልን መስጠት ይበልጣልና፡፡ እግዚአብሔር አስቀድሞ ለእሥራኤላውያን መናውን የሰጣቸው በኋላም እስራኤል ዘነፍስ ለምንባል ለእኛ ቅዱስ ሥጋዉንና ክቡር ደሙን የሰጠንም ስለዚሁ ነውና በሥጋ ከሰጠን ይልቅ በነፍስ የሰጠን ስለሚበልጥ እግዚአብሔርን እጅግ ልናመሰግነው ይገባናል፡፡

እግዚአብሔር በሥጋ ሲባርከን በዚያው (በሥጋዊው ነገር ላይ ብቻ) እንድንቀር አይደለም፤ የበለጠ ወደርሱ እንድንቀርብ ነው እንጂ፡፡ ሥጋዊውን ስጦታ ይዘን የምንቀር ከሆነ ግን ዓላማውን ስተናልና ልናስተካክል ይገባናል፡፡

ተወዳጆች ሆይ! በአፍአ ከተባረክነው ይልቅ በነፍስ የተባረክነው ይበልጣልና ስለዚያ እግዚአብሔርን ልናመሰግነው ይገባናል ብዬ እማልዳችኋለሁ፡፡ ለምን? መንፈሳዊው ነገር ከእኛ ዘንድ ካለ፥ ሥጋዊ ነገር ቢቀርም ምንም አናጣምና፡፡ መንፈሳዊውን ካጣን ግን ከእኛ ዘንድ ምን ተስፋ፥ ምንስ መጽናናት ይቀርልናል? አስቀድመን መንግሥቱንና ጽድቁን እንድንሻ የተፈለገውም ስለዚሁ ነው፡፡

የምወዳችሁ ልጆቼ! አስቀድመን እውነተኛውን ሀብት ይኸውም ሰማያዊውን ሀብት እንለምን፤ ርሱንም ለማግኘት እንጣጣር ብዬ እማልዳችኋለሁ፡፡ ሌላው ከዚያ በኋላ ይቀጥላል፡፡ እኛ ስለለመንን ሳይሆን ልቡናችን ዋናውን ስለፈለገ፡፡ ጸሎታችንን የምናገላብጠው ከሆነ ግን በነፍስ በሥጋ የተጐዳን እንሆናለን፡፡”

(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)
69.4K views05:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-09-07 12:28:47 "ሰማዕትነት ስር ነው፡፡ ክርስቲያኖች ደግሞ ከዚኽ ስር የሚያቆጠቁጡ ምርጥ ዘሮች ናቸው፡፡ ብዙ ዛፍ የሚያቆጠቁጥበት ስር በለም አፈር ስለሚሸፈን አይታይም፡፡ ከዚያ በሚያቆጠቁጡ ዛፎች ግን ስሩ እንዴት እንደተመቸው ይታወቃል፡፡ ሰማዕታትም በግዙፉ ዓይናችን እንደምን ያለ አክሊል ሽልማት እንደተቀበሉ አይታየንም፡፡ ፍሬያቸው ግን እነርሱን መስለው እነርሱን አኽለው በሚጋደሉ ምርጥ ዘሮች ይታወቃል፡፡

ሰማዕታት አክብሩን ብለው አይናገሩም፡፡ ነገር ግን በክርስቲያኖች ልብ የሚዘሩት ፍሬ ምእመናንን በፍቅር ያስገድዳል፡፡ እነርሱን እንዲመስሉ ያሳስባል፡፡

ሰማዕታት እንደ ፍቅረኛ ናቸው፡፡ አንድ ሰው የፍቅረኛውን ስም በየአጋጣሚው ያነሣል፡፡ በዓይነ ሕሊናው ያስባል፡፡ በተለያየ መልኩ ያያል፡፡ ሰማዕታትም ለክርስቲያኖች እንደዚያ ናቸው፡፡ እጅግ የተወደዱና በፍጹም ከሕሊና የማይጠፉ ተወዳጆች ናቸው፡፡ የልጆቻችንን ስም በነርሱ ስም የምንሰይመው፣ ሥዕላቸውን ሥለን የምንተሻሸው የምንስመው ለሰማዕታቱ ያለንን ጥልቅ ፍቅር የምንገልጽበት መንገድ ስለኾነ ነው፡፡"

(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)
56.2K views09:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-09-03 23:44:10 "ፍትወት ያጠፍኦ ለሂሩት፤ ፍላጎት ቸርነትን ያጠፋል" (መጽሐፈ ገነት)

ፈተወ ማለት ፈለገ፣ ወደደ፣ ከጀለ፣ ተመኘ፣ ጎመጀ የሚሉ ፍካሪያት ያለው ቃል ነው። ነገሩ ክፉና ደግ የሚሆነው ግን በአስደራጊ፣ በአድራጊ፣ በአደራራጊ፣ በተደራጊ፣ በድርጊት ነው። ለምሳሌ፦ ፍላጎቱ፣ ምኞቱ፣ ውዴታው፣ እግዚአብሔርን ማየት ከሆነ አስመኝው ራሱ እግዚአብሔር ነው። ተመኝውም መልአክ ነው፣ አብርሃም ነው። መመኛው ሃይማኖት ነው ምኞቱም ሥላሴ፣ ድርጊቱም ጽድቅ ነው፣ ዋጋውም መገለጥ ነው። (አብርሃም አባታችሁ ቀኔን ሊያይ ተመኘ አይቶም ደስ አለው) "መላእክትን የሚያስመኛቸው" እንዲል።
አስመኚው ሰይጣን፣ መመኛው ልብ ጠዋይ፣ ክህደት፣ ፈቃደ ሥጋ፣ ፍቅረ ሢመት፣ ትካዘ ዓለም፣ ሀልዮ መንበር፣ ፍቅረ ዉሉድ፣ ብእሲት ወዘመድ፤ ምኞቱም ሹመት ብዕል ድሎት በጥቅሉ የዓለም የልዕልና ማማ ላይ መውጣት የሆነ ጊዜ ግን "እፎ መልዐ ሰይጣን ውስተ ልብከ፤ ሰይጣን በልብህ ስለምን ሞላ?" የሚያስብል ቅዱሳንን ወደ ታች የሚያስደምም ርኩሰት ይሆናል። የሐ.ሥራ ፭፥፬ እንዲህ ያለው ምኞት ነው ቸርነትን የሚያጠፋ የተባለው።

ሰው ሁሉ ቸርነትን አቡሃ ለምሕረት ከሆኑ ከሥላሴ ዘንድ ይሻል። ምሕረትን የሚያገኙ ደግሞ ምሕረትን የሚያደርጉ ናቸው። "ብፁዓን መሐርያን እስመ ሎሙኒ ይምሕርዎሙ፤ የሚምሩ ብፁዓን ናቸው ይማራሉና" እንዲል። ማቴ. ፭፥፯
ይህ ሳይሆን እነርሱ እየጨከኑ ምሕረት የሚፈልጉ ግን አስደራጊው ሰይጣን ምኞቱ ምሕረት ማድረጊያው ጭካኔ ስለሆነ ፍየል ምሥራቅ ምዝግዝግ ምዕራብ መሆኑ ነው። መድኃኒትን በመርዝ መጠጣት እድን ብሎ ቢጠጡት ማዳኑንስ ቀርቶ መግደሉ ይብስ። የሥላሴን ቸርነት እየፈለጉ መጨከንም ማስማሩ ቀርቶ ያስፈርዳል። ወዲህም ጭካኔ የዲያብሎስ ምሕረት የእግዚአብሔር ስለሆነ ከሰይጣን ተነስቶ ወደ እግዚአብሔር ከመቼ ዕለት ወዲህ ተደርሶ ያውቃል? "እምኀበ እግዚአብሔር ይጸንዕ ሑረቱ ለሰብእ የሰው መንገዱ ከእግዚአብሔር የሆነ እንደሆነ ይቀናል" ተብሎ ነውና የተጻፈው። መዝ. ፴፮፥፴፬

ወንድሞቼ ሆይ ሞሕረትን የምንፈልግ ከሆነ ምሕረት ይኑረን። ምሕረትንም ለማድረግ ፍላጎታችን እንጠብቅ። ፍላጎት ምሕረትን ይደመስሳልና። የቀደመው ጠላት ምሕረት አጥቶ የቀረው ምሕረት የለሽ ስለሆነ ነው። ምሕረት የለሽ ያደረገውም ፍላጎቱ ነው። የማይገባውን አምላክነት ተመኘ፤ በክህደት ተመኘ፤ ክፋ ፍላጎቱ በአምላኩ ላይስ እንኳ ጨክኖ አምላክ ነኝ አስባለው። ስለዚህ ምሕረት ያልተገባው ሆነ። ይሁዳ በጌታው ላይ ለመሸጥ ያስጨከነው ክፉ የገንዘብ ፍላጎቱ። ጸሐፍት ጌታን ለመስቀል እንጀራ አበርክተው ያበሏቸውን እጆች ለመቸንከር የጨከኑት ክብርና የሥልጣን ፍላጎት ነው። ሄሮድስ በእናታቸው ወተት ቤተልሔም እስክትነጣ፣ በሕጻናቱ ደም እስክትቀላ እነዚያን ሕጻናት ያረዳቸው ያለ ሽረት ከመግዛት ክፉ መጎምጀት ነው። ኮቲባ ለድንግል ለምን ውኃ አልሰጥም አለች? ቅናቷና ስስቷ ነው።

ዛሬም ደም የሚያስፈስስ እኔ ብቻ ልኑር ነው። በሚያለቅሱና እንባን ከማሩኝታ ጋር በሚያቀርቡ ዓይኖች ላይ የሚጨክኑ ሾተል የሚመዙ እጆች ደም የተቀባን እንጀራ መጥገብ የሚልጉ ክፋ ልቦች ያበቀሏቸው ናቸው። በትዳራቸው ላይ የሚደፍሩ ለትዳራቸው ምሕረት የሌላቸው "በቃ ይበተን" የሚሉ ክፉ ምኞት የሚገረኛቸው ናቸው። በርህርኂቷ እመቤት፣ በጽድልቷ ንግሥት፣ በወላዲተ አምላክ ጨክነው ከልባቸው አሰድደው የሚሰድቧት የዛሬ ሄሮድሶችም እኔ ልክበር ልበልጽግ ልብላ ከሚል ምቀኛ ልብ የሚወጣ አሳባቸው ነው። አባቶቻችን የሚገባን መመኘት ጠቢብነት ነው የማያገኙትን ሁሉ መመኘት ግን ምቀኝነት ነው ይላሉ። ሰው በድንግል ማርያም ቢቀና እኔም እኮ ከእርሷ ጋር እኩል ነኝ ቢል አምላክን መውለድ አይችልምና አጉል ምቀኝነት ሆኖ ይቀራል።

ሄሮድስ የማይተካከለውን እገላለሁ ብሎ ሕጻናትን እንደገደለ ዛሬም እመቤታችንን ከልባቸው አሰድደው በአእምሮ ሕጻናት የሆኑትን የቤተልሔም እርሷ ልጆችን በምንፍቅና ሾተል ያርዳሉ።
ሄሮድስ እመቤታችንን በእኩይ ፍላጎቱ በርኩስ ቅናቱ አሰድዶ ሞተ። ወዳጄ ቅናትና ምቀኝነት እናታችን ከልባችን አንዳያሰድብን እንጠንቀቅ። ስለረከሱ ሕልሞች ስለሚጣፍጡ የሐኬት እንቅልፎች ውዳሴዋን አቋርጠን የምሕረትን ጠል ያዘለችውን ደመና ከእኛ እንዳትሰደድ እንንቃ። ለሄሮድስ መሰለው እንጂ ርግቢቱስ ገላግልቷን ይዛ በበረሃ ጉያ ውስጥ መዐዛዋን እያወደች ነው። ስለ ክፉ ምኞታቸው ሰማይን ከነ ፀሐይዋ አሳድደው ለጨለሙ ሄሮድሶች ይብላኝ እንጂ እርሷስ በየገዳማቱ "ምስለ ወልድኪ ልዑል በዘባንኪ ኅዙል ጎየይኪ እፎ ድንግል ደወል እምደወል" እየተባለች ትወደሳለች። ብቻ ዘመዶቼ በአንድ በጎ ነገር ላይ "አይ ይቅርብኝ" የሚያስብል አሳብ በመጣ ጊዜ የሰይጣን እንደሆነ አስተውሉ። ለቅዱስ ምኞት ያብቃን!!!
( መጋቤ ሐዲስ ወብሉይ አባ ገብረ ኪዳን ግርማ)
57.9K views20:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ