Get Mystery Box with random crypto!

መንፈሳዊ የህይወት ምክር

የቴሌግራም ቻናል አርማ menfesawimeker — መንፈሳዊ የህይወት ምክር
የቴሌግራም ቻናል አርማ menfesawimeker — መንፈሳዊ የህይወት ምክር
የሰርጥ አድራሻ: @menfesawimeker
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 23.40K
የሰርጥ መግለጫ

መንፈሳዊ የህይወት ምክር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን
ወዳጄ ሆይ ! መንፈሳዊ ተጋድሎን አትፍራ፥ ከእርሱም አትሽሽ፡፡ ተጋድሎ ከሌለ ምግባር ትሩፋትም የለምና፡፡ እምነትና ፍቅርም ካልተፈተኑ በእውን ከአንተ ጋር ስለ መኖራቸው ርግጠኛ መኾን አይቻልምና፡፡
ለ አስተያየት ወይም መንፈሳዊ ጥያቄ ካሎት
@menfesawimekerbot

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2022-09-03 22:15:41 ለፕሮፋይል ፒክቸር የሚሆኑ መንፈሳዊ ፎቶዎች እንዲሁም የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች እና ለፀሎት የሚያበቁ ድንቅድንቅ እና አነቃቂ ጽሑፎችን  ለማግኘት Open የሚለውን በንካት ይቀላቀሉ።




●◎◍▷Open ● ◊ ● Open ◁◍◎●
●◎◍▷Open ● ◊ ● Open ◁◍◎●
●◎◍▷Open ● ◊ ● Open ◁◍◎●
●◎◍▷Open ● ◊ ● Open ◁◍◎●




እንዲሁም አዳዲስ እና ወቅታዊ መዝሙሮችን ለማግኘትና የመዝሙር ጥማቶን ለማርካት ከስር Join የሚለውን በመንካት ይቀላቀሉ።




●◎◍▷Join ● ◊ ● Join ◁◍◎●
●◎◍▷Join ● ◊ ● Join ◁◍◎●
●◎◍▷Join ● ◊ ● Join ◁◍◎●
●◎◍▷Join ● ◊ ● Join ◁◍◎●


.
215 views19:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 23:56:38
እንኳን ደስ አላችሁ በዩቲዩብ የምናውቀው #ማኅቶት_ቲዩብ አሁን ደግሞ በቴሌግራም መጥቷል ለመቀላቀል ከስር ያለውን ሊንክ ንኩት።




https://t.me/+SLPMr-p0D_QzRyzI
https://t.me/+SLPMr-p0D_QzRyzI
https://t.me/+SLPMr-p0D_QzRyzI




.
135 views20:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 23:12:13
እንኳን ደስ አላችሁ በዩቲዩብ የምናውቀው #ማኅቶት_ቲዩብ አሁን ደግሞ በቴሌግራም መጥቷል ለመቀላቀል ከስር ያለውን ሊንክ ንኩት።




https://t.me/+SLPMr-p0D_QzRyzI
https://t.me/+SLPMr-p0D_QzRyzI
https://t.me/+SLPMr-p0D_QzRyzI




.
262 views20:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-17 16:41:21 ስለ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ምን ያህል ያውቃሉ

ቤተክርስቲያን ክርስቶሰን ማን ብላ ታስተምረናለች

ቅዳሴ ማለት ምን ማለት ነው

ለምንስ እናስቀድሳለን

ስለ ፆም ፣ ጸሎት ፣ ጸበል እና ስለ ቅዱሳን መፅሐፍ ቅዱስ ምን ይላል

እነዚህንና ሌሎችንም መንፈሳዊ እውቀቶችን ለማግኘት ከስር ኦርቶዶክስን እንወቅ የሚለውን ቻናል ይቀላቀሉ። ለሌሎችም ያጋሩ።



https://t.me/+WZfnEN8qnrw2NWE0
https://t.me/+WZfnEN8qnrw2NWE0
https://t.me/+WZfnEN8qnrw2NWE0
22.9K views13:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-12 01:17:13 የማንንን ስብከት ፈልገው አጥተዋል ሁሉንም በአንድ ቻናል ይዘንላችሁ መጥተናል ከ58ሺህ በላይ ተከታይ ያለው ቻናል ከፍተናል

➥የመምህር ምህረተአብ አሰፋ ስብከት

➥የዲያቆን ሔኖክ ኃይሌን ስብከት

➥የመጋቤ ብሉይ ወሐዲስ አባ ገብረ ኪዳንን ስብከት

➥የቀሲስ ዶክተር ዘበነ ለማን ስብከት

➥የመጋቤ ሐዲስ እሸቱ አለማየሁ ትምህርቶች

➥የዲያቆን ዳንኤል ክብረትን እይታ

➥የሊቀ ሊቃውን ዕዝራ ሐዲስ ስብከት

ቻናሉን ለመቀላቀል ሰማያዊውን ይጫኑ

@YE_DINGL_MARIAM_LIJOCH
@YE_DINGL_MARIAM_LIJOCH]
@YE_DINGL_MARIAM_LIJOCH
2.9K views22:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-24 20:00:00 የተዋህዶ ልጅ የሆነ እንዳያልፉ

ለህይወት ውጣ ውረድ እጅግ አስፈላጊ ከሆኑት ወሳኝ ጸሎት እና በበረሃ ያሉ ቅዱሳን ሰይጣን አጋንንትን የሚያሽመደምዱበት በተዋሕዶ ልጆች እጅግ ተወዳጅ የሆነውን መስቀል አጥር ጸሎት እነሆ ከብዙ ልፋት በኋላ በአፕሊኬሽን ቀረበ ። ይህንን ጸሎት ሲጸልዩ እጅግ ከባድ የሚመስለው የ ችግር እና ፈተና ተራራ እንደ ጉም ሲተን እራስዎ ምስክር ይሆናሉ

አሁኑኑ ከላይ የተቀመጠውን መተግበሪያ በማውረድ ታላቅ በረከትን ወደቤትዎ ያስገቡ
ማሳሰቢያ : ቢያንስ ለ15 ወዳጅዎች ማጋራትዎን አይርሱ
መታዘዝ ከመስዋት ይበልጣልና::
መጽ ሳሙኤል ምዕ 15 ቁ.22
ለበለጠ መረጃ
https://t.me/tewhastore
42.6K views17:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-08 15:43:13 Ebakachu admetut...Nefsun madan mifelg hulu yadmetew



106.8K views12:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-05-07 12:40:32 " ያዳነን በቅዱስም አጠራር የጠራን እግዚአብሔር ነውና፥ . . ." (2ኛ ጢሞ 1፥9)

መለኮታዊ የሆነውን ተልእኮ ለመፈጸም ከቶ የሰውን ፈቃድ መጠበቅ የለብንም። እግዚአብሔር ወደራሱ ሲጠራን ማንንም አላማከረም፤የእኛን የልብ ፈቃድ ከመመልከት ውጪ። ማንም ደግሞ እግዚአብሔር ወደራሱ እንዴት እንደሳበንና ልባችንን እንደነካው ፍጹም የሆነውን ሚስጥር አያውቅም፤ ከድንጋይ ይልቅ ጠጣራ፣ እንኳን የሰውን የአምላክን ማንነት ክዳ በምድረበዳ ልኖረችው ልባችን፡ እንዴት አድርጎ ክርስቶስ በፍቅሩ መዶሻ እንዳፈረከሳት የሚረዳም ሆነ የሚያውቅ ፈጽሞ የለም። እናም ሰውን ደስ ከማስኘት ይልቅ አምላክን መታዘዘ ብርቱ ከሆነ ኪሳራ አውጥቶ ዘላለማዊ ትርፍ የሚስገኝ ነገር መሆኑን ልብ ልንለው የሚገባ ነገር ነው።

በልብህም ይሁን በአእምሮ ጽላት ላይ የተጻፈውን መልኮታዊ አጀንድ፣ ለእግዚአብሔር ይህን በሕዝቤ መካከል አደርጋለው ብሎ ሲያመልክትክ ለልብህም ሲናገራት ማንን አማክሮ ነው? ባጠገብህስ ማንን ምስክር አስቀምጦ ነው? አምልካዊ እይታውን መንፈሳዊ አይኖችህን አብርቶ በመንግስቱ ውስጥ የድርሻህን እንድትወጣ ያየውን እንድታይ እና እንድትከውን ራዕይን ሲሰጥህ ማንን ተማምኖ ነው? ከዚያ ከውዳቂ ሰፈር እውጥቶ ወደ አላማ እና ግቡ ወደ ሚያደርሰው የከበረ ሰረገላ ላይ ሲያሳፍርክ እርሱን ለመታዘዝና ለመሄድ " አማላክ ሆይ ይህው እኔ ላከኝ" በሚል ልብ በፊት ከመሆን ይልቅ ስለምን በዙሪያ ያልውን ነገር ማይት አስፈለገ? ስለምንስ ካምላክ ይልቅ የሰውን ፍቃድ እንጠብቃልን?? አብርሃም አምላኩን እሺ ባይልና ባይታዘዝ ለዓለሙ መዳን ተስፋ የሆነው የክርስቶስ የኪዳን ዘር ምን ይመስል እንደነበረ ማሰብ ከባድ ነው። ዳዊት ስንቅን ሊያደርስ ሲሄደ ከአምላኩ ይልቅ፡ የሰማውንና የታዘዘው ውንድሞቹን ቢሆን ፍልስጤም በእስራኤል ላይ ምን ያደርግ ይሆን? ከደም መፍሰስ ነጻ ወጥታ የክርስቶስን እግር በሽቱ የጠበችው ማሪያም መቅደላዊት ያንን ለማደረግ ለቧ ከውሰነው ውሳኔ ይልቅ ለደቀመዛሙርቱና በቤቱ ለነበረው ማጉረምረም ታዛ ወደ ኋላ ብትል " ይህ ወንጌል በተነገረበት ስፍራ ሁሉ" የተባለው ስለ እርሷ የተነገረው ምስክርነት ይነገር ይሆን?።

እርግጥ ነው እንዳንድ ጊዜ ተመክሮዎችንም ይሁን ምክሮችን በመልካምነቱ ከሰዎች መቀበል ይሁን፣ መስማትና መተግበር አስፈላጊ ነው፤ ፍጹም በሆነ መንገድ ግን ሰምቶ መልኮታዊውን የአምላክ ትዕዛዝ ለመታዘዝ የሰውን ፍቃድ መጠበቅ ፈጽሞ ስህተት ነው። " ጴጥሮስና ሐዋርያትም መልሰው አሉ። ከሰው ይልቅ ለእግዚአብሔር ልንታዘዝ ይገባል።" ሐዋ 5፥29
ልንታዘዘው የተገባውን የመልኮትን እጀንዳ ጊዜና ውቅት ልንቀጥርለት አይገባም በፍጹም፤ ዘግይቶ መታዘዝ ካለመታዘዝ አይለይም። እርሱ ነውና ለአላማው የጠራችሁ እርሱን ታዘዙት።

" የሚጠራችሁ የታመነ ነው፥ እርሱም ደግሞ ያደርገዋል።" 1ተሰ 5፥24
179.9K views09:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-04-24 11:16:16 #በእርሱ #ቊስል #እኛ #ተፈወስን

ጲላጦስም የካህናት አለቆችንና መኳንንትን ሕዝቡንም በአንድነት ጠርቶ እንዲህ አላቸው ሕዝቡን ያጣምማል ብላችሁ ይህንን ሰው ወደ እኔ አመጣችሁት እነሆም በፊታችሁ መርምሬ ከምትከሱበት ነገር አንድ በደል ስንኳ በዚህ ሰው አላገኘሁበትም፡፡ ሄሮድስም ደግሞ ምንም አላገኘም ወደ እኛ መልሶታልና እነሆም ለሞት የሚያደርሰው ምንም #አላደረገም፡፡ እንግዲያስ ቀጥቼ እፈታዋለሁ አላቸው (ሉቃ. ፳፫፥፲፬‐፲፮)

ጲላጦስ የጌታችንን ንጹሕ መሆን ካወቀ በኋላ ቀጥቼ #እፈታዋለሁ አለ፡፡ ንጹሕ በመሆኑ ምክንያት የተቀጣ #ከጌታችን በቀር ማን አለ? ጲላጦስ አይሁድን ደስ ለማሰኘት ስለፈለገ ያን ሁሉ ጥያቄና መልስና ሕጋዊውን የፍርድ ሒደት ማስፈጸም ትቶ በንጹሑ ጌታ ላይ ግርፋት እንዲወርድበት ፈረደ፡፡

ነቢዩ ኢሳይያስ #በውርደቱ ፍርዱ #ተወገደ ብሎ #እንደተናገረው ትንቢት ጲላጦስ በእርጋታ ጀምሮት የነበረውን ሕጋዊ የምርመራና የፍርድ ሒደት አሽቀንጥሮ ጥሎ (አስወግዶ) ከሕግ ውጪ በዚያች ቀን በአይሁድ እጅ የተዋረደውን ጌታ ያለ ፍትሕ እንዲገረፍ ወሰነበት፡፡ (ሐዋ. ፰፥፴፫)

ጲላጦስ #ኢየሱስን ይዞ #ገረፈው (ዮሐ. ፲፱፥፩) የጲላጦስ አሳብ #በመሰቀሉ ፈንታ ግርፋት ቢገረፍ ሕይወቱን ካዳንኩለት #ቢቆስል ምንም አይደለም የሚል ነበር፡፡ አይሁድም የግርፋቱን ጽናት አይተው ይሙት ማለታቸው እንደሚቀር ተስፋ አድርጎ ነበር፡፡ በዚህ ምክንያት ከትናንት ምሽት ጀምሮ ታስሮ ሲንገላታ ያመሸውን ፣ በሐናና ቀያፋ ግቢ ውስጥ ሲደበደብና በጡጫ ሲመታ ያደረውን ጌታ በምሕረት የለሾቹ የሮም ወታደሮች እጅ እንዲገረፍ አሳልፎ #ሠጠው፡፡

የሮማውያን ግርፋት እንደ አይሁድ ግርፋት በጅራፍ ብቻ አይደለም፡፡ የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ጸሐፊው አውሳብዮስ ዘቂሣርያ እንደገለጠው ጅራፉ በቆዳ ከተሠራ በኋላ በላዩ ላይ ስለታማ የሆኑ የብረት ኳሶች ሾለው የተሳሉ የአጥንት ስብርባሪዎች ይደረጉበታል፡፡ በዚህ አሰቃቂ የግርፋት መሣሪያና በጨካኞቹ ወታደሮች እጅ ወድቀው ሥቃዩን መቋቋም ተስኖአቸው የሞቱም ብዙዎች ናቸው፡፡

በጅራፉ ላይ የተሠሩት የብረት ኳሶችና የአጥንት ስብርባሪዎች በሚገረፈው ሰውነት ላይ ሲያርፉ ሥጋውን እየነጩ የሚነሡ ስለሆኑ ጅራፉ በሰውነት ላይ ማረፉ ብቻ ሳይሆን ከሰውነት ላይ የሚነሣበትም ቅጽበት እጅግ ለመግለጽ የሚከብድ ሥቃይ የሚያደርስ ነው፡፡ የግርፋቱ መጠን በጨመረ ቁጥር የደም ሥሮችና #አጥንቶች እስከሚታዩ ድረስ የሚጎዳ ፣ የጎድን አጥንቶችን መሰባበር ፣ ከፍተኛ የሆነ ውጪያዊና ውስጣዊ የደም መፍሰስ ፣ የሳንባ መጎዳት የሚያስከትል አሰቃቂ ሒደት ነው፡፡

በዚያች ቀን #ጌታችንን ለመግረፍ የተመደቡት ወታደሮች እስራኤልን በብርሃን ዓምድ በሌሊት የመራቸውን #አምላክ #ሙሴና #አሮንን #በደመና ዓምድ ያነጋገራቸውን አምላክ በድንጋይ ዓምድ ላይ ለመግረፍ ዕርቃኑን #አሰሩት፡፡ የካህናት አለቆችን ደስ ለማሰኘት ሲሉም በሙሉ ኃይላቸው በታላቅ ጭካኔ እጅግ ብዙ ግርፋትን አዘነቡበት፡፡ አንድ ገጣሚ እንዳለው በሙሴ አድሮ #የፈጣሪን ክብር ለማየት የለመነው የሰው ልጅ ፈጣሪ በጊዜው #ጀርባዬን #ታያለህ ብሎ የገባለትን ቃል ቢፈጽምለትና ጀርባውን ቢያሳየው ግርፋትን አዘነበበት፡፡ (ዘጸ. ፴፫፥፳፫) በእርግጥም ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ #ከጲላጦስ ግርፋትን ይቀበልበት ዘንድ ጀርባን ፈጠረ እንዳለው አምላክ ሰው የሆነውና ጀርባን ለራሱ ያዘጋጀው ስለ ሁላችን #ኃጢአትን #ግርፋትን ሊቀበልበት ነበር፡፡

የሮማውያን ግርፋት ቅዱስ ጳውሎስ እንደተገረፈው እንደ አይሁድ ግርፋት በመጠን ተወስኖ አንድ ሲጎድል አርባ ግርፋት አምስት ጊዜ ገረፉኝ› እያለ የተገረፈው ሰው በሕይወት ተርፎ እያስታወሰ የሚናገረው ዓይነት ግርፋት አይደለም፡፡ (፪ቆሮ. ፲፩፥፳፬)
ቤተ ክርስቲያናችን #የጌታችን ግርፋት #ስድስት #ሺህ #ስድስት #መቶ #ስድሳ #ስድስት ጊዜ እንደሆነ ስታስተምር አምስት ሺህ ነው ፣ አራት ሺህ ነው የሚሉም አሉ፡፡ ይህን አሰቃቂ ግርፋት በሺህ ለሚቆጠር ጊዜ መገረፉን ግን ሁሉም ሊቃውንትና የታሪክ ሰዎች ተስማምተውበታል፡፡ ጌታችን እጅግ መገረፉን የሚያሳየን መስቀሉን ባሸከሙት ጊዜ በየሥፍራው እስኪወድቅ ድረስ አቅም ማጣቱ ነው፡፡

የጌታን ግርፋቱንስ መቁጠር ቢቻልም እንኳን ሥቃዩን ግን እንዴት ልንቆጥረው እንችላለን? ቤተ ክርስቲያናችን ከሥጋው አልፎ አጥንቶቹ እስከሚታዩ ድረስ ስለ ተገረፈው አምላክ በዕለተ ዓርብ የምታነበውና የምታዜመው ራሱ #ክርስቶስ አስቀድሞ በነቢዩ ዳዊት አድሮ ስለሕማሙ የተናገረው የትንቢት ቃል የሥቃዩ መጠን ጥቂትም ቢሆን ለማሰብ ያግዘናል፡-

‹‹እንደ ውኃ ፈሰስሁ #አጥንቶቼም ሁሉ ተለያዩ ፤
ልቤ እንደ ሰም ሆነ #በአንጀቴም መካከል ቀለጠ…
#አጥንቶቼ ሁሉ #ተቈጠሩ እነርሱም አዩኝ #ተመለከቱኝም …
#አጥንቶቼ #ተነዋወጡ (መዝ. ፳፪፥፲፬፣፲፯፤፴፩፥፲)

ቅዳሴያችን እንዲህ ይላል #የወልድን መከራውን የሚናገር ምን ዓይነት አፍ ነው? ምን ዓይነት #ከንፈር ነው? ምን ዓይነት አንደበት ነው? #የፍቅር #ጌታ #ሕማማቱ በተነገረ ጊዜ ልብ ይለያል ፤ ሕሊናም ይመታል #ነፍስም #ትንቀጠቀጣለች #ሥጋም #ይደክማል በእውነትም #የጌታችንን ሥቃይ ለመግለጽ ምንም ዓይነት ቋንቋ ምንም ያህል ቅኔ አቅም አይኖረውም፡፡

ቅዱስ ኤፍሬምም :-
#በክርስቶስ #የተወደዳችሁ ሆይ ኑ! ወዲህ ቅረቡ በዚች ዕለት በዳዊት ከተማ የሆነውን አብረን እንይ #በተስፋው ቃል ሲጠበቁ የነበሩት የተመረጡት #የአብርሃም #ዘሮች ዛሬ ምን እንዳደረጉ እንመልከት! ጌታ ሆይ ረዥሙን ሥቃይህን ማን ሊገልጸው ይችላል?›› ይላል፡፡

ይህ ሁሉ የሆነው #ስለ #እኛኃጢአት ነበር፡፡ ኦሪት የሚገረፍ ሰው ‹‹የግርፋቱም ቊጥር እንደ ኃጢአቱ መጠን ይሁን›› ትላለች፡፡ (ዘዳ.፳፭፥፪) ጌታችን ማንም ስለ ኃጢአቱ ሊወቅሰው የማይችል ንጹሕ ቢሆንም #እግዚአብሔር #የሁላችንን #በደል #በእርሱ ላይ #አኖረ ስለተባለ ግርፋቱም በተሸከመው የእኛ ኃጢአት መጠን ሆነ፡፡

እርሱ #ስለመተላለፋችን #ቈሰለ ስለ በደላችንም ደቀቀ #የደኅንነታችንም ተግሣፅ #በእርሱ ላይ #ነበረ በአጋንንት እጅ ልትገረፍ የጸጋ ልብስዋን አውልቃ ዕርቃንዋን በሲኦል የወደቀች ነፍሳችንን ነጻ ያወጣት ዘንድ እርሱ በጨካኝ ወታደሮች እጅ #ዕርቃኑን #ተገረፈ፡፡

እኛን #ከሚገባን #ግርፋት ያድነን ዘንድ #ኢየሱስ የማይገባውን ግርፋት #ተገረፈ የተገረፈባቸውም አለንጋና ገመድ በደም ታለሉ ተነከሩ ከግርፋቱ ጽናት የተነሣ ሥጋው ሁሉ አለቀ #ሐዋርያው #ጴጥሮስ በመገረፉ ቊስል ተፈወሳችሁ በማለት እንደተናገረ በእርሱም ቊስል እኛ ተፈወስን (፩ጴጥ. ፪፥፳፬፤ኢሳ. ፶፫፥፭)

#ህማማት #በዲያቆ #ሄኖክ #ሀይሌ
129.1K views08:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-23 22:41:20 "ጸሎት በሕይወት ማዕበል ውስጥ መጠጊያ ወደብ፣ ማእበል ለሚያንገላታቸው መልሕቅ፣ የድሃው ሀብት፣ የባለጸጋው ደህንነት፣ የታማሚው መዳኛ ወይም ጤና ማግኛ ነው። ጸሎት መጥፎ ነገሮችን ያስወግዳል መልካሙን ይጠብቃል።"

#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
በጸሎትህ ጊዜ አምላክህን አመስግን
የውስጥ ችግርህን አዋየው የፈለከውን ንገረው የውስጥህን አውራው ሁሉም ማድረግ የሚችል አባት ስላለህ እመነኝ ጸልይ ይሰማሀል
ማታ ማታ
።።።።።።የማታ ጸሎት።።።።።።
#ውዳሴ ማርያም የለቱን
# መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ 11እስከ 15ያሉትን ምዕራፍ ትጸልያለህ
# 1ጴጥሮስ ምዕራፍ 3 በሙሉ
# እግዚኦ ማሀረነ ክርስቶስ 24
# በእንተ ማርያም ማሀረነ ክርስቶስ 24
የግልህን የውስጥህን አውርተህ
አባታችን ሆይ ጸሎት አድርሰህ ትጨርሳለህ
እግዚአብሔር አምላክ የማታ ሰው ይበለን
የመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጸሎቷ ልመናዋ ይደርብን
አሜን
ማታ 4 ሰዓት ባለንበት በጋራ እንጸልይ
የተለየ ሀሳብ ወይ ይህ ቢሆን ገንቢ ሀሳብ ካላችሁ በውስጥ መስመር ላኩ
109.3K views19:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ