Get Mystery Box with random crypto!

የአዲስ ኪዳን ካህናት

የቴሌግራም ቻናል አርማ iyesusgetanw — የአዲስ ኪዳን ካህናት
የቴሌግራም ቻናል አርማ iyesusgetanw — የአዲስ ኪዳን ካህናት
የሰርጥ አድራሻ: @iyesusgetanw
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.56K
የሰርጥ መግለጫ

" እርሱም ደግሞ በመንፈስ እንጂ በፊደል ለማይሆን ለአዲስ ኪዳን አገልጋዮች እንሆን ዘንድ አበቃን፤ ፊደል ይገድላልና መንፈስ ግን ሕይወትን ይሰጣል።"
(2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 3:6)
✔የዚህ ቻናል አላማ #የጸጋውን_ወንጌል ለአለሙ ሁሉ ማወጅ ነው ፡፡
ለአስተያየት: @samidaba @sofiblessed
✆✆ ☞ 251941982842

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-22 06:28:35 #ጅማ #የኤፌሶን_መልዕክት_ጥናት #እኔ_ማነኝ??

(በህመም አይሳቅም: እንዳትስቁ) አንድ ጊዜ Psychiatric disorder(የአዕምሮ ህመም) ያለበት ታማሚ ለብዙ ጊዜ ከህመሙ የተነሳ #ባቄላ_ነኝ ብሎ ያምን ስለነበር ዶሮ ባየ ቁጥር እየፈራ ይሸሽ ነበር። እናም ከብዙ የስነ-አዕምሮ ህክምና treatment በኋላ ሰው መሆኑን አስረዱት። ከዚያም ከስንት ትግል በኋላ ምን ቢል መጥፎ ነው?? "እሺ አሁን ለእኔ ሰው መሆኔን አስረዳችሁኝ ግን ለዶሮዋ ማን ይነግራታል? " ነበር ያለው። አያችሁ ሰው #እንዲህ_ነኝ ብሎ ያመነውን ነገር በቀላሉ ማስጣል አይቻልም።ሰውም ሀጥያት የሚባል በሽታ ካመጣበት Psychic disorder ምክንያት በክርስቶስ ፀድቀሀል እየተባለ ይሄን እውነት ሲፈራና #ሲሸሽ ይኖራል።(ማንነቱን ባለመረዳቱም ለተሸነፈው ሰይጣን ሲንቀጠቀጥና ሲገዛ ይኖራል። በክርስቶስ ማን እንደሆነ ሲነገረውም #ለማመን ቢዘገይም የኤፌሶንን መልዕክት የመድሃኒት እንክብል መስጠት ተገቢ Treatment ይመስለኛል።
በክርስቶስ መሆኑን እርግጠኛ የሆነ ሁሉ የዚህ የክብር ህይወት ተካፋይ ነውና።

የኤፌሶንን መልዕክት ለማፍቀር የምንገደድበት ምክንያት በመንፈስ ወደ #ሰማያዊ_ስፍራ ከፍ የሚያደርግ መሆኑ ነው። ከዚህ መልዕክት ውጪ በየትኛውም የመፅሀፍቅዱስ ክፍል ይሄ ቃል አይገኝም።
ዘላለማዊ ምሉዕ የቃልኪዳን በረከት ያገኘንበት ስፍራ ነው። ( 1÷3 )
ታላቁ #ሊቀ-ካህናችን ኢየሱስ : በአሁኑም በሚመጣውም ዓለም ከሚጠራው ስም ሁሉ በላይ የገነነ ስም ያለው ኢየሱስ : ንጉሱ ያለበት ስፍራ ነው። (1:19-21)
የመንፈሳዊ
ህብረት(Communion)ስፍራ(2:6)
ሀጥያት እንደ አውሎንፋስ ጠራርጎ አርቆ ቢወስደንም መስቀሉ ሰበሰበን። የማይረጋው ልቤ ከሚለኝ እግዚአብሔር በቃሉ ሚለኝን ብሰማ ይሻለኛል ላለ ... የምስራች በክርስቶስ እጅጉን ቅርብ ሆነን ከእርሱ ጋር በሰማያዊ ስፍራ ተቀምጠናል።
ልዩ ልዩ መለኮታዊ ጥበብ ለቤተ ክርስቲያን የሚገለጥበት ስፍራ(3:10)
የተሸነፈን ጠላት የምንዋጋበት: የድል ነሺነት የውጊያ ስፍራ። (6:12)

#ሌላው በኤፌሶን መልዕክት ውስጥ በተደጋጋሚ እየመጣ ሀሴት የሚሞላን አንድ #የተባረከ_ቃል አለ። ይህም #በክርስቶስ( በእርሱ, in Christ , through Christ , by Christ , for Christ & so on) በዚች ከ 6 ምዕራፍ በማትበልጥ መልዕክት ውስጥ ቃሉ ከ50 ጊዜ በላይ ተጠቅሷል። መንፈስቅዱስ በቅዱስ ድርሰቱ ከ50 ጊዜ በላይ Remind ሊያደርገን የሚፈልገው ነገር በፀጋ የሆነልንና ተስፋ የምናደርገው ሰማያዊ ክብር ሁሉ በክርስቶስ ነው። እግዚአብሔር ሊሰጠን የሚችለውን #ሁሉ በክርስቶስ ሰጥቶናል። #ነፍሱን_የሰጠን_ምንም_እንደማይከለክለን_አስረዳን።

#ያለ_ክርስቶስ የነበርንበትን Extreme ዝቅጠት አሳይቶ : እንዲህ ወዳለ አስደናቂ ክብር በክርስቶስ ተሻገራቹ ሲለን ከምስጋና ውጪ ምን እንላለን??
(Regeneration by Christ)

ይሄን አስደናቂ መልዕክት የሚፅፍላቸው ሐዋሪያው ጳውሎስ ሳይድን(የጠርሴሱ ሳውል) ሊያያቸው እንኳ ለማይፈልግ Pagan Gentiles :ሲድን ህይወቱን አደጋ ላይ ጥሎ በኤፌሶን ወንጌል ሰብኳልና የጥል ግድግዳ በክርስቶስ ፈረሰ ሲል ያምርበታል። (Reconciliation by Christ )

#ታላቁ ሚስጥር እና አስደናቂው የጳውሎስ ፀሎት የሚደንቁ ሀሳቦች ሲሆኑ በመጨረሻም
Education of Grace
Excercise of Grace &
Exhortation of Grace ን በማብራራት መልዕክቱን ያጠናቅቃል።

እወዳችኋለሁ ተባረኩ
መልዕክቱን ያጋሩ

@untothelamb
@untothelamb
@untothelamn
91 viewsⓈ ⓘ, 03:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-04 14:33:06 #ልዑል_ወልደ-#አብ( ግጥም በታሜ(ሳሚ)

ነፍስ ከማወቁ እስከ ሽምግልና
የብራናው ጥቅልል ብሉዩ ሲጠና
'ምንድን ይሆን መላው?' ያረጀን ለት ጉድ ነው
አይናችን ሲደክም ማንበቡ ሲሳነው
ሲሉ የተጨነቁ
ለአይናቸው ጤንነት የተጠነቀቁ
እኚያ ሊቃውንቱ
ዕውቀት ፍልስፍናን የመረመሩቱ

መፃህፍት ወደ ልጁ ሲቀስቱ እንዳሉ
ሚስጥረ ሰማይን ባያውቁት በውሉ
በትንቢቱ ተስፋ ና'ፍቀውት ናፍቀውት
'መጣሁላችሁ' ሲል ጀርባቸውን ሰጡት

እንደምን መክሰር ነው ከከፍታ መውደቅ
ሲወጡበት ከርመው ከስኬቱ ማማ መሰላሉን መልቀቅ
ሲጓዙ መፀለይ ሲቀመጡ ማንበብ
በታወረ ፈረስ በሽምደዳ ጋሪ በፍጥነት መጋለብ
መድረሻው አያምር ግጥሙም ቤት አይመታ
ከጥንቱ ጀምሮ የሰሙት ያ ጌታ

ሁሉን በወረሰው በዓለማት ፈጣሪ
በክብሩ ነፀብራቅ አምሳለ ባህሪ
በስልጣኑ ቃላት ሁሉን በደገፈው
ያለ አንዳች ምሰሶ ሰማይን ባፀናው
ተራራ ሳንወጣ ደመና ሳይከበን
በመለኮት ሙላት ራሱን ሊገልጥልን
በልጁ ሲናገር ልባችን ካልሰማ
ከዚህ የተሻለ መናገሪያ መንገድ አብም የለውማ

ስሙኝ ልንገራችሁ
ልዑሉ ከመላዕክት አብዝቶ ይበልጣል
ከእነርሱ መሀከል ከቶ የትኛውን 'ልጄ ነህ' ብሎታል??
እሱን ተውትና
የትኛውን መልዓክ በአብ ቀኝ አያችሁ?
በልባችሁ መቅደስ በክርስቶስ ዙፋን ሌላ ያኖራችሁ
በእግዜር መልክ ቀርቶ በስጋ ሲገለጥ
ወድቀው እንዲሰግዱ እንደታዘዙለት
ማን በነገራችሁ

አይናችሁን አንሱ ከነቢያቱም ላይ
ጌታ መድሃኒያለም መልክተኛ ሳይሆን : ነው መልዕክተ ሰማይ
ነቢያቱማኮ
ምስክሮች ሆነው ልክ እንደ ደመና
ዝናብ እንዲመጣ ሰብከውናልና
እነሆኝ ኢየሱስ: የህይወት ምንጭ ውሃ
በፍቅሩ የሚያርስ የልብን በርሃ
ነቢያቱ በእርግጥ
'ከሀጥያት ተመለሱ ንስሃ ግቡ'አሉን
እርሱ ግን በደሙ
በራሱ አነፃው ሀጥያታችንን

ይሄ ጌታ ኢየሱስ
ከምትመኩበት ከሙሴም ይበልጣል
ይገደል ብትሉም ይሰቀል ብትሉም
ለራሱ ለሙሴ
'ያለና የሚኖር' እኔ ነኝ ብሎታል

እርሱ መድሃኒያለም ባሸነፈው ምድር
በመከራ ብዛት ልባችሁ ሲሸበር
"አዝናለሁ ጌታዬ: አንተ እስከምትመጣ ሁሉ ደና ነበር "
በሚለው በሚለው
ክርስቶስን ቀምሶ ወደ ሙሴ ጉዞ
ቅንጣትን መናፈቅ እልፍ አእላፉን ይዞ
ውድቀት ነው ሚዛኑ አይበጅም ስለ እውነት

ላመኑበት ሁሉ የመዳን ማህተም የሆነው ያ ትሁት
ለሚብሰው ቅጣት የኩነኔ አንቀፅ ነው ከዓለም ላሳነሱት
ብቻ ብቻ
ያ'ላጋን እንደሆን ፈተናው መዓቱ
መሰበር ማዘኑ መውደቅ መነሳቱ
ዘንግተነው እንጂ አንድ ነው እውነቱ

ከሀጥያት በስተቀር ተፈትናልና
ህመማችን በእርግጥ የሚያመው ነውና
"አንተ ምን አለብህ?' ላንለው በድፍረት
ቀድሞ ሄዷልና በምንሄድበት
የሰማይ ጠበቃ ለላቀው ክህነት
ደግሞም የታመነ የሚራራ ረዳት

መሆኑን በማወቅ
አይናችንን መትከል በልጁ ብቻ ላይ
የሚያበቃን ፀጋ ለመንግስተ-ሰማይ
ይቸረናልና
ከቶ አንሸቅጠውም የእርሱን ልዕልና !!

የዕብራውያን መልዕክት : ልጥፉን Share እወዳችኋለሁ

@untothelamb
@untothelamb
219 viewsⓈ ⓘ, 11:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-02 22:09:56
"ታላቅ የፍቅር ሥራ"

#ሰማንያ አሃዱ መጽሐፍ || በውስጡ ከያዛቸው 15ት መጽሐፎችን ፣ ከሌሎች 66 መጻሕፍትቶች ጋር የሚመዝነውን፣ የሚፈትሸውን ፥የነጠረውን እውነት በግልጽ የሚያሳየውን ድንቅ መጽሐፍ ፥ ተሻሽሎ ፣ተጨምሮ ፣ ተካብቶ ፣ጮማ ጮማ ነጥቦችን ይዞ ፥ ለ5ተኛ ግዜ ልታተም በሕትመት ቤት ውስጥ ገብቷል።
እንኳን ደስ አላችሁ ።

መጽሐፍ በገበያ ላይ እንድውል የእርሶ እሪዳታ አስፈልጎናል ።ለፍቅር ሥራ በፍቅር የተቻሎትን እንድታበረከቱ በእግዚአብሔር ስም ጥሪ አቅርበናል ።

TEWODROS DEMELASH ADAL

#የባንክ አካውንት:- 1000151023111 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ


#የባንክ_አካውንት:- 01320033464000 አዋሽ ባንክ
__________
187 viewsኢያሰጲድ ἴασπις, 19:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-21 21:55:13 https://t.me/jesus_daily?livestream=89e7e7361f4a99b8c8
259 viewsEphrem Bulbula, 18:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-19 22:33:37
አንድ ብቻ...
270 viewsቴዎድሮስ, 19:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-18 23:04:58
ለውጥማ አለ
286 viewsቴዎድሮስ, 20:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-17 22:56:19 #TRINITY_and_Salvation
ከጥቂት ጊዜያት በፊት አንዳንድ ትምህርተ ስላሴን ከማይቀበሉ የኑፋቄ አስተማሪዎች ጋር በአካል ተገናኝቼ ለማውራት እና ለመነጋገር ሞክሬ ነበር። እዚህ ግባ በማይባል አመክንዮ እና የመፅሀፍቅዱስ ጥቅሶችን እነሱ የሚፈልጉትን እንዲልላቸው በማስገደድ የተጠመዱ መሆናቸውን ተገንዝቤያለሁ። ስሁታኑ immature የሆኑትን ነፍሳት #በትጋት እያሳቱ በመሆናቸውም እጅግ አዝኛለሁ። ዳሩ ግን ሙሉ መፅሐፍ ቅዱስን አንብቦ ትምህርተ ስላሴን መካድ በሰይጣን Deceptive ሀሳብ ከመነዳት ውጭ ምንም ሊሆን እንደማይችል ግልጥ ነው። ትንሽ ነገር እንመልከት እስኪ

በሚያስደንቅ መንገድ #በዘመነ_ብሉይ የነበሩት ሶስቱ ታላላቅ አባቶችን ተመልክተን የስላሴን ምስጢር ህብረ አምሳል ገና በዘፍጥረት መፅሀፍ እናገኛለን።

#አብርሃም : የሚወደውን አንድ ልጁን ለመሰዋት ያልሰሰተ አብርሃም : "የሚወደውን አንድያ ልጁን ሳይሰስት(ለገዛ ልጁ ያልራራለት እንዲል) የሰጠንን" እግዚአብሔር #አብ'ን አያሳየንም??

#ይስሐቅስ ብትሉ : አባቱ ሊሰዋው በወደደ ጊዜ በሙሉ ፈቃደኝነት መታዘዙ " ይኸውም እስከመስቀል ሞት እንኳ የታዘዘ ሆነ " የተባለውን ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን በምሳሌ ገለጠው።

#ያዕቆብስ በስጋ እስራኤላውያን ለሆኑት ነገዶች አባት የሆኑትን አስራሁለቱን በመውለዱ #በነፍስ_እስራኤላውያን( ሮሜ 9:6 , ገላ 3:7&29 , ገላ 4) ለሆኑት ክርስቲያኖች ሁሉ አባት የሆኑትን 12ቱን ሀዋሪያት የወለደውን መንፈስ ቅዱስን በህብረ አምሳልነት አያሳይምን??

ይሄ ምስጢር ድንቅ ነው : አብርሃም ልጁን ለመሰዋት እንዲሄድ እግዚአብሔር 3 ቀን የሚያስኬድ መንገድ መምረጡ አጋጣሚ አይደለም። ይልቁንም 3 ቀን ሙሉ በአብርሃም ህሊና ይስሃቅ እንደሞተ መቁጠሩ(Amazing passion) : ነገር ግን እግዚአብሔር ተው ሲለው እንደሞተ የቆጠረውን ልጁን ዳግመኛ ማግኘቱ : 3 ቀን በመቃብር የነበር : በትንሳኤ ሀይል ደግሞ የተነሳውን ጌታችንን እንዲያሳይ እንጂ...

በአዲስ ኪዳን ደግሞ እንመልከት (የድህነታችን ምሉዕነት በሚስጥረ ስላሴ መገለጡን)

በሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ 15 ጌታችን 3 ድንቅ ምሳሌዎችን አስተማረ #የጠፋው_በግ , #የጠፋው_ድሪም, #የጠፋው_ልጅ ;እባካችሁ አንብቡት

በመጀመሪያው ምሳሌ በዘጠናዘጠኙ ሳይረካ አንዲቷን በግ ለመፈለግ የሚጠመደው ሰው : በጎቹ በጉስቁልና ወዳሉበት ስፍራ መቶ ሞቶ ያዳነን : በግልም የፈለገን የጌታችን ምሳሌ ነው።( Jesus loves you personally ; not just peoples as general )
ከዛ ሲያገኛት በደስታ በትከሻው ላይ አድርጎ ያመጣታል።ሀሌሉያ

በሁለተኛው ምሳሌ አንዲት ሴት የጠፋውን ድሪም በመብራት ትፈልገዋለች። #ድሪም አንድ ሰራተኛ በቀን የሚከፈለው የብር ሳንቲም ነው። ያ ሳንቲም በትቢያ ውስጥ ሲወድቅ አንፀባራቂነቱ እና ውበቱ ይጠፋሉ። የሚደንቀው ሳንቲሙ ላይ ያለውንም #ምስል ለማየት ያስቸግራል። በእግዚአብሔር መልክ የተፈጠረውም ሰው እንዲሁ ነው። የእግዚአብሔር መልክ አይታይበትም። ግን #በመብራት ፈለገችው። ይሄ መብራት #የመንፈስ_ቅዱስ ምሳሌ ነው። ይሄ ሳንቲም እንዲገኝ ቀን ሙሉ ስራ ተሰርቷል : ዋጋ ተከፍሏል። ( የክርስቶስ የመስቀል መከራ የአምላክ ሰው መሆን ሁሉ ስለ እኛ የተከፈለ ዋጋ መሆኑን ያስታውሷል። ) ያን ውበቱን : ያንን አንፀባራቂነቱን : ያንን እግዚአብሔርን መምሰል የሚመልሰው መንፈስ ቅዱስ ነው።

በሶስተኛው ምሳሌ : ሀላችንም በምናውቀው በጠፋው ልጅ ታሪክም ገና ልጁ ከሩቅ ሲመጣ ሲያይ በደስታ ሮጦ ያቀፈው የአብ አባት ምሳሌ ነው።
የተሻለው ልብስ(የእግዚአብሔርን ፅድቅ 2ቆሮ5:21) የወርቁ ቀለበት
የታደሰ ልዩ ህብረትን( 1ዮሐ 1:3) : ጫማው በወንጌል አደራ መመላለስን ( ኤፌ 6:15) : የሰባው ጥጃ በክርስቶስ ያገኘናቸውን በረከቶች ያመለክታል።( ኤፌ 1:3)

“በክርስቶስ በሰማያዊ ስፍራ በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ የባረከን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና #አባት ይባረክ።”
— ኤፌሶን 1፥3

እነዚህ ሶስቱ ምሳሌዎች የጠፋውን በመፈለግ እና በማዳን ስራ ውስጥ በሶስትነት ያለ እግዚአብሔር የሰራውን ስራ ያሳያሉ። #Trinity of Persons, in the unity of the divine essence. This unity of
essence, or nature, is asserted and secured, by their being said to be #one.

እወዳችኋለሁ። ተባረኩ

@untothelamb
@untothelamb
@untothelamb
290 viewsⓈ ⓘ, 19:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 16:59:08 ፀሀይ
ስለ አስደናቂዋ ፀሀይ ትንሽ ነገር ልበላችሁ እስኪ

ስለ Universe አስገራሚ እውነቶች ማወቅ : የህዋ ዘመናዊ ሳይንስን ማጥናት የአምላኬን አስደናቂ ጥበብ የማይመረመር ችሎታውንም እየተረዳሁ ሀሴት እንዳደርግ ስለሚያደርገኝ በመጠኑ interested ነኝ ሳይንሱን ለመመልከት።

ከፀሀይ መጠን ብንጀምር : መጠነ ቁሷ እጅግ ታላቅ ነው። #ፕላኔቶች ሁሉ ተደምረው የፀሀይን 0.1 ፐርሰንት ብቻ ይደርሳሉ። ከምንኖርባት መሬት ጋር እንኳን ብናወዳድራት የመሬትን 300,000 ዕጥፍ ይሆናል። ምን ያህል ግዝፈት እንደሆነ መሳል እንኳ ከባድ ነው።

ተፈጥሮዋ እንዲሁም ዑደቷ ፍፁም ውስብስብ እና ሰፊ በመሆኑ ልዝለለውና ስለ ማያልቀው የሀይል ምንጯ ትንሽ ልዳስስ

ፀሀይ በአንድ ቅፅበት(with in one second) 390000000000000000000000000(3.9×10^26) ጁል ጉልበት ታመነጫለች። በዚሁ በ 1 second 600 ሚሊዮን ቶን ሃይድሮጅንን ወደ ሂሊየም የምትቀይር ሲሆን የዚህ ጉልበት መጠን ሲሰላ #100_ሚሊዮን_ኒውክለር_ቦምብ
ጉልበት ያህል በ second ታመነጫለች ።

በጣም የሚደንቀው ለ6 ሰከንድ የምታወጣው ጉልበት ቢሰበሰብ የምድርን #ውቅያኖስ ውሃ ሁሉ #ማትነን ይችላል። የ3 ደቂቃ ጉልበቷ ደግሞ ቢሰበሰብ የመሬት የላይኛውን ንጣፍ (crust) ማቅለጥ ይችላል።

በአንስታይን "special theory of relativity " ባለው ህጉ መሰረት E=mc^2 መሰረት ቁስ አካሏ ወደ ጉልበት ሲቀየር ነው ወይ በሚል ጥናታቸውን የጀመሩ ሳይንቲስቶች ፀሀይ hydrogen fusion በሚባለው አካሄድ ፀሀይ ሃይድሮጅንን እያቀጣጠለች ወደ ሂሊየም በምትቀይርበት ጊዜ ይሄንን ታላቅ ሀይል ታመነጫለች በማለት አስቀምጠዋል።

ሌላም ብዙ ይላሉ : ነገር ግን መንገዱ ምንም ሆነ ምንም እኔን የሚያስደንቀኝ እግዚአብሔር ይህቺን ታላቅ ፍጥረት በቅፅበት መፍጠሩ ቅዱሱ መፅሀፍም ለዚህ ታላቅ ክስተት ከጥቂት መስመር በላይ አለማባከኑ የእግዚአብሔር የሀይልና የጥበቡን ታላቅነት ማሳየቱ ነው።

ዘፍጥረት 1
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁴ እግዚአብሔርም አለ፦ ቀንና ሌሊትን ይለዩ ዘንድ ብርሃናት በሰማይ ጠፈር ይሁኑ ለምልክቶች ለዘመኖች ለዕለታት ለዓመታትም ይሁኑ፤
¹⁵ በምድር ላይ ያበሩ ዘንድ በሰማይ ጠፈር ብርሃናት ይሁኑ፤ እንዲሁም ሆነ።
¹⁶ እግዚአብሔርም ሁለት ታላላቆች ብርሃናትን አደረገ ትልቁ ብርሃን በቀን እንዲሠለጥን፥ ትንሹም ብርሃን በሌሊት እንዲሰለጥን ከዋክብትንም ደግሞ አደረገ።

ከዚህ ክስተት በላይ ድህነታችን የተፈፀመበት የወንጌሉ ሂደት የእግዚአብሔር ታላቅ ሀይል እንደተገለጠበት ቅዱሱ መፅሀፍ ይነግረናል።

ኤፌሶን 1
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁸-¹⁹ ይህም #የልባችሁ_ዓይኖች ሲበሩ የመጥራቱ ተስፋ ምን እንዲሆን በቅዱሳንም ዘንድ ያለው የርስት ክብር ባለ ጠግነት ምን እንዲሆን ለምናምን ከሁሉ የሚበልጥ #የኃይሉ_ታላቅነት ምን እንዲሆን ታውቁ ዘንድ ነው፤
²⁰-²¹ ክርስቶስንም ከሙታን ሲያስነሣው ከአለቅነትና ከሥልጣንም ከኃይልም ከጌትነትም ሁሉ በላይና በዚህ ዓለም ብቻ ሳይሆን ነገር ግን ሊመጣ ባለው ዓለም ደግሞ ከሚጠራው ስም ሁሉ በላይ በሰማያዊ ስፍራ በቀኙ ሲያስቀምጠው በክርስቶስ ባደረገው ሥራ #የብርታቱ_ጉልበት_ይታያል፤

ሌላው #ፀሀይ አሁን ከምድር ያላት ከፍታ 93 million miles (149,598,000km) ነው ።

እና #አሁን ካላት ከፍታ ትንሽ #ከፍ ወይም ትንሽ #ዝቅ ብትል ፍጥረት sustain ማድረግ አይችልም። ይጠፋልም።

#ግና ከፍም ሳትል ዝቅም ሳትል #ቀጥ አድርጎ የያዛት ጌታዬ ኢየሱስ ነው ። በስልጣኑ ቃል ሁሉን ደግፎታል ክብር ለስሙ ይሁን።

“እርሱም ከሁሉ በፊት ነው ሁሉም በእርሱ ተጋጥሞአል።”
— ቆላስይስ 1፥17

“እርሱም የክብሩ መንጸባረቅና የባሕርዩ ምሳሌ ሆኖ፥ ሁሉን #በስልጣኑ_ቃል_እየደገፈ፥ ኃጢአታችንን በራሱ ካነጻ በኋላ በሰማያት በግርማው ቀኝ ተቀመጠ፤”
— ዕብራውያን 1፥3

ይሄን ውጥንቅጡ የወጣውን የምድሬን ሰለምና የቤተክርስቲያን ከከፍታዋ መዝቀጥ ተመልክ በሁሉን ቻይ ክንዱ ደግፎ ቀጥ እንዲያደርገው በስሙ ፀሎቴ ነው።

ልጥፉን share እወዳችኋለሁ ተባረኩ

@untothelamb
@untothelamb
@untothelamb
301 viewsⓈ ⓘ, 13:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-03 13:37:06
ሽንኩርት ጉድ አመጣች
340 viewsቴዎድሮስ, 10:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-03 10:24:32
ያዝ እንግዲህ
319 viewsቴዎድሮስ, 07:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ