Get Mystery Box with random crypto!

ቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም

የቴሌግራም ቻናል አርማ memehirhenok — ቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም
የቴሌግራም ቻናል አርማ memehirhenok — ቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም
የሰርጥ አድራሻ: @memehirhenok
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 12.40K

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 16

2023-02-06 13:30:18
2.2K views10:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-06 13:30:12 #_ኢሃዴግ_እንኳን_አጀንዳ_ቀርጾ_ኦርቶዶክስን_ለማፍረስ_አልተነሳም!

ሰይጣን_ቤተ_ክርስቲያንን_እየተዋጋት ያለው በመንግስት በኩል ነው!

በቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም!

ሼር በማድረግ ለወዳጆ አዳርሱ!

ወዳጆቼ መንግስት እንደ መንግስትነቱ ሀገርን ለማሳደግ፣ የሕዝብን ኑሮ ለማሻሻል ተግቶ ይሠራል እንጂ እንዴት አጀንዳ ቀርጾ ኦርቶዶክስን ለማፍረስ ለመከፋፈል ይሠራል?

የሕገ ኦሪቱን እንተወውና በዘመነ ሐዲስ ኪዳን በኢትዮጲያዊው ጃንደረባ በ 34 ዓ.ም ሥርዓተ ጥምቀትን የተቀበለች፣ በአቡነ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን በ3ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ምስጢረ ቁርባንን የተቀበለች እና የፈጸመች የሁለት ሺ ዓመታት የሐዲስ ከዳን የአምልኮት ዘመንን ያሳለፈች የኢትጲያን ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን አምስት ዓመት ባልሞላው፣ በሁለት እግሩ ባልቆመው መንግስት ትፈርሳለች ማለት ሞኝነት ነው።

ኢሃዴግ 27 ዓመት ሀገርን ሲመራ ለፖቲካው ዕድሜ ማራዘሚያ ቤተ ክርስቲያንን ተጠቀመባት እንጂ ለማፍረስ ለመከፋፈል እጁን አላነሳባትም። የብልጽግናው መንግስት ግን ሀገርን በፊደል፣ በስነ ጹሑፍ፣ በኪነ ጥበብ ወዘተ ያበለጸገችውን የኦርቶዶክስ ኦርቶዶክስ ተዋህዶን ቤተ ክርስቲያንን ለማጥፋጥ መነሳቱ እጅግ ያሳዝናል።

መንግስት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖትን አጠፋለሁ፣ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን አፈርሳለሁ ካለ ከስልሳ ሚሊዮን ሕዝበ ክርስቲያን ጋር ነው ጦርነት ልግጠም የሚለው። በኢትዮጲያ ታሪክ ነገሥታት፣ መንግስት ሀገርን ማልማት ሕዝብን መምራት ትተው ያልበቸላውን ሲያኩ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ሲነካኩ ነው ዕድሜያቸው ያጠረው።

ከሃያ ሚሊዮን ሕዝብ በላይ በረሃብ ጠኔ የሚሰቃዩ ሰዎች በሀገራችን እንዳሉ ይታወቃል። መንግስት ሥራው የረሃብተኞችን ቁጥር መቀነስ እንጂ ኦርቶዶክስን ማፍረስ አጀንዳው መሆን የለበትም።

ምዕመናን ልብ ልትሉት የሚገባው ሰይጣን በተዘዋዋሪ ሳይሆን በጥታ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንን በግልጽ እየተዋጋት ያለው በመንግስት ነው። ከላይ እስከ ታች ፕሮቴስታንት ሆነው ነው ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንን እየተዋጉ ያሉት።

ወዳጄ ከሃዲው ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ የመንግስቱ እና የእሱም ዕድሜ ያጠረው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ እጁን አንስቶ ነው። ቅዱሳንን ገደለ፣ ቤተ ክርስቲያንን አቃጠሉ፣ ምዕመናኑን በጣዖት አምልኮ ከፋፈለ ነገር ግን የግፉ ፅዋዕ ሲሞላ እግዚአብሔር ቀሰፈው፣ ተልቶ፣ ሸቶ፣ የገዛ ሥጋውን እንደ አውሬ በልቶ በክፉ አሟሟት ሞቷል።

ዛሬ ዲዮቅልጥያኖስ የለም ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን አለች። ዛሬ የዲዮቅልጥያኖስ ስም አጠራሩ ጠፍቷል። እሱ የገደላቸውና ያስገደላቸው ቅዱሳን ሰማዕታት ከሞቱለት ጌታ ቃል ኪዳን ተቀብለው ለእኛ ተርፈው ይኖራሉ።

ዛሬ የሐሰተኛ ነብያትን የውሸት የፈጠራ ትንቢት እየሰማቹ፣ በሰይጣን ሞራል ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን እንከፍላለን ብትሉ እናንተው ትከፋፈላላችሁ። ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን እናፈርሳለን ካላችሁ እናንተ እና ሥርዓታችሁ ይፈርሳል። ኦርዶክስ ተዋህዶን እናጠፋለን ካላችሁ እናንተ ትጠፋላችሁ። ስለዚህ የግፍ እጃችሁ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን በማፍረስ ሳይሆን እጃችሁን በኪስ ብታደርጉት ይመረጣል።

መርሳት የሌለባችሁ በክርስቶስ ደም የተመሠረተች ቅድስት ቤተ ክርስቲያንና በክርስቶስ ደም የተገዛው ምዕመናን ደማቸውን እያፈሰሱ፣ ነፍሳቸውን እየለገሱ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት እና ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ይቀጥላሉ። ለኦርቶዶክስ አማኝ ሞት ሰማያዊ ሠርጉ ነው። የሚፈሰው ደሙ ለክርስቶስ የሚያቀርበው መስዋዕቱ ነው።

በነገራችን ላይ የኤሃዴግን ዕድሜ ያራዘመው በእሱ ዘመን ሌላው እንዳለ ሆኖ ሰላም መኖሩ፣ ሀገር መረጋጋቷ ብቻ ሳይሆን ኦሮቶዶክስ እንደ ኦርቶዶክስ ተከብራ ስለኖረች ነው። አየህ ወዳጄ በአንድ አጥብያ አንድ ቤተ ክርስቲያን ላይ ችግር ስትፈጥር በሚሊዮን ከሚቆጠረው ምዕመናን ጋር ነው ችግር ውስጥ የምትገባው።

መንግስት እንደ መንግስት መቀጠል የሚፈልግ ከሆነ በአፋጣኝ እጁን ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ ማንሳት አለበት። ኦርቶዶክስን በባለጊዜነት፣ በተረኝነት ስሜት፣ በዘረኝነት ለሁለት እከፍላለሁ፣ አማኙን አዳክማለሁ፣ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን አፈርሳለሁ የሚልበትን አጀንዳውን ለልማት፣ ለሀገራ አንድነት፣ ድህነትን ባታጠፉም ድህነትን ለመቀነስ ወዘተ ብትጠቀሙበት ሁሉም ኢትዮጲያዊ ከጎናችሁ ይቆም ነበር።

ኤሃዴግ እንኳን በዘመኑ ያልሠራውን ግፍ እናንተ አጀንዳ ቀርጻችሁ፣ ኦርቶዶክስን እናጠፋለን፣ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን የማንም መፈንጫ እናደርጋለን ካላችሁ ጠባችሁ ከስልሳ ሚሊዮን ኦርቶዶክሳዊ ጋር ብቻ ሳይሆን ከሰማይ አምላክ ጋር ነው። ኦርቶዶክስ ሀገር ናት ሲባል ቀልድ ይመስላቸዋል። ፊደል ቀርጻ የሰጠች፣ ሃይማኖትን፣ ሥርዓትን፣ ትውፊትን፣ ታሪክን በብራና ጽፋ የሰነደች፣ ጥበብን ያኖረች፣ ትውልድን በሥነ ምግባር የቀረጸች፣ ኢትዮጲያ እንደ ኢትዮጲያ እንድትቀጥልና እዚህ እንድትደርስ ያደረገች ናት። ልትመሰገን እንጂ ልትከፋፈል፣ ልትጠበቅ እንጂ ልትፈርስ አይገባም።

ኦርቶዶክሳውያን ሆይ መንግስት ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ እጁን እንዲያነሳ በደሙ የመሠረታት ኢየሱስ ክርሰቶስ መለኮታዊ እጁን በእነሱ ላይ እንዲያነሳ በርትተን፣ በንስሐ ሆነን እንጸልይ። ድህነቱን ቻልን፣ ዘረኝነቱን ቻልን ነገር ግን የነፍስ ጉዳይ በሆነው፣ በማንችለው በሃይማኖታችን መጥቷልና እግዚአብሔርን እንደ ሙሴ እጅህን አንሳ ልንለው ይገባናል። አሁን ያለነው የመጨረሻው መጀመሪያ ላይ ነው።

ጥር 29-5-15 ዓ.ም
አዲስ አበባ
2.7K viewsedited  10:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-05 21:52:35
1.4K views18:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-05 21:52:30 #_የኬልቄዶን_ጉባኤ_እና_የሲኖዶሱ_የአዋጅ_ጾም!

የዘመናችን ፓፓ ሊዮን ንጉሥ መርቅያንና ብርክልያ

በቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም

ሼር በማድረግ ለወዳጆ አዳርሱ!

ተወዳጆች ሆይ ቅዱስት ቤተ ክርስቲያናችን ሦስቱን ዓለም አቀፍ ጉባኤ ትቀበላለች አራተኛውን የኬልቄዶን ጉባኤ ግን አትቀበልም አውግዛ ለይታለች፡፡ የኬልቄዶን ጉባኤ በ 451 ዓ.ም የተካሄደ ነው፡፡ ጉባኤውም የመለያየት ጉባኤ ይባላል። የጉባኤው ዋና ዓለማ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን መጥቀም ሳይሆን ለሁለት መክፈል ነው፡፡

የኬልቄዶን ጉባኤ የሮም ነገስታትን የፖለቲካ ፍላጎት ለሟሟላት የተካሄደ ጉባኤ ነው፡፡ ፓፓ ሊዮን በኬልቄዶን ጉባኤ የንስጥሮስን የስህተት ትምህርት ይዞ ብቅ ቢልም ከፓፓ ሊዮን ጀርባ በተዘዋዋሪ ሳይሆን በቀጥታ የንጉሥ መርቅያንና የብርክልያ እጅ ነበረበት፡፡

ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ለፓፓ ሊዮን እና ለሮም ነገሥታት ፖለቲካዊ ፍላጎት አልገዛም፣ የስህተት እና የክህደት ትምህርት አልቀበልም በማለት ያመነበትንና እውነቱን በመናገሩ፣ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አንድ አካል አንድ ባህሪይ መሆኑን በመመስከሩ በንጉሥ መርቅያንና በብርክልያ ብዙ ግፍ ደርሶበት ጺሙን ከመነጨት እስከ ጥርስ መውለቅ ዋጋ ከፍሏል፡፡ ዓለም አቀፏ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ለሁለት የተከፈለችው፣ እስከ ዛሬም አንድ መሆን ያልቻለችው በጉባኤ ኬልቄዶን ነው፡፡

ወዳጆቼ ዛሬም የሆነው እንደ ኬልቄዶን ጉባኤ ነው፡፡ በቤተ ክርስቲያናችን ታሪክ ታይቶም ተሰምቶም በማይታወቅ ደረጃ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን አስተምራ፣ አክብራ የጵጵስና ማዕረግ የሰጠቻቸው አባቶች የኬልቄዶንን ጉባኤ አዘጋጅተው፣ የራሳቸውን ጳጳሳት ሾመው ከ1550 ዓመታት በኋላ ኦርቶዶክስ ተዋህዶን ለሁለት ለመክፈል ብዙ ርቀት ሄደዋል፡፡

ቀድሞ የነበሩት ፓፓ ሊዮን ማለት ያለ ቅዱስ ሲኖዶስ እውቅና ውጪ ቀኖናን በመጣስ 26 ኤጲስ ቆጶሳት ብለው በራሳቸው ሥልጣን፣ በማንአለብኝነት፣ የሾሙት ጳጳሳት ሲሆን፤ ንጉሥ መርቅያንና ብርክልያ ማለት ከሿሚዎቹ እና ከተሿሚዎቹ ጳጳሳት ጀርባ ሆነው፤ ኦርቶዶክስን በማዳከም እና ለሁለት በመክፈል የምዕራቡን ሃይማኖት የለሽ ዓለምን እና የራሱን ፖለቲካዊ ፍላጉት ለሟሟላት ደፋ ቀና የሚለው መንግስት ማለት ነው፡፡ እጅግ በጣም የሚያሳዝነው በእኛ ዘመን ይሄ መሆኑ ነው፡፡

አባቶችም ምዕመናንም እያንዳንዳችን በኬልቄዶን ጉባኤ እንደተገኘው እንደ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ መሆን አለብን፡፡ እውነቱን በመናገር እውነቱን በመመስከር መርቅያንና ብርክልያ እጃቸውን ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ እንዲያነሱ አባቶቻችን በቅዱስ ሲኖዶስ ያዘዙልንን ጾም ተግባራዊ ልናገደርግ ይገባናል፡፡ በተለይ የታዘዝነውን ጾመ ነነዌ በእውነተኛ ንስሐ ሆነን መጸለይ ግድ ነው፡፡

ያለ ንስሐ የሆነ ጸሎት፣ ጾም ወዘተ ቅድመ እግዚአብሔር ደርሶ የፓፓ ሊዮንን፣ የመርቅያንና የብርክልያን ሴራ አያከሽፍም፡፡ ስለዚህ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ የመጣውን ፈተና ተባብረን ለማራቅ እኛ ከኃጢአት በመራቅ መጸለይ አለብን፡፡ ዛሬ ቁጭ ብለን የሰቀልነውን ነገ ቆመን ተባብረን ማውረድ ያቅተናል፡፡ በዚህ በነነዌ ጾም የነነዌን ሕዝብ የተለመነ እግዚአብሔር እንዲለመነን የአባቶቻችንን ትዕዛዝ በመቀበል ሦስቷን ቀን መጸለይ ይገባናል፡፡

ፓፓ ሊዮን ንጉሥ መርቅያንና ብርክልያንን ተማምኖ፣ መርቅያንም ለፓፓ ሊዮን ወግኖ ነው የምስራቅ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ከምዕራቡ የሮም ቤተ ክርስቲያንና ከሌሎቹ መሰሎቻቸው ጋር የተለያዩት የተቆራረጡት፡፡ የዛሬዎቹም ፓፓ ሊዮኖች መንግስትን ተማምነው፣ ጊዜያዊ መንፈሳዊ ሥልጣንን ሽተው ነው ቤተ ክርስቲያንን ለሁለት ለመክፈል የሚሯሯጡት፡፡ ይሄ የሚርቀው በንስሐ በሆነ ጸሎት እና ጸሎት ብቻ ነው፡፡

ወዳጆቼ በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን እና በሃይማኖታችን ላይ የተፈጠረውን ችግር መጋፈጥ እንዳለ ሆኖ በጸሎት ወደ እግዚአብሔር ማንጋጠጥ መርሳት የለብንም፡፡ በነነዌ ጾም ለነነዌ ሕዝብ የተለመነ እግዚአብሔር እኛንም ይለመነን፡፡ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንም አንድነትን ይስጥልን፡፡

ጥር 28-5-15 ዓ.ም

አዲስ አበባ
1.5K viewsedited  18:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-03 23:15:46

1.8K views20:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-02 22:55:29

2.4K views19:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-02 21:16:45
2.5K views18:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-02 21:16:39 ምዕመናኑን ስለ ክፉ መናፍስት ውጊያ ያሳወቁ፣ ከ 30 ዓመታት በላይ በፈተና በታጀበ አገልግሎት የዘለቁ፣ ስድብን እንደምርቃት እየቆጠሩ፣ ትውልድን የአምልኮት ሕይወት ያስተማሩ፣ አገልግሎትን ካለመታከት፣ ተግባራዊ ክርስትናን ከጸሎት ጋር አስተባብረው የያዙት ክቡር አባታችን መላከ መንክራት መምህር ግርማ ወንድሙ! የማገለግላት ወለላይቱ እመቤት ዕድሜ ከጤና ጋር ትስጣቸው።
2.5K viewsedited  18:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-02 15:30:17
3.0K views12:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-02 15:30:09 #_የንስሐ_እና_የቄደር_ጥምቀት_ጥሪ

ጾመ ነነዌን በንስሐ እንቀበል!

#_እሑድ_ጥር_28_ጠዋት_2_ሰዓት

#_በእመብርሃን_መጥታችሁ_ንስሐ_ግቡ_ቄደር_ተጠመቁ

#_በወይን_አምባ_ቅድስት_ማርያም_ቤተ_ክርስትያን!

"ጥሩ ውኃንም እረጭባችኃለሁ እናንተም ትጠራላችሁ" ሕዝቅ 36፥25

"የትኛውንም ኃጢአት ብንሠራ ሁሉም ኃጢአቶች ከንስሐ በታች ናቸው። ከንስሐ በላይ የሆነ ኃጢአት የለም። የእኛ ኃጢአት ከእግዚአብሔር ቸርነት በላይ አይደለም"

#_ቄደር_ለመጠመቅ_የሚያበቁን_ኃጢአቶች_የትኞቹ_ናቸው?

#_ቄደር_ለምን_እንጠመቃለን?

#_ቄደር_በመጠመቃችን_ምን_ጥቅም_እናገኛለን?

የነፍስ ጉዳይ ነውና ሳትቸኩሉ በደንብ አንብቡት!

"የአሕዛብን ፈቃድ ያደረጋችሁበት በመዳራትና በሥጋ ምኞትም በስካርም በዘፈንም ያለልክም በመጠጣት ነውርም ባለበት ለጣዖት ማምለክ የተመላለሳችሁበት ያለፈው ዘመን ይበቃልና።" 1ኛ ጴጥ 4፥3

ቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም

#_ሼር_በማድረግ_የነፍስ_ግዴታዎትን_ይወጡ!

ተወዳጆች ሆይ እሑድ ጥር 28 ጠዋት 2 ሰዓት በወይን አምባ ማርያም ቤተ ክርስትያን የቄደር ጥምቀት እና ንስሐ የመስጠት አገልግሎት ስላለ መጥታችሁ ንስሐ ግቡ ቄደር ተጠመቁ። እባካችሁ ሰዓቱን ጠብቃችሁ ኑ። በተቻለ መጠን ደጇ ሁለት ሰዓት ድረሱ!

የጸሎት መርሃ ግብሩ ካለቀ በኋላ ብትጠመቁ ዋጋ የለውም። ምክንያቱም ለምሳሌ የጸሎቱ መርሃ ግብር ላይ አቡነ ዘበሰማያት 41 ጊዜ ካርያላይሶን 41 ጊዜ እግዚኦ መሃረነ ክርስቶስ ወዘተ እንድትጸልዩ ስለሚሰጣችሁ እነዚህን ጸሎቶች ሳትካፈሉ ሰዓት አርፍዳችሁ ብትመጡ መጠመቅ አይቻልም። ስለዚህ የነፍስ ጉዳይ ነውና ሰዓት ይከበር።

#_ቄደር_ለመጠመቅ_የሚያበቁን_ኃጢአቶች_የትኞቹ_ናቸው?

ቀደር ለመጠመቅ የሚያበቁን ኃጢአቶች ለምሳሌ ረቡዕ ብና አርብ የፍስክ ከበላን፣ ውርጃ ከፈጸምን፣ ከሃይማኖታችን ውጪ ካሉ ሰዎች ጋር ሩካቤ ሥጋ ከፈጸምን፣ በልጅነት እና ካደግን በኃላ ግብረ ሰዶም ከፈጸምን፣ ከእንስሳት ጋር ግንኙነት ካደረግን፣ በልጅነት መሬትን ካወሰብን፣

ከሥጋ ዘመድ ጋር ግንኙነት ከፈጸምን፣ ቅዱስ ቁርባን ተቀብለን በዝሙት ከወደቅን፣ በቅዱስ ቁርባን አግብተን ባል በሚስት ላይ ሚስት በባል ላይ ከዘሞተች፣ ኢ- ሩካቤ ከፈጸምን ማለት ከተፈጥሮ ውጪ የሆኑ ግንኙነቶችን ከፈጸምን፣ የአሕዛብን ምግብ ከበላን፣ ኦርቶዶክስ ሆነን ወደ ሌላ እምነት ገብተን ከተመለስን፣

ለዛር ለጨሌ ለአቴቴ ከገበርን፣ የተገበረውን መስዋዕት ከበላን፣ ጠንቋይ ቤት ከሄድን፣ ዛር አንጋሽ ጋር ከሄድን፣ ግለ ወሲብን ከፈጸምን፣ ሴት የወር አበባዋን ሳትጨርስ ግንኙነት ካደረገች፣ ወንድም የወር አበባ ካልጨረሰች ሴት ጋር ግንኙነት ካደረገ፣ ጫት ሲጋራ ከተጠቀምን ወዘተ ቄደር የግድ መጠመቅ አለብን።

ወዳጆቼ ልብስ በሳሙና ይታጠባል በመጨረሻ በኦሞ ተዘፍዝፎ ይለቀለቃል። በዚህም ጸዐዳ ይመስላል። ንስሐ ኃጢአታችንን የምናጥብበት ሳሙና ነው። ቄደር ደግሞ ኦሞ ነው ያነጻናል።

በተለይ ንስሐ ገብታችሁ ቅዱስ ቁርባን ለመቀበል ያሰባችሁ ቄደር ተጠምቃችሁ ብትቀበሉ መልካም ነው። በንስሐ ያላካተትነው ኃጢአት በቄደር ይነጻልና። እንዲሁም በቄደር ነጽተን ቅዱስ ቁርባን ብንቀበል ይሰምርልናል።

ሌላው ንስሐ ለመግባት አስባችሁ የንስሐ እድሉን ያላገኛችሁ እና ንስሐ አባት የሌላችሁ እሑድ ጥር 28 ቀን ጠዋት 2 ሰዓት መጥታች በደብሩ ካህናት ንስሐ መግባት ትችላላችሁ።

የእናንተን ችግር የሚረዱ በተለይ ለካህናት መናገር የምትጨነቁበትንና የምታፍሩበትን ለምሳሌ ግለ ወሲብንና የወሲብ ፊልምን የተመለከቱ ወዘተ ዘመን አመጣሽ ኃጢአትን የሚረዱ ካህናትን ስላዘጋጀን መጥታችሁ በነፃ ንስሐ ግቡ፣ የኃጢአት ሸክምን በእናታችሁ ቤት አራግፉ።

የወለላይቱ እመቤት ልጆች የትኛውንም ኃጢአት ብንሠራ ሁሉም ኃጢአተቶች ከንስሐ በታች ናቸው። ከንስሐ በላይ የሆነ ኃጢአት የለም። የእኛ ኃጢአት ከእግዚአብሔር ቸርነት በላይ አይደለም።

የእኛ ኃጢአት የደም ጠብታ ነው። የእግዚአብሔር ቸርነት ደግሞ ውቅያኖስ ነው። ስለዚህ የደም ጠብታ የውቅያኖስን ውሃ እንደማያደፈርስ ሁሉ የትኛውም የእኛ ኃጢአት የእግዚአብሔርን ቸርነት አይበልጥም። ንስሐ ግቡ ቄደር ተጠመቁ።

ስለዚህ እሑድ ጥር 28 ቀን ከጠዋቱ ሁለት ሰዓት ወይን አምባ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስትያን ኑ። ከጠዋቱ ሦስት ሰዓት ጸሎቱ ይጀመራል መጥታችሁ ተጠመቁ።

#_የትራንስፖርት_መምጫው ፦

ከየትኛውም አቅጣጫ የምትመጡ ጎሮ አደባባይ ወርዳችሁ፣ ሠፈራ ብላችሁ በባጃጃ ተሳፍራችሁ፣ ድልድዩን እንደተሻገራችሁ አስፓልቱ ጫፍ ላይ ቤተ ክርስትያኗ ትገኛለች።

ከመገናኛ ቀጥታ ወይን አምባ ማርያም የሚል ታክሲ አለ ቤተ ክርስቲያኑ በር ላይ ያወርዷቹኃል።

ከመገናኛ በቀጥታ ጎሮ ብለው ተሳፍረው፣ ጎሮ አደባባይ ወርደው፣ ከዚያ ባጃጅ ተሳፍረው፣ ሠፈራ ድልድይ ጫፍ ላይ ስትወርዱ ትገኛለች፡፡

ከሲ አምሲ፣ ከአያት፣ ከሰሚት የምትመጡ ጎሮ አደባባይ ወርደው፣ ባጃጅ ተሳፍረው ሠፈራ ድልድይ ጫፍ ወርደው ትገኛለች፡፡

ከቃሊቲ፣ ከቱሉ፣ ዲምቱ፣ ከኮዬ ፈጩ የምትመጡ ጎሮ አደባባይ ወርደው ከዚያ በባጃጅ ተሳፍረው ሠፈራ ድልድይ ወርደው ጫፍ ላይ ትገኛለች፡፡

ሐሙስ 25-5-15 ዓ.ም
አዲስ አበባ
2.8K viewsedited  12:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ